Posts Tagged ‘ማህተብ’
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 2, 2020
ትክክለኛዋ እምነት በተዓምር፣ በማርያም መቀነት / በቀስተ ደመና የታጀበች እምዬ ኦርቶዶክስ ፥ አድዋ ዘምታ ጊዮርጊስ ድል ያደረገላት፣ መከላከያ ሚንስትሯ ጊዮርጊስ የሆነ፣ ጳጳሳቷ ለአገር የሞቱ፣ አንድነት የምትሰብክ፣ የድኾች መጠጊያ፣ ፀበሏ የሚፈውስ፣ እምነቷ የሚፈውስ፣ ደመራዋ የሚያምር፣ ጥምቀቷ የሚያምር፣ አፅዋማቷ የሚያምሩ፣ ሥርዓቷ፣ መጻሕፍቷ፣ ገዳማቷ፣ ውቅር ዓብያተክርስቲያናቷ፣ የካህናቱ ዝማሬው፣ ቅኔው፣ ማሕሌቱ፣ ቅዳሴው፣ አለባበሳችን ፥ ሁሉ ነገራችን እንደ ኦርቶዶክሶች የሚያምር የለም።
___________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: ሕፃን, መወለድ, ማህተብ, ማተብ, ተዋሕዶ, ኢትዮጵያ, የእግዚአብሔር ተዓምር, ፀረ-ክርስቶስ | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 14, 2020
አንገታችን ላይ ያለው መስቀል እና ማህተብ የሚፈተንበት ጊዜ ላይ ነን !!!
በ24/22 ሠፈር ባለፈው ሳምንት በግራኝ አህመድ ፖሊሶች የተፈጸሙትን ጽንፈኛ የግዳይ ተግባራት የተቃወሙ አባቶች በፖሊስ መታሰራቸው ይታወቃል።
በህገ–አልባው መንግስት የአሸባሪ አካል በተፈጸመዉ ነገር ሁሉ እጅግ ማዘናቸው አባቶች ተናግረዋል።
የታሳሪ አባቶች ስም ዝርዝር፦
1-ንቡረ ዕድ አባ ዮሐንስ የክፍለ ከተማው ቤ/ክ ስራ አስኪያጅ
2-መ/ አዕላፍ ቀሲስ ስንታየሁ ይግዛው የመስራች ኮሚቴዉ ሰብሳቢ
3-መ/ መዊዕ ቀሲስ እንዳለዉ ደምሴ የመስራች ኮሚቴው ጸሐፊ
4-ቀሲስ ፍቃዱ ፀጋ
5-መ/ር ኤልያስ አዳሙ
6-አቶ ሞላ ፍቃዱ
7-አቶ ጣዕመ ተኬ
8-አቶ ዮናስ ገብረ እግዚአብሔር
+_________________________________+
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: መስቀል, ሙስሊሞች, ማህተብ, አሕዛብ, ኢትዮጵያ, ክርስቲያኖች, ዋቄዮ አላህ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት, ደቡብ ኢትዮጵያ, ጂሃድ, ጋሞ ጎፋ, ጥላቻ, ፀረ-ተዋሕዶ ዘመቻ, ፪ሺ፲፪, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 13, 2019
ትክክለኛዋ እምነት በተዓምር፣ በማርያም መቀነት / በቀስተ ደመና የታጀበች እምዬ ኦርቶዶክስ ፥ አድዋ ዘምታ ጊዮርጊስ ድል ያደረገላት፣ መከላከያ ሚንስትሯ ጊዮርጊስ የሆነ፣ ጳጳሳቷ ለአገር የሞቱ፣ አንድነት የምትሰብክ፣ የድኾች መጠጊያ፣ ፀበሏ የሚፈውስ፣ እምነቷ የሚፈውስ፣ ደመራዋ የሚያምር፣ ጥምቀቷ የሚያምር፣ አፅዋማቷ የሚያምሩ፣ ሥርዓቷ፣ መጻሕፍቷ፣ ገዳማቷ፣ ውቅር ዓብያተክርስቲያናቷ፣ የካህናቱ ዝማሬው፣ ቅኔው፣ ማሕሌቱ፣ ቅዳሴው፣ አለባበሳችን ፥ ሁሉ ነገራችን እንደ ኦርቶዶክሶች የሚያምር የለም።
ቃለ ሕይወት ያሰማልን፡ ወንድማችን!
+______________________________+
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: 666, ሕፃን, መምህር ምህረተአብ, መወለድ, ማህተብ, ማተብ, ተዋሕዶ, ኖቤል ሽልማት, አብይ አህመድ, አውሬው, ኢትዮጵያ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እመነት, የእግዚአብሔር ተዓምር, የክርስቶስ ጠላት, ፀረ-ተዋሕዶ, ፀረ-ክርስቶስ | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 11, 2019
ለኢትዮጵያውያን ክብራቸው፣ ኩራታቸውና ደስታቸው ማሕተባቸው እንጂ በደም የተቀባው የኖቤል ሜዳሊያና የአይ.ኤም.ኤፍ ዶላር አይደለም። ከእነ ማሕተቡ መወለድ የበለጠ ፀጋ አለን?
ነፍሳቸውን የሸጡት ሜዲያዎችና እንደ እስስት ተለዋዋጪዎቹ የማሕበራዊ ድህረገጽ ተዋንያዮች ስለ እነ ገዳይ አብይ የቱርክ ድራማ ሌት ተቀን ከመለፈፍ ይልቅ ለራሳቸው ሲሉ ስለ ልጃችን የማሕተብ ተዓምር በማውሳት የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ ያለማቋረጥ ማወደስ ቢችሉ ይመረጥ ነበር። ግን አለመታደል ሆኖ አብዛኛዎቹ ሜዲያዎች በአውሬው እጅ ውስጥ ገብተዋል። ስለዚህ፡ ምስክራችን ከላይ ብቻ ነው!!!
የዚህች መልአክ የመሰለች ሕፃን የማሕተብ ተዓምር ዜና የበሰረበት ወቅት ልክ ገዳይ አብይ የኖቤል ሰላም ሽልማቱን ከሚቀበልበት ወቅት ጋር መገናኘቱ ያለምክኒያት አይደለም፤ ሰውየው ከክርስቶስ ተቃዋሚዎቹ አንዱ እንደሆነ 100% እርግጠኛ ነኝ፤ ስለዚህ፡ በተፈጥሯዊው ማሕተብ በኩል እግዚአብሔር እጅግ በጣም ትልቅ የሆነ መልዕክት እያስተላልፍልን ነው። ጆሮ ያለው ይስማ ፣ ዓይን ያለው ይመልከት፣ ላልደረሰው ያድርስ፡ ለ አስራ ሁለት ሩብ ጉዳይ ሆኗል!
+ ማተብሽን ፍች በጥሽው ቢሉኝ+
እኔስ ከነ አንገቴ ውሰዱት አልኩኝ
ፊተኛ ነንና አንዳንሆን ኋላኛ
ህዝቤ ተነቃቃ ተነስ አትተኛ
ጅብ ከሄደ ውሻ እንዳይሆን ጩኽት
የተዋህዶ ልጆች አሁነ ነው ሰዓቱ
አይተን እንዳላየን ስንቱን አሳልፈናል
የእርሱ ፈቃድ ይሁን ብለን ዝም ብለናል
አሁን ግን ይበቃል ዝምታው ይሰበር
+ይገለጥ ይታወጅ የተዋህዶ ሚስጢር+
ክርስቲያን ማለት ኢትዮጵያ ማለት ነው!
+____________________________+
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: 666, ሕፃን, መወለድ, ማህተብ, ማተብ, ተዋሕዶ, ኖቤል ሽልማት, አብይ አህመድ, አውሬው, ኢትዮጵያ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እመነት, የእግዚአብሔር ተዓምር, የክርስቶስ ጠላት, ፀረ-ተዋሕዶ, ፀረ-ክርስቶስ | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 11, 2019
ሰሞኑን አባ ዘ–ወንጌልን በተመለከተ አንዳንድ ሕልሞች ይታዮኝ ነበር። ሕልሞቹን ለማስታወስ እየታገልኩ ነው። አባታችን የጠቆሙን ነገሮች ሁሉ አንድ በአንድ በመፈጸም ላይ ናቸው።
አባታችን አባ ዘ–ወንጌል በአንድ ወቅት እንዲህ ብለውን ነበር፦
“ኢትዮጵያን በዚህ ወቅት እያስተዳደሯት ያሉት ጠላቶቿ ናቸው!”
አዎ! አውሬው ጦርነቱን አስቀድሞ በማካሄድ ላይ ያለው የቤተ ክርስቲያን በር በሆኑት በሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ላይ ነው፦
፩. ምሥጢረ ጥምቀት
፪. ምሥጢረ ሜሮን
፫. ምሥጢረ ቁርባን
፬. ምሥጢረ ክህነት
፭. ምሥጢረ ተክሊል
፮. ምሥጢረ ንስሐ
፯. ምሥጢረ ቀንዲል
መጀመሪያ በቁርባን(ሕብስትና ወይን / ስጋውና ደሙ) ፣ ቀጥሎም በጥምቀት ላይ ነው የዘመቱት። በኢትዮጵያ የእንጀራና ዳቦ መጋገር ባሕል ባልተለመደ መልክ የአሕዛብ ዳቦ ቤቶች በብዛት እየተከፍቱና በየትምህርት ቤቱ ለሕፃናቱ ዳቦና ማርማላታ እያጎረሷቸው መሆናቸውን እንዲሁም ዓብያተ ክርስቲያናት ባሕረ ጥምቀትን በመነጠቅ ላይ መሆናቸውን በግልጽ እያየነው ነው። የሰው ልጅ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ እንደማይችል ምቀኛው ጠላታችን ዲያብሎስ አጠንቅቆ ያውቃልና።
________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: ማህተብ, ባሕረ ጥምቀት, ቦሌ, ተዋሕዶ, አውሬው መንግስት, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, የረር, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እመነት, የእግዚአብሔር ተዓምር, የክርስቶስ ጠላት, ፀረ-ተዋሕዶ, ፀረ-ክርስቶስ | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 10, 2019
በእውነት በጣም የሚገርም ነው፤ ያውም በመድኃኔ ዓለም ዕለት ነው ሕፃኗ የተወለደችው። የአብ ሥራ እፁብ ድንቅ ነው! እግዚአብሔር በጥበቡ ያሳድግልን!
[ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ ፩፥፭]
“በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ።“
በአንገቷ ልዩ ምልክት ያሰረች ሕፃን ተወለደች::
በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዳንግላ ወረዳ በአባድራ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ በአንገቷ ላይ ልዩ ምልክት ያሰረች ህፃን መወለዷ ተገለጸ፡፡
የአባድራ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ አዋላጅ ነርስ እውነቱ አብየ እንደገለፁት ጥቅምት 27 ቀን 2ዐ12ዓ.ም ከሌሊቱ 8፡ዐዐ አካባቢ በውፍታ ዳጢ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ጥሩወርቅ አብነት በአንገቷ ላይ የክርስትና እምነት ተከታዮች የሚያደርጉትን የማተብ ምልክት በአንገቷ ያሰረች ሕፃን መውለዳቸውን ተናግረዋል።
ሕፃኗ ስትወለድ 3 ኪሎ ግራም የምትመዝን ስትሆን አሁን ላይ ሕፃኗም ሆነ እናቷ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡
የሕፃኗ እናት ወይዘሮ ጥሩወርቅ አብነት “ስትወለድ ክስተቱ አስደንግጦኝ ነበር፤ አሁን ግን ልዩ ማተብ አድርጋ የተወለደች ሕፃን ልጅ እናት ስለሆንኩ ደስተኛ ነኝ” ብለዋል፡፡
ምንጭ፦ ዳንግሌላ ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን
________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: ሕፃን, መወለድ, ሙስሊሞች, ማህተብ, ማተብ, ተዋሕዶ, ኢትዮጵያ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እመነት, የእግዚአብሔር ተዓምር, የክርስቶስ ጠላት, ፀረ-ተዋሕዶ, ፀረ-ክርስቶስ | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 11, 2019
እውነተኛው የእስልምና ገጽታ ይህን ይመስላል። ጊዜው የዋቄዮ–አላህ ልጆች ነው።
በአንዲት ሃገር የሙስሊሞች ቁጥር ከ30% በላይ ሲሆን እና ስልጣኑንም የጨበጡና ኃይሉን ያገኙ ሲመስላቸው ክርስቲያኖችን በዚህ መልክ ማሳደድና ማንገላታት ይጀምራሉ። ይህ ለ1400 ዓመታት ያህል በመላው አለም የታየ ነው፤ የቤተክርስቲያን ታሪክ ይህንኑ ነው የሚያስተምረን፤ አዲስ ነገር የለም።
በኢስላሞች እጅ ሰማዕትነትን የተቀበሉ ሰማዕታት የተደረጉ ጥናቶችና ቆጠራዎች እንደሚያሳዩት ከሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከነቢያቸው መሀመድ ዘመን ጀምሮ በኢስላሞች እጅ በጂሃድ እንቅስቃሴ የተገደሉ የሌላ ሃይማኖት ተከታዮች ቁጥር ከ270 ሚሊዮን በላይ ነው፡፡ ይህንም የሚያደርጉት እርኩሱ ቁርአን በግልጽ ስለሚያዛቸው ነው።
በቁርአኑ ውስጥ የመሀመድ አምላክ እስላም ባልሆኑት ሰዎች ልብ ውስጥ ሽብርን እንደሚነዛባቸው ነው የተነገረው፡፡ (ቁርአን 8:12፣ ቁርአን 8:57፟፣ ቁርአን7:4 ፣ ቁርአን 8:67፣ ቁርአን 33:26 & ቁርአን 59:2.) ነቢያቸው መሀመድ ለተከታዮቹም አስረግጦ የነገራቸው ገነት ሽብርን መሠረት ባደረገ ጎራዴ (ሰይፍ) ጥላ ስር መሆኗን ነው፡፡(ሳሂ ሙስሊም 41፡20፡4681፡)(ሳሂ ቡኻሪ 4፡51፡73)
ነቢያቸው መሀመድ ጀነት በጎራዴ (በሰይፍ) ጥላ ስር መሆኗን አስረግጦ ስለመናገሩ የሐዲሱ መጽሐፋቸው ምስክር ነው፡፡ ይህም ማለት ያለ ጂሃድ ጀነት አይገባም ማለት ነው፡፡ ቁርአኑም ይህንን ነው የሚያረጋግጠው፡፡ ስለዚህ መሀመድ እንዳለው አሸናፊ (ባለድል) የሆነው በሽብር ከሆነ፣ አላህም እርሱን በማያምኑት ሰዎች ልብ ውስጥ ሽብርን ከነዛ፣ ገነትም በሰይፍ ጥላ ሥር ከሆነች ማለትም ያለ ሰይፍ የማትወረስ ከሆነች “አሕዛብ በክርስቶስ ያመኑ ክርስቲያኖችን ለምን ይገድላሉ?” የሚለው ጥያቄ አሁን መልስ አግኝቷል ማለት ነው፡፡ ቀጥሎ የተጠቀሱት የቁርአን መመሪያዎች በደንብ ስናያቸው ደግሞ ጉዳዩ የበለጠ ግልጽ ይሆናል፡፡
– ጂሃድ–የእስልምናን እምነት ማስፋፊያ ብቸኛው መንገድ!
“ባገኛችሁባቸውም ስፍራ ሁሉ ግደሉዋቸው፤ ከአወጡአችሁ ስፍራ አውጡዋቸው፤ መከራም ከመግደል ይበልጥ የበረታች ናት፡፡” (ቁርአን–ሱረቱ አል–በቀራህ 2፡191፡፡)
“የተከበሩትም ወሮች (ረመዳን) ባለቁ ጊዜ አጋሪዎቹን (ኢስላም ያልሆኑትን) በአገኛችሁባቸው ስፍራ ግደሉዋቸው፤ ያዙዋቸውም፤ ክበቡዋቸውም፤ ለእነሱም መጠባበቅ በየመንገዱ ተቀመጡ፡፡” (ቁርአን–ሱረቱ አል–ተውባህ 9፡5፡፡)
“እነዚያ አላህንና መልዕክተኛውን የሚዋጉ፣ በምድርም ላይ ለማጥፋት የሚተጉ ሰዎች ቅጣት መገደል ወይም መሰቀል ወይም እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን በማፈራረቅ መቆረጥ ወይም ከሀገር መባረር ነው፡፡ ይህ ለርነሱ በቅርቢቱ ዓለም ውርደት ነው፣ በመጨረሻይቱም ለነርሱ ከባድ ቅጣት አላቸው፡፡” ሱረቱ አል–ማኢዳህ 5፡33፡፡
በጣም የሚያሳዝነው እና የሚገርመው ሌላ ነገር፤ ተዋሕዶ ካህናትና ምዕመናን በታረዱበት፣ ዓብያተክርስቲያናት እንደ ችቦ በእሳት በጋዩበት ማግስት፤ ለክርስቶስ ተቃዋሚውና ለክርስቲያኖች ገዳይ ሃሰተኛው ነብይ መሀመድ የልደት ቀን “እንኳን አደረሳችሁ!” ለማለት የሚደፍሩ “ተዋሕዶ ነን” ባይ ወገኖች መኖራቸው ነው። ከፍተኛ ቅሌትና ውርደት እንደሆነ ለማወቅ እንዴት ተሳናቸው? በራሳቸውና በቤተሰቦቻቸው ካለደረሰ በቀር ሁሌ በዓል?! ክርስቶስን ቢያስደስቱ ወይስ የተቃዋሚውን ዘሮች ቢያስደስቱ ደስ የሚላቸው?
_________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: መንፈሳዊ ውጊያ, ሙስሊሞች, ማህተብ, በደል, እስላም, እስልምና, ኦሮሞዎች, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን, ድሬደዋ, ጂሃድ, ግፍ, ጭፍጨፋ, ፀረ-ተዋሕዶ ዘመቻ, ፀረ-ኢትዮጵያ | Leave a Comment »