ልብ በል ወገኔ፤ በተዋሕዶ ልጆች ላይ እየተፈጸሙት ስላሉት መንግስታዊ ሽብርና ግዳያዎች አንድም የውጭ ሃገር የሜዲያ ተቋምና የዜና ወኪል አልዘገበም። በመላው ዓለም ለክርስቲያኖች ሰቆቃ ቆመናል የሚሉት እንደ “International Christian Concern” ያሉ ታዋቂ ተቋማት እንኳን አብዮት አህመድ ከመጣ በኋላ በኢትዮጵያ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ላይ እየተካሄደ ስላለው ጭፍጨፉ ሲናገሩ አይሰሙም። በሌላ በኩል ግን በ ቡርኪና ፋሶ ከሳምንት በፊት በሙስሊሞች ስለተገደሉት አሥር ጴንጤዎች እና በናይጀሪያም እንዲሁ በወጣት ሙስሊም አንገቱ ስለታረደው ታዋቂ ፓስተር ወይም 32 ጴንጤዎች ቸርቻቸው ውስጥ በፉላኒ ሙስሊሞች በእሳት ተቃጥለው ስለመሞታቸው ሁሉም የዜና ወኪሎች ዜናዎቹን እየተቀባበሉ ሲዘግቡ ተሰምቷል። እንደሚታየው ደም–አፍሳሹ የእስላም ጂሃድ በመላው አፍሪቃ በመጧጧፍ ላይ ነው።
በዚህ ሳምንት ግብረ–ሰዶማዊው የካናዳ ጠቅላይ ሚንስትር ጀስቲን ትሩዶ የአፍሪቃውን ህብረት ስብሰባ አጋጣሚ በማድረግ ወደ አዲስ አበባ ይጓዛል፤ ሜዲያው ይህን ጉዳይ ከፍተኛ አትኩሮት ይሰጠዋል። በጭካኔ የተገደሉት የተዋሕዶ ልጆችና የታገቱት እህቶቻችን ጉዳይ ይረሳል።
የአዲስ አበባ ልጆች ቅዳሜ የማንንም ፈቃድ ሳይሹ ወደ አፍሪቃ ህብረት ሕንፃ ሄደው በተቃውሞ ሰልፍ ሆ ብለው ለመጮህ ጥሩ አጋጣሚ አላቸው። የተገደሉትን ወንድሞቻችንን የታገቱን እህቶቻችንን ፎቶዎች ይዘው ቢወጡ እንዴት ጥሩ ነበር።
ልብ በል ወገን፤ በዛሬው የቀብር ስነ–ሥርዓት ላይ አንድም “አንድ ነን ፥ አብረን በልተናል ጠጥተናል” ተብሎ ሲነገረው የነበረው መሀመዳዊ አልተገኘም ነበር። አንድም! ለምን? ምክኒያቱም ጊዜው ሌላ ነውና ነው፤ ጊዜው አልፏል አብቅቷልና ነው። ዛሬ ጊዜው ሁሉንም ነገር ገላልጦታል፤ በፊት በተዋሕዶ መሪነት በጉም ፍየሉም ሁሉም አብሮ መኖር ይችል ነበር፤ አሁን ግን መናፍቅንና አህዛብን ጊዜ ስላነሳቸው ያው በተገደሉት የተዋሕዶ ልጆች ላይ በንቀት ሲስቁና ሲሳለቁ እያየን ነው። ወገን፤ እንደ ሎጥ ሚስት የጨው ሃውልት ሆነን እንዳንቀር ወደ ኋላ ባንመለከትና ከፍየሎች የምንለይበትን ይህን ጥሩ አጋጣሚ ብንጠቀምበት ይሻለናል፣ እራሳችንን እናድን!
መምህር ዘመድኩን በቀለ እንዳካፈለን፦
ትንናንት እንዲህ ነበር የሆነው፦
ከሁለቱ ሰማእታት በተጨማሪ በትናንትናው ዕለት ሞተ ተብሎ የዕረፍቱ ዜና ቅዱስ ፓትርያርኩ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለጸሎተ ፍትሃት በተገኙበት ቦሌ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ዐውደ ምህረት ላይ እንዲነገር የተደረገው ሦስተኛው ልጅ ጉዳይ ሆን ተብሎ በእነ ታከለ ኡማ አስተዳደር ሰዎች የተፈበረከ መሆኑ ተደርሶበታል ይላሉ ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ሰዎች። በትናንትናው ዕለት #ኦህዴድኦፒዲፒፒኦነግ ሆን ብሎ የሁለቱ በግፍ የተገደሉት ሰማዕታት ቀብር እንዲሰናከልና ረብሻ ተፈጥሮ በድጋሚ ሁከት ለመፍጠር ተጨማሪ ጥፋት ለማድረስ የተደረገ የጥፋት ሙከራም እንደነበርም ተነግሯል።
መጀመሪያ ጠዋት ላይ ከማኅበረ ቅዱሳን ቢሮ ነው የምንደውለው ያሉ ግለሰብ የቀብር አስፈጻሚው ኮሚቴ ዘንድ በመደውል የቀብር ስፍራና የቀብር ሰዓት ለውጥ እንዲደረግ ሃሳብ አቅርበው ኮሚቴው ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ እንዲገባ አስደርገው የነበረ ሲሆን ኮሚቴው ግን ቢሆን እንኳ ትናንት ነበር እንጂ አሁን ለፍትሃት ወደ ቦሌ መድኃኔዓለም እየሄድን ሳለ የምን ህዝብን ማደናገር ነው? ደግሞስ ለምን በዚህ ሰዓት መደወል አስፈለገ? በሚል በነገሩ ላይ በብዙ ከመከሩ በኋላ ከማኅበረ ቅዱሳን መጣ የተባለውን የቀብር ቦታና የቀብር ሰዓት ለውጥ ውድቅ አድርጎ ሂደቱ በነበረበትና በተያዘለት መርሃ ግብር እንዲቀጥል ተደርጓል። [ የቀብር ሥፍራው ቅድስት ካቴድራል እናስደርጋለን፣ የቀብር ሰዓቱ ከ9 ሰዓት ወደ 6 ሰዓት ይምጣ ባዮች ነበሩ የሃሳቡ አመንጪዎች ዕቅድ ]
ይሄ አልሳካ ሲልና ህዝቡ ግልብጥ ብሎ መውጣቱን ሲያዩ ደግሞ ቀድሞ የጥምቀት ተመላሽ ወጣቶች ሰብሳቢ በነበረችው እህታችን ፌቨን በኩል መንግሥት ረጅም እጁን ከሰድዶ ሌላ አፍራሽ ሃሳብ በማመንጨት ሌላ ሙከራ እንዳደረገም ተነግሯል። ፌቨን ቦሌ መድኃኔዓለም ድረስ በመሄድ ከቦሌ መድኃኔዓለም ከጸሎተ ፍትሃቱ በኋላ እስከ ገርጂ ጊዮርጊስ ድረስ የሚኬደው ጉዞ እንዲቀርና በምትኩ ራሷ ፌቨን እስከ 60 አውቶቡሶች በነፃ ማቅረብ እንደምትችል ለቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴዎቹ በመንገር የእግር ጉዞው እንዲቀር በብርቱ ጥራ ነበርም ተብሏል። ፌቨን ከደኅንነት ቢሮውና ከከንቲባው ቢሮ በቀጥታ የደረሰኝ መረጃ ነው። በጉዞው ላይ የእነ ጃዋር መሐመድ ቡድን መጠኑ ከፍተኛ የሆነ ፈንጂ ሊያፈነዳ በዝግጅት ላይ እንደሆነ ስለተደረሰበት የእግር ጉዞው ይቅር በማለት አጥብቃ ትሟገት እንደነበር ነው መረጃዎቹ ያመለከቱት። በመጨረሻ ግን ኮሚቴው የመጣ ይምጣ አንቺም ሂጂ ጥፊ። ቅድም በማኅበረ ቅዱሳን በኩል አሁን ደግሞ በአንቺ በኩል መንግሥት እንዲጋልበን አንፈቅድም፣ የሚመጣ ነገር ካለ እኛው እንወጣዋለን በማለት የጉዞ መርሀ ግብሩ በተያዘለት መርሀ ግብር እንዲቀጥል አስደርገዋል። ኮሚቴዎቹ።
እነዚህ ሁለቱ አሰናካይ ሃሳቦች አልሳካ ሲሉ የዐብይታከለ መንግሥት ሌላ የፈጠራ ዜና ቅዱስ ፓትርያርኩ ባሉበት ዐውደምህረት ላይ እንዲነገር አስደረገ ተብሏል። የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴዎችም ጉዳዩን የሚያጣሩበት ጊዜ ላይ ባለመሆናቸው ሚዲያዎችም ዜናውን ተቀባብለው ሠሩት። ይኸውም ዜና ምንድነው? የተባለ እንደሆን የሦስተኛው ልጅ የሞት ዜና ነበር። በዜናው ላይ ማስተላለፍ የተፈለገው ህዝቡ ዜናውን ሲሰማ በቁጣ ተነሳስቶ በስሜት ወደ ሁከት እንዲሄድ ተፈልጎ የነበረ ሲሆን ህዝቡ ግን እንኳን ሊረብሽ “ የሞተው ልጅ በረከቱ ይደርብን ብሎ ጭራሽ በዝማሬ ዜናውን በደስታ መቀበሉ ራሳቸው ዜናውን የፈበረኩትን ግራ እንዲጋቡ አድርጓልም ተብሏል።
በኦሮሚያ ፖሊስ ብልቱ ላይ የተመታውና ሆስፒታል የተኛው ወጣት ሀብታሙ ሲሆን እነ ታከለ ኡማ ሞተ ብለው ያስወሩት ተጎጂውን በማስታመም ላይ ያለውን ወንድሙን ወጣት አብርሃምን ነበር። የሃሰት ዜናው እንዲለቀቅ የተደረገው በአስታማሚው በወንድሙ በአብርሃም ነው። ይሄ ቅሽምናቸውን ነበር የሚያሳየው። እናም ሦስተኛው ልጅ እስካሁን አልሞተም። ምን አልባት ከዚህ በኋላ ካልገደሉት በቀር እስከአሁን አልሞተም ነው የሚሉት የመረጃ ምንጮቼ።

ሌላው አስቂኙ ነገር በኦሮሚያ ፖሊስ ታፍሰው የታሰሩት የ24 ቀበሌ ልጆች በሙሉ በታከለ ኡማ ትእዛዝ ከታሰሩበት ወኅኒቤት በዛሬው ዕለት ተፈትተዋል ተብሎ ሌላ ዜና እንዲሠራም ተደረገ። ዜናው እንዲሠራ ከተደረገ በኋላ ግን ህዝቡ በደስታ ስሜት ለጥቂት ደቂቃዎች ብቻ እንደሚቆይ አለማወቃቸው ዜናውን የፈበረኩት ፖለቲከኞች ምን ያህል ርጥብ ቄጤማ የሆነ ሰገጤ ፖለቲከኞች እንደሆኑና ሀገሪቷን የሚሚመሩት ምንያህል ጨቅላዎች እንደሆኑ ማሳያ ነውም ይላሉ ታዛቢዎች። ታከለ ኡማ የታሰሩትን 30ዎቹንም የ24 ቀበሌ ልጆችን በዛሬው ዕለት ፈትተናቸዋል ብሎ ጋዜጠኞች ሰብስቦ ቢናገርም፣ በፌስቡክ ገጹም ላይ ቢጽፍም የቦሌ ክፍለከተማው ሂትለር ግን “ ታከለ ምን አገባውና ነው የሚፈቱት? ” በማለት አንዳቸውንም ያለመፍታቱ ተነግሯል። የቦሌው ሂትለር በስልጣን ታከለ ኡማን ይበልጠዋልም ተብሏል። የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል በመሆን ታከለን ይበልጠዋል። ስለዚህ ታከለ ይሄን ትእዛዝ የሰጡና በምሽት ሰዎች እንዲገደሉ ያደረጉ አካላት ለፍርድ ይቀርባሉ ሲል አለቃውን እያለ ያለው አለቃዬን አስራለሁ ማለቱ እንደሆነ ይታወቅም ይላሉ ታዛቢዎቹ። ታከለ አለቃውን የማሰር አቅም እንደሌለው መቼም የታወቀ ነው ተብሏል።
እንዲያውም ይባስ ብለው ቀድመው ያሰሯቸውን እንኳን ሊፈቱ ይቅርና በተጨማሪም ትናንት ከቅዱስ ሲኖዶስ ተልከው ሀዘንተኞቹ ጋር የመጡትን ሊቃነጳጳሳት ተቀብለው ያስተናገዱ ሁለት ልጆችን ሊቃነ ጳጳሳቱ በስፍራው ደርሰው ከተመለሱ በኋላ የቦሌው ደም መጣጭ ፖሊሶች ምእመናኑን አንቀው ወደ ዘብጥያ ወስደዋቸዋልም ነው የተባለው። ልብ በሉ ቅዱስ ሲኖዶሱ ነገሩን ለማብረድ የላካቸውን ብፁዓን ሊቃነጳጳሳት ተቀብለው በማስተናገዳቸው ብቻ ነው ሁለቱን ምእመናን ያሰሯቸው።
በመጨረሻም ሞቷል ተብሎ በቤተ ክርስቲያን ዐውደ ምህረት ላይ የተነገረው ልጅ ጉዳይ ሌላ መረጃ ይዞ መጥቷል። #የዐብይታከለ መንግሥት ከዜናው በኋላ የፈለገው ብጥብጥ አልሳካና አልመጣ ሲል በቀጥታ ወደ ሆስፒታል በመሄድ ዶክተሮቹንና ነርሶቹን በመሰብሰብ የተጎጂዎቹን ፎቶ ሆስፒታል ድረስ ገብቶ አንስቶ የሄደው የባልደራሱ ሊቀመንበር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ነውና የሀሰት ዜናውን ያሰራጨውም እሱ ነው ብላችሁ የምስክርነት ቃላችሁን እንድትሰጡ ተብለው ሀኪሞቹ በግድ እንዲፈርሙ መደረጋቸውን የመረጃ ምንጮቼ ተናግረዋል።
እነ ማሞ ቂሎ ይሄ ዜና ቀድሞ በመውጣቱ አፍረው የሞኝ ድርጊታቸውን ካላቆሙ በቀር እነዚህ ሃፍረተ ቢሶች ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን በማያገባውና በማይመለከተው እርሱንም በማይመጥነው የፈጠራ ክስ ለመክሰስና ለማሰር ፖሊስ በሆስፒታል ከሚገኙ ሀኪሞችና የሆስፒታሉ ሠራተኞች ጋር ከስምምነት መድረሱን ከመረጃ ምንጮቼ ጋር ባደረግኩት የመረጃ ልውውጥ አረጋግጫለሁ። በተለይ ከመንግሥት ጋር የሚሠሩ ኦሮሞ የሆኑ የመረጃ ምንጮቼ ሊመሰገኑ ይገባል። የመንግሥቱ አካሄድ ያልጣማቸው ንጹሃን የኦሮሞ ልጆች የሚያደርሱኝም መረጃ በቀላሉ የሚታይ አይደለም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ኃይሌ ጋርመንት ጋር 9ሺ ካሬ ሜትር መሬት በጉልበት አጥረው መስጊድ ስለሠሩት የወሀቢይ እስላሞች ጉዳይ ታከለ ኡማ የተናገረውን ንግግር በቀጣይ ይዤላችሁ እቀርባለሁ። የ24 ሰፈር ልጆች ገዳይ ግን በታከለ ኡማ መንግሥት አስተዳደር እጅ ነው። የጊዜ ጉዳይ እንጂ ሁላቸውም በወንጀሉ እጃቸው ያለበት በሙሉ ተጠያቂዎች ናቸው።
_____________________________
Like this:
Like Loading...