Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • March 2023
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘መፈናቀል’

ሰልፍን የሚወድዱትን አሕዛብን በትናቸው ፥ ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 10, 2022

❖❖❖[መዝ.፷፰፥፴፬]❖❖❖

ሰማይና ምድር ባሕርም በእርስዋም የሚንቀሳቀስ ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግኑታል

እንግዲህ ምልክቶቹ በሰማዩና በዓየሩ ላይ ናቸው። ከእንግዲህ “አላየንም! አልሰማንም!” የለም።

🛑 አምና ልክ በዚህ ጊዜ ፩ሺህ የዋልድባ አባቶችን የፋሺስቱ ኦሮሞ አገዛዝ አባረራቸው፤ ዘንድሮ በፀሐይ ዙሪያ የማርያም መቀነት ታየ። አሕዛብ ወዮላችሁ! ወዮላቸው!

በዋልድባ ገዳም የሚኖሩ አባቶች ከሰማይ በማርያም መቀነት አምሳል ከሰማይ ብርሐን ሲወርድላቸው አይተው መጥተው እሙሀይን በረከት በረከትዎ ይድረስብን እናታችን ብለው እጅ ነስተዋል።

❖❖❖[የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፩፥፳፭፡፳፮]❖❖❖

በፀሐይና በጨረቃም በከዋክብትም ምልክት ይሆናል፤ በምድር ላይም አሕዛብ ከባሕሩና ከሞገዱም ድምፅ የተነሣ እያመነቱ ይጨነቃሉ፤ ሰዎችም ከፍርሃትና በዓለም የሚመጣበትን ከመጠበቅ የተነሣ ይደክማሉ፤ የሰማያት ኃይላት ይናወጣሉና።”

🛑 ባለፈው ሐሙስ / መጋቢት ፳፱/29 ፳፻፲፬ ዓ.ም ዕለት በታላቁ የቅድስት ድንግል ማርያም በዓል የደስታ ንሰት እና በአለ ወልድ/ትስብእት ባለ እግዚአብሔር ቀን በኢትዮጵያ ሰማይ ፀሐይቱ በማርያም መቀነት አክሊል ተከብባ ነበር። ከሳምንት በፊት እዚህ አውሮፓ ፀሐይዋ ላይ የሆነ ምልክት(ታች ምስሉ ላይ መኻል ፀሐይዋ ላይ እንደሚታየው) ታይቶኝ ወደ ሰማይ ሳንጋጥጥ መንገዶች፤ “ምን እየተመለከትክ ነው?” ብለው ሲጠይቁኝ ነበር። ለካስ መጭውን በኢትዮጵያ የታየውን የፀሐይ ክስተት ሊጠቁመኝ ኖሯል። ይህ በአክሱም ጽዮን ላይ ለዘመቱትና ጽዮናውያንን በረሃብ ቆልተው ለመጨረስ ለደፈሩት የምንሊክ ፬ኛ ትውልድ ከሃዲዎች ለሆኑት ለደቡባውያኑ ለኢትዮጵያ ዘ-ስጋ ትልቅ የማስጠንቀቂያ ምልክት ነው! ዋ! ብለን ነበር። በመላው ዓለም ተዓምር እየታየን ነው!

ወንጀለኞቹ የኦሮሞ፣ አማራ እና ኤርትራ ሰአራዊቶች ሆን ብለው ኦርጋኒክ የሆኑትን የጤፍ እንጀራዎች፣ ጥራጥሬዎች፣ አታክልቶችና ፍራፍሬዎች የትግራይ ሕዝብ እንዳይመገብ ነው ማሳዎችን፣ እርሻዎችን፣ የአታክልት ቦታዎችን፣ የእኅል ጎተራዎችን እንዲሁም ቤት ውስጥ ያሉ ሊጦችን ሲያቃጥሉ፣ ሲያበላሹና ሲመርዙ የነበሩት። እንስሳቱን እና ከብቶችንም ገድለዋቸዋል፣ ዘርፈዋቸዋል። እንግዲህ ይህ ሁሉ አረመኔያዊ ተግባር የትግራይን ክርስቲያን ሕዝብ ከማስራብ ዘልቆ የተረፉት በእርዳታ ለሚመጡ የተዳቀሉ/GMO ተጋላጭ እንዲሆኑና ማንም በማይመረመረው የእርዳታ ምግብ፣ መጠጥና ክትባት መንፈሳዊ ፀጋቸውንም እንዲያጡ በማሰብ ነው።ለአሚሪካ አውሎ ነፋሳት ምክኒያት ይሆናሉ የሚሏቸውን ፩ሺህ ትግርኛ ቋንቋ ተናጋሪ የጸሎት አባቶች/መነኮሳት ከዋልድባ ገዳም እንዲባረሩ የተደረጉበት አንዱ ዓላማቸው ይህ ነው፤ አዎ! አባቶች በእርዳታ ለሚመጡ የተዳቀሉ/GMO ምግቦች ተጋላጭ ሆነው ከእግዚአብሔር እንዲለዩ ለማድረግ በማሰብ ነው።

እርግጠኛ ነኝ ትዕዛዙ የመጣውም በተለይ ከአሜሪካውያኑ የፋሺስቱ ኦሮሞ አገዛዝ ሞግዚቶች ነው። በመላው ዓለም ስውርና ኃይለኛ የሆነ መንፈሳዊ ውጊያ እየተካሄደ ነውና፤ በጸሎታቸው አውሎ ነፋሳቱን/ሃሪኬኖቹን/ቶርናዶዎቹን የሚያስነሱት አባቶችን በማፈናቀልና ወደ አክሱም ወስዶ ለረሃብና ለክትባት በማጋለጥ ከመላው የትግራይ ሕዝብ ጋር በጅምላ አብሮ በመጨረስ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ ነው። መንፈሳዊ ውጊያውን አልቻሉትምና! ድራማ እየሠሩ ያሉትም ጊዜ ለመግዛት ነው።

ዋልድባ ገዳም ሺህ የዋልድባ መነኮሳትን በሑዳዴ ጾም ባበረራቸው በክርስቶስ ተቃዋሚው የፋሺስቱ ኦሮሞ አገዛዝ ላይና ድርጊቱንም በደገፈው ሁሉ ላይ ለተገፉ የሚፈርድ፣ ለተበደሉ የሚበቀል እውነተኛ ዳኛ ልዑል እግዚአብሔር ቁጣውን በቅርቡ ያወርድበታል 😠😠😠

✞✞✞[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፷፯፥፴፡፴፩]✞✞✞

በሸምበቆ ውስጥ ያሉትን አራዊት፥ በአሕዛብ ውስጥ ያሉትን የበሬዎችንና የወይፈኖችን ጉባኤ ገሥጽ፥ እንደ ብር የተፈተኑት አሕዛብ እንዳይዘጉ፤ ሰልፍን የሚወድዱትን አሕዛብን በትናቸው። መኳንንት ከግብጽ ይመጣሉ፤ ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች። እግዚአብሔር በቅዱስ ቦታው ለድሀ አደጎች አባት፥ ለባልቴቶችም ዳኛ ነው። እግዚአብሔር ብቸኞችን በቤት ያሳድራቸዋል፥ እስረኞችንም በኃይሉ ያወጣቸዋል፤ ዓመፀኞች ግን በምድረ በዳ ይኖራሉ።”

💭 በክርስቶስ ተቃዋሚ ቱርክ ድሮን የወደመው ወፍጮ የዋልድባ ገዳም ንብረት ነው | ፲፱ እናቶች ተሰውተዋል

😠😠😠 የጨለማ ዘመን ኢትዮጵያ😢😢😢

በደደቢት ከተማ፤ በጌታችን ልደት ዕለት ሃምሳ ዘጠኝ እናቶችና ሕፃናት በክርስቶስ ተቃዋሚ ቱርክ ድሮኖች ተጨፍጭፈው የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጅተዋል።

ከሁለት ቀናት በኋላ ደግሞ በማይ ጸብሪ ከተማ ግራኝ መሀመዳውያኑን የክርስቶስ ተቃዋሚዎች አጋሮቹን ጋብዞ ለዋልድባ መነኮሳት እህል ሲፈጭ የነበረውን የወፍጮ ቤት አውድሞ እናቶችን በአሰቃቂ ሁኔታ ገደላቸው። ምን ዓይነት ሰይጣናዊነት ነው፤ ጃል?! እነ ግራኝና ጭፍሮቻቸው ምን ያህል ከሃዲዎች፣ አረመኔዎችና ደፋሮች ቢሆኑ ነው!? ዓይናችን እያየ? ከፕሬዚደንት ጆ ባይደን ፈቃዱን አግኝተው ነውን? ወደ አሜሪካ የሚጓዙት አውሎ ነፋሳት መነሻቸው ይህ አካባቢ መሆንን ደርሰውበታል። ከወራት በፊትም አንድ ሺህ የሚሆኑ ጽዮናውያን አባቶችን ከዋልድባ ገዳም እንዲባረሩ ያደረገውም እርኩሱ ግራኝ አብዮት አህመድ አሊ መሆኑም ግልጽ ነው። ግራኝ በገዳማቱ ላይ ጥቃት እንደሚፈጽም፣ የኑክሌር መሳሪያ ካገኘም (ምናልባት በቅርቡ በቱርክ የሚገኙትን የአሜሪካ የኑክሌር መሣሪያዎች ኦሮሚያ በተሰኘው ሲዖል ለማስፈር ከእብዱ ኤርዶጋን ጋር ሳይስማማ አልቀረም)በአክሱም ጽዮን ላይ ምንም ሳያመነታ ሊጠቀም እንደሚችል ከሦስት ዓመታት በፊት አውስተን ነበር።

✞✞✞“ዋልድባ ሐጢአት አይሻገርብሽ እህል እንዳይበላብሽ”✞✞✞

✞✞✞ደብረ ዋሊ ወይም ዋልድባ ገዳም በ ፬ /4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አካባቢ ተመሰረተ✞✞✞

✞✞✞ ስለ ዋልድባ ገዳም ታሪክ (አቀማመጥና ስያሜ)✞✞✞

ዋልድባ ገዳም በሰሜን ጎንደር በምዕራብ ትግራይ በተከዜ ወንዝ በዛሬማ ወንዝ በእንስያ ወንዝ በወልቃይት በጠለምት በፅንብላ በስሜን ጃናሞራ በአርማጭሆ በነዚህ ቦታዎችና ወንዞች ተከቦ ተከብሮና ታጥሮ በአስደናቂ የመሬት ተፎጥራዊ አቀማመጥ ልዩ በሆነ የምድር ካርታ በወንዞች ብቻ የታጠረ ነው ዋልድባ አብረንታንት ገዳም በኢየሱስ ክርስቶስ የተገደመ ነው።

ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ ፬ /4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ከተገደሙት ገዳማት አንዱ የሆነው ይህ ገዳም፤ምድር ስትፈጠር ጌታ ባወቀ ያዘጋጀው ቅዱስ ቦታ ነው። የትንቢቱ ቃል የተነገረለት ዋልድባ ወይም ዋሊ ማለት ምን ማለት ነው? እመቤታችን ዋሊ የሚባል ገዳም ደረስን ብላ ተናገረችው በውስጡ ባለችው ዕፅ ምክንያት ሲሆን፤ ይቺ ዋሊ የተሰኝች ዕፅ በገነት የምተገኝ ናት።

የርሷም ቅጠሎች ሰፋፊና ቅርንጫፎቿ የበዙ፣ ሁል ጊዜ ጠዋት አብባ በ፱ ሰዓት የምታፈራ ዕፅ ናት። ዋሊ ዱባ የሚያክል ፍሬ በመያዟ በተለምዶ ዋሊዱባ በማለት ስትጠራ ቆይታ በኋላ ዋልድባ ለመባል በቅታለች። ዛሬም ቢሆን የቅዱሳን ምግብ ሆና የምታገለግለውን ዕፅ ከሥጋ ህፀፅ የራቀ ሁሉ በዓይነ ኅሊናው የብቃት መጽሔት ሊያያት ይችላል።

በዚች ዕፅ ስያሜ የተጠራው የዋልድባ ገዳም የቆዳ ስፋት ከምስራቅ ወደ ምዕራብ ከ፴ እስከ ፵ ኪሎሜትር ርቀት ስኖረው ከሰሜን ወደ ደቡብ ከ፹—፺ ኪሎ ሜትር ስፋት አለው። ገዳሙን እንደ ገነት ዙሪያውን በአራት አፍላጋት(ወንዞች) የተከበበ ሲሆን በምስራቅ የእንስያ፣በምእራብ የዛሬማ፣በደቡብ የማይወባ፣በሰሜን የተከዜ ወንዞች አጥር ቅጥር ሆነው ገዳሙን ይከልሉታል።አዋሳኝ ቦታዎቹም በምስራቅ የፀለምት ወረዳ፣ በምዕራብ ወልቃይት፣በደቡብ የዛሬማ ወረዳ፣በሰሜን ፅምብላ ናቸው።

በዚህ ስፋት ወስጥ እህል አይበላም፣ጠላና የመሳሰሉት መጠጣት አይፈቀድም፣የሞቀ ደመቀ አይለበስም።ይህ ገዳም ብዙ ዋሻዎች፣ፍርክታዎችና ገደላማ ስፍራዎች ያሉበት ሲሆን፤በየውኃ ምንጮችም ጭምር የጥንት የአበው ቅሪት ምልክቶች እስከ ዛሬ ድረስ ይታዩበታል።

የታተሙ ህንፃዎች፣የምድር ውስጥ ቤቶች፣የታሸጉ ዋሻዎች፣ዝጉሃን የሚኖሩባቸው ጉድጓዶችና የድንጋይ ስር ቤቶች ይገኛሉ።እልፍ አእላፈት ስውራን ይኖሩበታል።እነዚህም ለብቁአን፣ ለእረኞች ይከሰታሉ፣በአብዛኛው ደግሞ ከእይታ ውጭ በድምፅ ብቻ ጽንሐ ደውልና ይሰማል የእጣን ሽታ ይሸታል።

ቀድሞ የነበረው የሁል ጊዜ ምግባቸው፤ ለእመቤታችን ቆፍሮ የሰጣት ባለ ሶስት መቶ አስራ ስምንት ሥር ያለው ገመሎ፣ሣዳ፣ፃሌብ፣አጽግቢት ሲሆኑ፣ከቅጠላ ቅጠሎች ሓምለ አበው የተባለ፣ክረምት ብቻ የሚበቅል፣ጎመንን የሚተካ የፀጋይቶ የሚባል እጅግ መራራ ቅጠል፣ሰብኣ የሚባል ቅጠል ሌሎችም ናቸው። ፀጋይቶ ቅጠል ሁለቴና ሶስቴ ተቀቅሎ ምሬቱና መርዙ ሲቀንስ ሚበላ ነው። እስከመጨረሻው ቢቀቀል ምሬቱ አይጠፋም። ከመሬት ተቆፍሮ ከሚወጡት ውስጥ ፃብሌ የድንች መልክ የያዘ ሆኖ ለጊዜው ቀቅለው ቢበሉት ልብን ያጠፋል፣አምሮን ያናውዛል፣ለእብደት ያደርሳል።ይህ ተቆፍሮ ከወጣ በኋላ ከሳምንት ያለነሰ ጊዜ በውኃ ውስጥ እየተዘፈዘፈና እየታጠበ ተቀቅሎ ከቆየ በኋላ በፀሀይ ደርቆ በማጠራቀሚያ ጎተራ ይቀመጣል። ከዚህ በኋላ ነው ለምግብነት የሚጠቀሙበት። ከላይ የተጠቀሱት ሥራ ሥሮች ዛሬም ቢሆን በመነኮሳቱ እየተዘጋጁ ከሚበላው ቋርፍ በተጨማሪ ለመጠባበቂያ ለእለታዊ ምግብ ይጠቀማሉ።

✞ ከዱር አራዊትና እንስሳት ወገን፤

አጋዘን፣ድኩላ፣ወደምቢ፣ተኩላ፣ዘንዶ፣ጊንጥ፣ቀበሮ፣ጅብ፣ጉሬዛ፣ዝንጀሮ፣ጦጣ፣ሰስ፣ሚዳቋ፣የመሳሰሉት ሲኖሩ፤ አንበሶች(ከስውራኖቹ በስተቀር) እና ዝሆኖች፤በአድን ገዳሙን በየአመቱ ጥርግ አድርጎ በሚበላው ሰድድ እሳትና በአደን ምክንያት ተሰቅቀው በወልቃይት አደርገው ወደ መተማና ሱዳን ተሰደዋል።

✞ ከእጽዋትም ወገን፤

ሰርኪን፣ደማቅ፣እንኮይ፣የእጣን ዛፍ(መቀር)፣ሐሴን፣ሑመር፣ዋንዛ፣ሳላና፣ልዩ ልዩ አበቦች፣የሌሎችም እፅዋት ዝርያ ያለበት ገዳም ነው። በገዳሙ አንድ ክፍል በሆነው በአምርሓ ደጋ /አብርሃ ደጋ/ በተባለው ተራራማ ስፍራ ቁስቋም ማርያም ተብሎ የሚጠራ ስውር ቤተ-ክርስቲያን እንዳለ ይታወቃል።

በአሁኑ ሰአት እጅግ ብዙ ሊሒቃን ሙሁራን መናንያን መነኮሳት ያሉበት ቦታ ነው ዋልድባ እህል አይበላም በገዳሙ ቛርፍ የሚባል ከሙዝ የሚዘጋጅ ምግብ ይመገባሉ በተጨማሪም ግመሎ ሳዳ ጫብሌ ፃብሌ የሚባሉ ስራ ስሮች ከመሬት ከጫካው በመቆፈር መነኮሳቱ የሚመገቡት ምግብ ነው። ሌላ ስኳር ጨው በርበሬ ተልባ ኑግ ማር ብቻ በገዳሙ የሚፈቀዱ ናቸው ሌላ የእህል አይነት ፈፅሞ አይገባም ክልክል ነው።

ዋልድባ በዓለማችን ካሉ ገዳማት በስርአተ ገዳም በመነኮሳት ስምሪት እና በስርአተ ቤተ ክርስቲያን መሰረት የዋልድባ ገዳም ግንባር ቀደም ነው። ዋልድባ ገዳም በሶስት ታላላቅ ቦታዎች በአራት የአንድነት ማህበር ተከፍሎ የሚገኝ ብቸኛው በኢትዮጵያ የምናኔ ቦታ ነው። ዋልድባ በስሩ ብዙ ቅርጫፎች አነስተኛ ገዳማት ያሉት ሲሆን የእርሻ ቤቶች ሞፈር ቤቶች የአትክልት ቦታዎች የንብ ቤቶችና ወፍጮ ቤቶች በመባል የሚታወቁ ብዙ ቦታዎች ይገኛሉ። በአንዱ ሞፈር ቤት ከሁለት መቶ በላይ መነኮሳት ይኖሩበታል። ለምሳሌ በዶንዶሮቛ ሁለት መቶ ሐምሳ መነኮሳት በመዘጋ እጣኖ ማርያም መቶ ሰላሳ፣ በማይ ሐርገፅ መቶ ስድሳ፣ አባነፃ ሰማንያ ቤት ሙሉ በአሁኑ ማይገባ አምሳ በማይለበጣ ሁለት መቶ የሚኖሩ መናንያን አሉ።

በነዚህ ገዳማት የሚኖሩ መነኮሳት ሁሉ ተጠሪነታቸው ለዋናው አብረንታንት ነው። ዋልድባ አንድ አይነት ልብስ ነው የሚለበሰው፤ ስሙ ወይባ ይባላል። ዋልድቦች በምናኔ በመንፈሳዊ አስተዳደር ሊሒቃን ናቸው። ገዳሙ ፍፁም የመናኞች ቦታ ነው። እጅግ ፀሎተኞች ናቸው በስራም ቢሆን ዋልድቦች እጅግ አስደናቂ ተአምር ሰሪ ናቸው የዋልድባ መነኩሴ ሰውነታቸው ቀጫጭን ለፀሎት የሚተጉ አዕምሮአቸው በመንፈስ ሙጡቃን ናቸው። ዋልድባ ስርአተ ዐበው በሚባለው መፅሐፍ እንደተፃፈው “ዋልድባ ሐጢአት አይሻገርብሽ እህል እንዳይበላብሽ” የሚል ትዕዛዝ እስካሁን ገዳሙ ውስጥ እህል አይበላም እርሻም አይታረስም ያረሰ ካለ ራሱ ቀድሞ ይጠፋል።

_____________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

በጅማ አካባቢ የተዋሕዶ ልጆች እየታረዱ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 8, 2019

___________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ለገጣፎ | የግራኝ አህመድ መንግስት በመድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን የተጠለሉትን እናቶች “ከዚህም ውጡ!“ እያለ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 5, 2019

[መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳፮፥፳፬፡፳፮]

ጠላት በከንፈሩ ተስፋ ይሰጣል፥ በልቡ ግን ተንኰልን ያኖራል።

በልቡ ሰባት ርኵሰት አለበትና በቃሉ አሳምሮ ቢናገርህ አትመነው።

ጠላትነቱን በተንኰል የሚሸሽግ፥ ክፋቱ በጉባኤ መካከል ይገለጣል።”

_________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የዋቄዬ አላህ ልጆች ሥራ | በአሜሪካ የለገጣፎ ከንቲባ እህት፡ “ፕሬዚደንት ትራምፕን መፈንቀል አለብን” አለች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 1, 2019

በእነ ባራክ ሁሴን ኦባማ ከሚነሶታ ተመልምላ ወደ ዋሽንግተኑ የህዝቦች ምክር ቤት ሠርጋ እንድትገባ የተደረገቸው ሶማሊት ሙሊት/ ሙላ ኢልሃን ኦማር “በፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ላይ መፈንቅለ መንግስት ማድረግ አለብን” ትላለች። ወቸው ጉድ! ያሰኛል፤ አይደል?

አመጽ፣ መፈንቀልና ማፈናቀል ከአባታቸው ከዲያብሎስ የተማሩት ነው። መሪያቸው መሀመድም ይህን ነው የፈጸመው፤ ካሊፋቶቹ ሁሉ ይህን ነው ላለፉት ሺህ አራት መቶ አመታት እያካሄዱ ያሉት።

በአገራችን የሶማሊያዋ ሙስሊም እህት የሆነችው ሙሊት/ ሙላ ሃቢባ ሲራጅ በለገጣፎ የጀመረችው የማፈናቀልና የዘርማጣራት ዘመቻ ከዚህ አንፃር መታየት ያለበት ጂሃዳዊ ዘመቻ ነው። አይናችን እያየ ቱርክ በቅርቡ የሶሪያ ክርስቲያኖችንና ኩርዶችን በሱኒ አረብ ሙስሊሞች ባጭር ጊዜ ውስጥ ለመተካት እንደበቃችው፤ በአገራችንም የዋቄዮ አላህ አርበኞች አይናችን እያየ ተመሳሳይ ሥራ በመሥራት ላይ ናቸው። ይህ አሁን አልተጀመረም። ላለፉት ሃምሳና መቶ አመታት በረቀቀ ፕላን እየተካሄደ ያለ ዲያብሎሳዊ ተግባር ነው።

ለጣዖቱ ዋቄዮ አላህ የማይሰግዱትና እሱን የማይከተሉት በረሃብ፣ በበሽታ፣ በጦርነትና በቀይ ሽብር ሲጨፈጨፉና ቁጥራቸውም ሲመነምን፤ የዋቄዮ አላህ ተከታዮች ግን በሰላም ከአራትና አምስት ዘመዶቻቸው ልጆች እየፈለፈሉ ቁጥራቸውን በሰላም ከፍ ለማድረግ በቅተው ነበር።

አሁን በአዲስ አበባ እየተካሄደ ያለው ጽንፈኛ ተግባር በብዙ የደቡብ ኢትዮጵያ ክፍሎች ለረጅም ጊዜ ሲካሄድ የቆየ ተግባር ነው። በቅርብ እንኳን በጂማ እና ጂጂጋ በተዋሕዶ ክርስቲያኑ ላይ የተካሄደው ጥቃትና ጭፍጨፋ የሚያስተላልፈው መልዕክት፤ “ሂዱ ይህን ቦታ ለቃችሁ ውጡ” የሚለውን ነው።

ዘመቻው በዚህ አያበቃም፤ የዋቄዮ አላህ ልጆች (ሶማሌ + ኦሮሞዎች የሚባሉት) ሆን ተብሎ እርስበርስ እንዲጋጩ በማድረግ ከፈለፈሏቸው መካከል “ትርፍ ናቸው” የሚሏቸውን ልጆቻቸውን ወደ ሌላው የኢትዮጵያ ክፍል ይልካሉ። በመላው የሙስሊሙ ዓለም ሁልጊዜ የሚካሄደው ይህ ነው፤ እርስበርስ እየተባሉ፡ ተቸግረናል በማለት “ኩፋር” ወደሚሏቸው ሃገራት “ሰላምፈላጊ” ስደተኞች ይሆናሉ፤ ይህንም በድብቅ “ሂጂራ” ይሉታል። የመሀመድ የመጀመሪያው ሂጂራ ወደ ኢትዮጵያ ነበር፤ በስደተኞች መልክ “ጥገኝነት ጠይቀው” የነበሩት ተከታዮቹ የተዋሕዶ ክርስትናን ለመዋጋት የተላሉ የጂሃዳዊ ሠራዊት አርበኞች ነበሩ።

በኢትዮጵያ ዙሪያ ምን እየተካሄደ እንደሆነ እያየን ነው፤ ከኬኒያ በስተቀር፡ ሁሉም ጎረቤት የሆኑት ሃገራት ብጥብጥ ላይ ናቸው፤ ይህም ትርፍ የሆኑትን ሱዳኖችን፣ የመኖችን፣ ሶማሌዎችን እንዲሁም ሶሪያዎችን ወደ ኢትዮጵያ በማስግባት የእንግዳ ተቀባዩን ሕዝብ አንድ ቀን ቀስ በቀስ ለመተካት ያስችላቸዋል ማለት ነው። በአንድ በኩል ኢትዮጵያውያን ወደ አረብ አገር እንዲላኩና በአላህ አጋንንት እንዲሞሉ ይደረጋሉ፤ አገር ቤት ያሉት ደግሞ አዳዲስ አይጥደጋሚ ጎረቤቶችን ተቀብለው እንዲያስተናግዱ ይገደዳሉ። የዶ/ር አህመድ አመድ መንግስት ሉሲፈራውያኑ የተባበሩት መንግስታት ባለሥልጣናት ያጨበጨቡለትን አዲስ የስደተኞች ህግ ለማርቀቅ የበቃው ከዚህ አንፃር ነው።

ሕዝባችንን አደንዝዘውታል፤ ወገን ተኝቷል፤ እግዚአብሔር ግን ዝም አላለም፤ አንቂ የሆኑ ምልክቶችን እያሳይንና መልዕክቶችንም እያስተላለፈልን ነው። የእርሱን እና የእኛን የልጆቹን ጠላቶች አፍ በመክፈት ላይ ነው፤ ሆን ተብሎ ሥልጣኑን እንዲረከቡ የተደረጉት የአውሬው ፍዬል ልጆች ባልጠበቁት መልክ እራሳቸውን እያጋለጡና እያዋረዱ ነው፤ የሚነሶታዋ ሶማሊት በአሜሪካ፤ እንዲሁም ዶ/ር አህመድ አመድ እና ለማ ገገማ በኢትዮጵያ ሰሞኑን እየቀባጠሩ ነው፤ ገና ብዙ ይቀባጣጥራሉ….ጥሩ ነው

ሁሉም የኢትዮጵያና የእግዚአብሔር አምልክ ጠላቶች ናቸውና፤ አሁን ቀየር በማለት በለሰለሰ ምላሳችሁ ደግመው እንዳያታልሏችሁ ተጠንቀቁ፡ ወገኖቼ!

እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን!

[መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳፮፳፬፡፳፮]

ጠላት በከንፈሩ ተስፋ ይሰጣል፥ በልቡ ግን ተንኰልን ያኖራል።

በልቡ ሰባት ርኵሰት አለበትና በቃሉ አሳምሮ ቢናገርህ አትመነው።

ጠላትነቱን በተንኰል የሚሸሽግ፥ ክፋቱ በጉባኤ መካከል ይገለጣል።”

[ወደ ሮሜ ሰዎች ምዕራፍ ፲፮፥፲፰]

እንዲህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና፥ በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ልብ ያታልላሉ።”

__________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የለገጣፎ እንባ | ግብጽ እና ሳውዲ አረቢያ በመጪዎቹ ወራት ታይቶ የማይታወቅ የአንበጣ መቅሰፍት ይመጣባቸዋል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 24, 2019

የአንበጦቹ መነሻም ከኢትዮጵያ(ኤርትራ)እና ሱዳን ነው

የግራኝ አህመድና ዋቄዮ አላህ ልጆች ሞግዚቶች ሳውዲ አረቢያ፣ ግብጽ፣ ኤሚራቶች፣ ቱርክ፣ አሜሪካ እና አውሮፓ ናቸው። ሁሉም የአውሬው ፍየል አገሮች ናቸው፤ ወዮላቸው! ንፍጣቸውን እንኳን ያልጠረጉ ውርንጭላዎች በአገራችን ላይ ሲሳለቁና ሲሳሳቁ የእኛ ደካማ ትውልድ በዝምታ ማለፉን ቢመርጥና በከንቱ የእባቡን ጅራት ለመያዝ ቢደክምም፤ እግዚአብሔር ግን ዝም አይልም፤ አይዘገይም፤ የእባቡን እራስ ነው የሚቀጠቅጠው።

አንዳንዴ እንዲያውም የጣናው እንቦጭ መብቀል እና በአንዳንድ ገዳማቱ ቅዳሴ ማቆም ምናልባት እግዚአብሔር ግብጽን ለመቅጣት ያዘጋጀው ቅድመ ሁኔታ ሊሆን ይችላል የሚል ሃሳብ አለኝ። እስራኤላውያን ግብጽን ለቀው ከወጡበት ዘመን አንስቶ የአባይን ውሃ በመባረክ ላይ ያተኮረው የአባቶቻችን የፀሎት ሥራ የጠቀመው የእግዚአብሔር እና የኢትዮጵያ ጠላት የሆኑትን ግብጻውያን ብቻ ነውና። እግዚአብሔር ለአባቶቻችን “ሂዱ! ግብጽ አይገባትም!“ እያለን ይሆን?

በጊዜው ፈርዖን የዓለም ተፈሪ ንጉሥ ነበር፡፡ ግብጽ የዚያኛው ዘመን ልዕለ ኃያል አገር ነበረች፡፡ ይህን ትልቅ አገዛዝ እግዚአብሔር በቅማልና በአንበጣ ነበር ያንበረከከው።

 

_________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

ለገጣፎ ፭ኛ ቀን | „ከዚህ በፊት እርዳታ ያደረግንላቸው ተፈናቃይ ሶማሌዎች መጥረቢያና ገጀራ ይዘው መጡብን”

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 24, 2019

ያረፉትን ወገኖቻችንን ነፍስ እግዚአብሔር በአፀደ ገነት ያሳርፍላቸው!

ጅማ፣ ጅጅጋ፣ አምቦ….

ወገኖቼ፡ ምን እየተሠራ እንደሆነ እያየንና እየሰማን ነው?

ላለፉት ሰላሳ ዓመታት ሦስት መቶ ሺህ ሶማሌዎች አዲስ አበባ መጥተው እንዲሠፍሩና ቦሌ ቅዱስ ሚካኤል የመሳሰሉት አካባቢዎችን እንዲወሩ መደረጋቸው ለዚህና ለመጭው ወቅት ጂሃድ መዘጋጀታቸው ነው።

ወጣት እና ጤናማ የሆነው የሕዝባችን ቁጥር ማደግ እጅግ በጣም ያሳሰባቸው የሉሲፈራውያኑ ተባበሩት መንግሥታት፣ የአውሮፓው ህብረት፣ አለም ባንክ እና ወዘተ ሴራ። ባገራችን ታይቶ የማይታወቅ መዓት ይመጣል።

ባካባቢያችን ያሉት መሀመዳውያን ሃገራት ሁሉ (ሶማሊያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ የመን፣ በቅርቡ ሳውዲ አረቢያ) እርስበርስ እየተባሉ ነው፤ ይህም ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ነው፤ ልክ ሶሪያ፣ ኢራቅ እና አፍጋኒስታን በጦርነት ታምሰው ዜጎቻቸው አውሮፓን እንዲወሩ እንደተደረገው፤ ያካባቢያችንም ሃገራት ዜጎቻቸውን በዚህ መልክ ወደ ኢትዮጵያ በመላክ ሕዝበ ክርስቲያኑን ለመተካት ይሻሉ። እቅዱ ይህ ነው።

የክርስቶስ ተቃዋሚዋ ቱርክ ሰሜን ሶሪያ በገባች አመት ባለሞላ ጊዜ ውስጥ እንደ ጠላት የምታያቸውን የሶሪያ ክርስቲያኖች እና ኩርዶች አፍሪን ከሚባለው አካባቢ አፈናቅላ በምትካቸው የሱኒ እስላም ተከታይ አረቦችን በብዛት አስፍራለች፤ በዚህ ጉዳይ አለም ጸጥ ብሏል። በለገጣፎ፣ በፉሪ፣ በላፍቶ፣ በአለም ባንክ፣ በቡራዮና በሌሎችም አካባቢዎች እየተካሄደ ያለው ጽንፈኛ ዘመቻም ቱርኮችና አረቦች ከሚሠሩት ዘመቻ ጋር የተያያዘ ነው።

_________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ጂሃድ በ ለገጣፎ | ቤተክርስቲያን ያፈረሰችው ሙስሊሟ ከንቲባ፡ “ታቦት የሚሉት እስቲ ኃይል ካለው ለምን አያድናቸውም?!”

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 24, 2019

ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ከሚፈርስ የኔ ቤት ለምን አልፈረሰም ብዬ አልቅሻለሁ

የለገጣፎ ጉዳዩ ከዓመት በፊት ነበር የጀመረው

መጀመሪያ ቤተክርስቲያናቸውን (መንፈሳዊ ሕይወታቸውን) ከዚያ መኖሪያ ቤቶቻቸውን (ሥጋዊ ሕይወታቸውን) ማወክ፣ መዋጋትና ማጥፋት

ይህ ለአንድ ሺህ አራት መቶ ዓመታት ያህል በመላው ዓለም የሚታይ የእስልምና ጂሃዳዊ አካሄድ ነው። በዘመነ ግራኝ አህመድ ተከስቷል፤ በዳግማዊ ግራኝ አህመድ ዘመንም በመከስተ ላይ ይገኛል።

ከሁለት ዓመት በፊት፡ ሰኔ ፴/ ፪ሺ፱ ዓ.በአንዲት እርኩስ ሙስሊም ከንቲባ የሚመራ ጂሃዳዊ ሠራዊት አላህ ወአክበር እያለገጣፎ የሚገኘውን የመጥምቀ መለኰት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያንን ሙሉ በሙሉ አፈራረሰው።

ሙስሊሟ ከንቲባ ጫልቱ ሰይና አህመድ ራሷ ቆማ ነበር ያስፈረሰችው። በቦታው የነበሩ ታዛቢዎች የከንቲባዋ ደስታ ወደር እንዳልነበረው ገልጸዋል።

በትክክለኞቹ የቁርአን ሙስሊሞች ዘንድ ቤተክርስቲያን ማፍረስና ክርስቲያኖችን መግደል እንደ ጂሃዳዊ ግዴታ ብቻ ሳይሆን፤ ትልቅ ሽልማት የሚያስገኝና “ጀነት” የሚያስገባ ተግባርም ነው።

ሰኔ ፳፱/፪ሺ፱ ዓም ፦ በማግስቱ ዓርብ ሰኔ ፴ ለሚከበረው የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ክብረ በዓል ካህናቱ የዋዜማውን ጸሎት አድርሰው በዓውደምህረቱም ላይ የሰርክ ጉባኤው በሚያምር መልኩ ተካሂዶ ካህናቱም ጥቂት አረፍ ብለው ለማኅሌቱ አገልግሎት ለመዘጋጀት ፣ ምእመናንም ለበዓሉ ዝግጅት ወደየማረፊያቸው ይሄዳሉ ።

ከምሽቱ ፪ ሰዓት ሲሆን ግን አስደንጋጭ ነገር በስፍራው ተከሰተ። በሙስሊሟ ከንቲባ የሚመራና ከሰንዳፋ ከተማ የመጡ ናቸው የተባሉ የወታደር ቁመና ያላቸውና በሲቢል እንዲንቀሳቀሱ የተደረጉ ማንታቸው የማይታወቅ ጎሮምሶች በወታደር ታጅበው ከስፍራው ይደርሳሉ። በቤተክርስቲያኑም ውስጥ ያገኙት የቤተክርስቲያኒቱን አስተዳዳሪና ቀሳውስቱን በመያዝ ወደ ዘብጥያ ያወርዷቸውና አፍራሽ ግብረ ኃይል የተባሉት መጤዎችና ፀጉረ ልውጦች አሏህ ወአክበር እያሉ እስከ ምሽቱ ፬ ሰዓት ድረስ ቤተክርስቲያኒቱን ማፍራሳቸው ነው የተነገረው ። የከንቲባዋ ደስታ ግን ይህ ነው ተብሎ አይገለፅምም ተብሏል ።

ከዚያ በመቀጠል ሰኔ ፴ የመጥምቁን በዓል ለማክበር የሚመጣው ህዝብ በአካባቢው ድርሽ እንዳይል ከጎዳናው ጀምሮ የፌደራልና የኦሮሚያ አርማን ያጠለቀ የወታደር ዓይነትና የመከላከያ ሠራዊቱም አንድ ላይ በመሆን በባጃጅ ፣ በእግር ሀገር ሰላም ብለው ወደ ቤተክርስቲያን የሚሄዱትን በሙሉ እየቀጠቀጡ መልሰዋል ተብሏል።

ሐምሌ ፬ /፪ሺ፱ ዓም ከቀኑ ፬ ሰዓት ሲሆን ደግሞ የለገጣፎዋ ከተማ ከንቲባ የሆነችውና ይኽችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮችን ክፉኛ ትጠላለች የምትባለው አክራሪ ሙስሊም ከንቲባ ወይዘሮ ጫሉት አህመድ በእርሷ የሚመራ የከተማውን አስተዳደር ሠራተኞች አስከትላ በመምጣት ለምልክት እንዳይገኝ አድርጋ በድጋሚ በግሬደር አስፈርሳዋለች።

የሚገርመው ነገር ቤተክርስቲያኑ ለማስተር ፕላኑ ውበት በማይሰጥ ቦታ ነው ያለው በሚል ተልካሻ ምክንያት የለገጣፎ መዘጋጃ ቤት ሠራተኞችን እና የዚያው ከተማ አፍራሽ ግብረ ኃይሎችን ይዛ በመምጣት ለማፍረስ ባደረገችው ሙከራ በሁኔታው ግራ የተጋቡት የመዘጋጃ ቤቱ ሠራተኞችና አፍራሽግብረ ኃይሎቹ ፤ የከንቲባዋን ድርጊት በመቃወም እኛ በፍፁም እንዲህ አይነት ተልካሻ ድርጊት ላይ አንሳተፍም በማለት አልታዘዝ ቢሏትም ከንቲባዋ በኃይልና በቁጣ በማስፈራራትና በዛቻ ለማስገደድ ብትሞክርም ሰሚ ታጣለች ። በሁኔታው የተናደደችው ወጠጤዋ ከንቲባዋ ስልኳን በማውጣት አለቃዋ ለሆነና ትእዛዝ እየሰጣት ነው ለሚባል አካል በተደጋጋሚ ትደውላለች ። በመጨረሻም የአካባቢው ወጣቶች በማፍረሱ ሥራ ላይ አልተባበር ማለታቸው ሲረጋገጥ ወደ ሰንዳፋ በመሄድ ማንነታቸው ያልታወቀና ሲቪል ልብስ እንዲለብሱ የተደረጉ ወታደሮችን በማምጣት ቤተክርስቲያኒቱን አፍርሳለች ።

አስቀድሞ የጦር ሠራዊቱ አነጣጣሪ ተኳሽ ይዞ በስፍራው እንዲፈስ በመደረጉ ምክንያት ህዝቡ ወደ ቤተክርስቲያኑ ለማለፍ አልቻለም ነበር። በሁኔታው የተናደዱ የሚመስሉ ወታደሮች ከንቲባዋን በመለመን ካግባቧት በኋላ ካህናት መጥተው ታቦቱን ይዘው ወደ መዘጋጃ ቤት እንዲወስዱት አስደርገው ነበር። ሌሎች ንዋያተ ቅዱሳቶችም በአፍራሽ ግብረ ኃይሉ እንዲወድሙ ከተደረገ በኋላ ንዋያተ ቅዱሳቱም ልክ እንደ ታቦተ ህጉ ወደ መዘጋጃ ቤቱ ተወስደዋል።

ቤተክርስቲያኑ ሙሉ በሙሉ እንዲወድም የተደረገ ሲሆን ፤ አገልጋይ ካህናቱ ከእነ የህግ ባለሙያቸው በሙሉ ወደ ዘብጥያ ወርደዋል። ታቦተ ህጉ በመዘጋጃ ቤቱ በሚገኝ ኮንቴነር ውስጥ እንዲቀመጥ የተደረገ ሲሆን ንዋያተ ቅዱሳቱም በመዘጋጃ ቤቱ መጸዳጃ ቤት አጠገብ ዝናብና በረዶ ፣ ፀሐይና ነፋስ እየተፈራረቁባቸው እንዲቀመጡ ተደርገው እጅግ በሚያስለቅስ ሁኔታ እንዲቀመጥ ተደርገዋል ተብሏል ። ከሁሉም በላይ ሕዝበ ክርስቲያኑን እያስለቀሰና በቁጭት እያንገበገበ የሚገኘው የከንቲባዋ ታቦት የሚሉት እስቲ ኃይል ካለው ለምን አያድናቸውም?!” የሚለው መርዛማ ንግግሯ ነበር

[መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕራፍ ፭፥ ፩፡፲፪]

ፍልስጥኤማውያንም የእግዚአብሔርን ታቦት ወሰዱ፤ ከአቤንኤዘርም ወደ አዛጦን ይዘውት መጡ።

ፍልስጥኤማውያንም የእግዚአብሔርን ታቦት ወስደው ወደ ዳጎን ቤት አገቡት፥ በዳጎንም አጠገብ አኖሩት።

በነጋውም የአዛጦን ሰዎች ማለዱ፥ እነሆም፥ ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በምድር ላይ በግምባሩ ወድቆ ነበር፤ ዳጎንንም አንሥተው ወደ ስፍራው መለሱት።

በነጋውም ማለዱ፥ እነሆም፥ ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በምድር ላይ በግምባሩ ወድቆ ነበር፤ የዳጎንም ራስ እጆቹም ተቈርጠው በመድረኩ ላይ ወድቀው ነበር፤ የዳጎንም ደረት ብቻውን ቀርቶ ነበር።

ስለዚህም የዳጎን ካህናት ወደ ዳጎንም ቤት የሚገቡት ሁሉ በአዛጦን ያለውን የዳጎንን መድረክ እስከ ዛሬ ድረስ አይረግጡም።

የእግዚአብሔርም እጅ በአዛጦን ሰዎች ላይ ከበደች፥ አጠፋቸውም፥ አዛጦንንና ድንበራቸውንም በእባጭ መታቸው።

የአዛጦንም ሰዎች እንዲህ እንደ ሆነ ባዩ ጊዜ። እጁ በእኛና በአምላካችን በዳጎን ላይ ጠንክራለችና የእስራኤል አምላክ ታቦት ከእኛ ዘንድ አይቀመጥ አሉ።

ልከውም የፍልስጥኤማውያንን አለቆች ሁሉ ወደ እነርሱ ሰበሰቡና። በእስራኤል አምላክ ታቦት ምን እናድርግ? አሉ፤ እነርሱም። የእስራኤል አምላክ ታቦት ወደ ጌት ይዙር ብለው መለሱ። የእስራኤልንም አምላክ ታቦት ወደዚያ ተሸከሙት።

ከተሸከሙትም በኋላ የእግዚአብሔር እጅ በታላቅ ድንጋጤ በከተማይቱ ላይ ሆነች፤ ከታናሹም እስከ ታላቁ ድረስ የከተማይቱን ሰዎች መታ፥ እባጭም መጣባቸው።

የእግዚአብሔርንም ታቦት ወደ አስቀሎና ሰደዱት። የእግዚአብሔር ታቦት ወደ አስቀሎና በመጣ ጊዜ አስቀሎናውያን። እኛንና ሕዝባችንን ሊገድሉ የእስራኤልን አምላክ ታቦት አመጡብን ብለው ጮኹ።

በከተማይቱ ሁሉ የሞት ድንጋጤ ነበርና፥ የእግዚአብሔርም እጅ በዚያ እጅግ ከብዳ ነበረችና ልከው የፍልስጥኤማውያንን አለቆች ሁሉ ሰብስበው። የእስራኤልን አምላክ ታቦት ስደዱ፥ እኛንና ሕዝባችንን እንዳይገድል ወደ ስፍራው ይመለስ አሉ።

ያልሞቱትም ሰዎች በእባጭ ተመቱ፤ የከተማይቱም ዋይታ እስከ ሰማይ ወጣ

_________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ወያኔ ፳፯ አመት ከሠራው ጥፋት ዶ/ር አብይ አህመድ ፩ አመት ሳይሞላው የሠራው ወንጀል ይበልጣል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 23, 2019

ወገኖቼ፤ በአገራችን ጂሃዱ በገሃድ እየተጧጧፈ ነው

ከዚህ ቀደም “አሊ” የተባለውን መሀመዳዊ የአዲስ አበባ ከንቲባ እንዲሆን በማድረግ ባጭር ጊዜ ውስጥ ስንት ጥፋት ሊያደርስ እንደበቃ እናስታውሳለን፤ ግን ከዚህ ትልቅ ስህተት አሁንም አልተማርንም። አየን አይደል፡ ሆን ተብሎ ከአምቦ የመጣው ውርንጭላ የአዲስ አበባ ከንቲባ ምን እየሠራ እንደሆነ?! አየን አይደል ቀይ ምንጣፍ የለበሰችውና የአረብ ወኪል የሆነችው የለገጣፎ አስተዳደር “ከብቲባ” ሸኻ ሀቢባ ሲራጅ በለገጣፎ ወገኖች ላይ እየፈጸመች ያለችውን ጭካኔ? “ሴትየዋ” እንደ ሴት ርህራሄ እንኳን አይታይባትም?!

ወገኖቼ፡ ግራኝ አህመድ የዶክተርነት ማዕረግ ይዞ እንደገና መጥቷል፤ እግዚአብሔር ስራውን በፍጥነት እያጋለጠው ነውና በፍጥነት ልንነቃ ይገባናል።

እስኪ የዶ/ር ግራኝ አህመድን እና ከሃዲ “ኢትዮጵያውያንን” የ፱ ወር ወንጀል አብረን እንመልከት፦

  • + የኢትዮጵያ ጠላቶች አዲስ አበባ መግባት

  • + የአዲስ አበባ፡ ኢትዮጵያን በከዱ የዋቄዬ አላህ ልጆች መወረር

  • + ጠላት የሆኑ ፈረንጆች እና አረቦች ኢትዮጵያ እንዲገቡ መደረግ

  • + ለአንድ ኢትዮጵያውያን (ኤርትራ) ትውልድ መጥፋት ተጠያቂ የሆነው ኢሳያስ

አፈወርቂ አዲስ አበባ መሄድ

  • + ለአንድ ኢትዮጵያውያን ትውልድ መጥፋት ተጠያቂ የሆነው መንግስቱ ኃይለ ማርያም በቀድሞው ጠቅላይ ሚንስት ኃይለ ማርያም ደሳለኝ መጎብኘት

  • + ጠላት ለሆኑ ለእስላም እና ጴንጤ ወራሪዎች የአገራችንን በር መክፈት

  • + በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ኢትዮጵያውያን እና አፍሪቃውያን

ከፈረንጆች እየተለዩ ለብቻቸው እንዲፈተሹ ማዘዝና መቅጣት

  • + በአምቦ እና አካባቢዋ የክርስቲያን ህፃናት መበረዝ

  • + ከአምቦ የመጡ የመንደር ፖለቲከኞች አዲስ አበባን እንዲመሩ ማድረግ

  • + የአረብ ድንኳን የለበሱ ሴቶችን ቁልፍ ቁልፍ ቦታ ላይ ማስቀመጥ

  • + ሴቶቻችን በክትባት መልክ መኻን እንዲሆኑ መሥራት

  • + እህቶቻችንን ለአረቦች በባርነት መልክ መሸጥ

  • + ታላላቅ ተቋማትና ፕሮጀክቶች ለምዕራቡና አረቡ ነጣቂዎች እንዲሸጡ መደረግ

  • + የባህል ምግቦቻችንን በማስወደድ ሕዝባችን በተመረዘ ፒዛና በርገር መመገብ

  • + የጅጅጋ አባቶች እልቂት ዓብያተክርስቲያናት ቃጠሎ

  • + የኢንጂነር ስመኘው መገደል

  • + የእኅተ ማርያም ባለቤት እና የሌሎች ኢትዮጵያውን ግለሰቦች መገደል

  • + የህዳሴውን ግድብ ለግብጽ መሰጠት

  • + በሚሊየን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን መፈናቀል

  • + የአዲስ አበባ ልጆች መታሠርና መገደል

  • + የአዲስ አበባን ነዋሪዎች መተናኮል

  • + የለገጣፎ ጭካኔ የተሞላበት ማህበረሰባዊ ሙከራ / ኤክስፔሪሜንት

የረሳሁት ነገር አለ?

ለመሆኑ አሁን “እንዴት ደፈሩ? ማንስ ይህን ያህል አደፋፈራቸው?“ ብለን ብንጠይቅ

መልሱ፦ ሉሲፈራውያኑ አረቦች እና ምዕራባውያን

አቤት ቅሌት! አቤት ድፍረት! አዬ ጉዳችሁ እናንት የ666 ቅጥረኞች፤ የኢትዮጵያን እና ልጆቿን ትዕግስት ታጠናላችሁ፤ እግዚአብሔር አምላካቸውንም ትፈታተናላችሁ፡ አይደል? የህፃናቱ ዋይታ፤ የአረጋውያኑ ለቅሶ ለከንቱ ይመስላችኋልንየፈለጋችሁትና ያቀዳችሁለት ይህን ነው፤ ለምን ያህል ጊዜ ጮቤ ትረግጡበት ይሆን? ዝምታው ድክመት ይመስላችኋልን? ግድየለም! አይዟችሁ አትፍሩ! እኛ በቀልን ለኔ ተዉልኝ!” ላለን አምላካችን ትተናችኋል፤ ሃገረ እግዚአብሔር የሆነችውን ኢትዮጵያን አታጠፏትም፤ እናንተ ግን ለዘላለም ትጠፋላችሁ፤ ከሃዲዎች!

ለገጣፎ” ከ አሰፋ በላይ

መክት ወገኔ

ጠዋት አራት ኪሎ ማታ ለገጣፎ፣

ሜዳ ላይ አሰጣው ነባሩን ዘርግፎ፣

አፈናቃይ ሆነ ኦፒዲ ፀንፎ።

የአራት ልጆች እናት መግቢያ ጠፍቶባታል፣

መክት ወገኔ ሆይ በአንተም ላይ ይደርሳል።

የዘመኑ ዘራፊዎች ከንቲባ ፣

ይባላሉ ታከለና ሃቢባ፣

ኦነግ ምንጥስዬ ኦዴፓ።

ወራሪ ገብቶ በሀገር፣

ተሰቃየ ኑዋሪ በችግር።

እህል ሲጠፋ ጨው ሲሆን፣

ጠመንዠ ነው ነፍስ አድን፣

መክት ወገኔ አሁኑን።

አቤቱታ ለማሰማት ቀርበን፣

አፈናቅለው አፍርሰው ቤታችንን ፣

መጋላ ኬኛ አሉን።

ወራሪ መሬትክን ዘርፎህ፣

ከአገር ከቀዬህ ተሰደህ፣

ምኑን አለኝታ አገኘህ ።

መክት ወገኔ ለነፍስህ፣

ጠላት ሞጋሳ መጣብህ።

የእናታችን የቅድስት ኪዳነ ምህረት እረድኤት በረከቷ ምልጃ ፀሎቷ በሁላችንም ይደርብን ሀብተ ስጋን ሀብተ ነፍስ በምልጃዋ በፀሎቷ ታሰጠን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እናቱ ስለቅድስት ድንግል ማርያም ብሎ በሰጣት ቃልኪዳን ፀሎት ልመናችንን ይስማ ምሀራነውና በምህረቱ ለዘለዓለም ይጎብኘን!!! አሜን! አሜን! አሜን!

__________

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: