Posts Tagged ‘መስከረም ፪ሺ፲፪ ዓ.ም’
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 14, 2020
ጊዜው የሚያዘናጋ፣ የሚያዘልል፣ የሚያስፈነጭ የሚያስጨበጭብ ጊዜ አይደለም ፥ ለፀሎት የምንነቃበት ጊዜ እንጂ: ሕዝብ ሲያምጽ፣ ኃጢዓት ሲበዛ፣ ጽዋ ሲሞላ እምቢ ለሚል እግዚአብሔርን ለሚገዳደር በተናጠል ይቀጣል
[መጽሐፈ መክብብ ምዕራፍ ፫፥፩፡፰]
“ለሁሉም ነገር ጊዜ አለው፤ ከሰማይ በታች ለሚከናወነው ለማንኛውም ነገር ወቅት አለው፤ ለመወለድ ጊዜ አለው፤ ለመሞትም ጊዜ አለው፤ ለመትከል ጊዜ አለው፤ ለመንቀልም ጊዜ አለው፤ ለመግደል ጊዜ አለው፤ ለማዳንም ጊዜ አለው፤ ለማፍረስ ጊዜ አለው፤ ለመገንባትም ጊዜ አለው፤ ለማልቀስ ጊዜ አለው፤ ለመሣቅም ጊዜ አለው፤ ለሐዘን ጊዜ አለው፤ ለጭፈራም ጊዜ አለው፤ ድንጋይ ለመጣል ጊዜ አለው፤ ድንጋይ ለመሰብሰብም ጊዜ አለው፤ ለመተቃቀፍ ጊዜ አለው፤ ለመለያየትም ጊዜ አለው፤ ለመፈለግ ጊዜ አለው፤ ለመተው ጊዜ አለው፤ ለማስቀመጥ ጊዜ አለው፤ አውጥቶ ለመጣልም ጊዜ አለው፤ ለመቅደድ ጊዜ አለው፤ ለመስፋትም ጊዜ አለው፤ ለዝምታ ጊዜ አለው፤ ለመናገርም ጊዜ አለው፤ ለመውደድ ጊዜ አለው፤ ለመጥላትም ጊዜ አለው፤ ለጦርነት ጊዜ አለው፤ ለሰላምም ጊዜ አለው።“
የሰይፈ ሥላሴ ፀሎት ከክፉ ነገር ሁሉ ይጠብቀን!
_______________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: መስከረም ፪ሺ፲፪ ዓ.ም, መንፈሳዊ ውጊያ, ስላሴ, ቅድስት ሥላሴ, ቅድስት ቤተክርስቲያን, ቅድስት ድንግል ማርያም, ትምህርት, ኃጢአት, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን, ኢየሱስ ክርስቶስ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሐዶ እምነት, ፀሎት, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 21, 2020
እኛ እግዚአብሔር አምላካችንን እንዲህ ስለምነወድደው ከዚህ የተነሳ ሰይጣን በቅናት፣ በጥላቻ እና በእብደት ይሞላል። ዲያብሎስ ሁሉም እግዚአብሔርን የሚወዱትንና የሚያገለግሉትን ፍጥረታት መግደል እና ማጥፋት ይፈልጋል።
ያው እንግዲህ ዲያብሎስ በሸቀ፣ አበደ፣ ቅጥል አለ። ዲያብሎስ ሰይጣን ወደ እኛ የማለፍ ፈቃድ ካገኘ ይሰርቃል፣ ይገድላል እንዲሁም ያጠፋል። መስረቅ፣ መግደል እና ማጥፋት የእርሱ የደመ ነፍስ ስራዎች ናቸውና እግዚአብሔርን የሚወዱትን ለመግደል ወደ ሐረርና ድሬዳዋ አመራ።
_________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: ሐዋሳ, መስከረም ፪ሺ፲፪ ዓ.ም, መንፈሳዊ ውጊያ, ቀስተ ደመና, ቅድስት ሥላሴ, ቅድስት ቤተክርስቲያን, ኢትዮጵያ, ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን, ኢየሱስ ክርስቶስ, የማርያም መቀነት, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሐዶ እምነት, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 16, 2020
እንኳን ለአግዓዚተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን። የአብርሃሙ ሥላሴ ሀገራችንን ኢትዮጵያን ይጠብቅልን። ሕዝባችንንም በሰላም በፍቅር በአንድነት ያኑርልን።
ወደ መጨረሻ ላይ ያለውን መልዕክት እናዳምጥና እራሳችንን እንጠይቅ፤ “እንደው በዚህች ዓለም ላይ እንደ ኢትዮጵያ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ወደ ቤተክርስቲያን አዘውትሮ የሚሄድ፣ በጾምና በጸሎት የሚተገባ ሕዝብ ይኖራልን? እኔ መመስከር እችላለሁ፤ የለም! የትም ሃገር የለም። ሃጢአተኞች ሁላችንም ሃጢአተኞች ነን፤ ነገር ግን ቤተክርስቲያን እየተቃጠለ ያለው እኛ ከዓለም ሁሉ የከፋ ሃጢአት ሰርተን ሳይሆን ክርስቲያን ወገናችንን እና ቤተክርስቲያናቱን ለመከላከል ዝግጁ ባለመሆናቻን፣ የእኛና የአምላካችን ጠላት ከሆኑት አህዛብ ጋር በመደባለቃችን፣ የሃገር ጠላት ከሆነው መንግስት ጋር በመደመራችን ብሎም እንደ ቀደሙት አባቶቻችን መንግስትን በቁጣ ለመገሰጽና ለማስጠንቀቅ ባለመድፈራችንና በራድ ወይ ትኩስ ስላልሆንን ነው። ስለዚህ መንግስትን ለመቃወም “ሰልፍ አትውጡ፡ እኛ እንደራደራለን!” ቅብርጥሴ የሚለው መልዕክት የትም አያደርሰንም። እንዲያውም የተዋሕዶ አርበኞች በቁጣ ወደ አራት ኪሎ ቤተመንግስት አምርተው ባለሥልጣናቱ ሁሉ እንዲወገዱ መጮኽና አጥሩን መነቅነቅ ይኖርባቸዋል። ለሁሉም ጊዜ አለው፤
“ከወዳጆችህ ጋር ብቻ ሳይሆን ከጠላቶችህም ጋር እንኳ ሳይቀር በሰላም ኑር፤ ነገር ግን እንዲህ የምልህ ካንተ ከግል ጠላቶችህ ጋር እንጂ ከእግዚአብሔርና ከቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ጋር አይደለም፡፡”አንድ ገዳማዊ አባት
“ሰውን ከእግዚአብሔር ከሚለየው አጉል ሰላም ይልቅ ከእግዚአብሔር የማይለየው ጦርነት ይሻላል፤ ስሜታዊ ከሆነና ለቤተ ክርስቲያን ዘለቄታዊ ጉዳት ከሚኖረው ስምምነትና አንድነት ይልቅ ስለ ሐይማኖት መጠበቅ ዘለቄታዊ ጠቀሜታ የሚኖረውና ለዚህ ሲባል የሚሆን አለመስማማት ይሻላል፡፡” ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ
በዚህ የጥምቀት በዓል ከአባቶች የምጠብቀው መልዕክት፦
“ሴት ልጆቼ በደምቢዶሎ ጫካ ውስጥ የጥምቀት በዓልን እንዲያሳልፉ አልሻም፤ ስለዚህ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ በቃህ፡ ስልጣኑን አስረክብና በሥላሴ ስም ተጠመቅ!”
የሚለውን መልዕክት ነው።
እስኪ እናስበው፤ አቡነ ማትያስ ይህን ቢናገሩ፤ ምንም ጥርጥር የለኝም ብዙ እንቅስቃሴ ሊታይ ይችል ነበር።
የቤተክርስቲያን አገልጋዮች፡ በቃን! “ስሜታዊ አትሁኑ!” እያላችሁ ሰውን አታስተኙት፤ ወኔውን አትንጠቁት! እንዲያውም “ምርጫ” የተባለው ነገር የሚካሄድ ከሆነ በመጭዎቹ ሳምንታት ምእመናኑን ለእነ አብዮት አህመድ፣ ለእነ ብርሃኑና ስብሐት ነጋ፣ እንዲሁም ለሌሎቹ አቋም–የለሽ ልክስክስ ፓርቲዎች በጭራሽ ድምጽ እንዳይሰጡ ማስጠንቀቅ፤ በተቃራኒው ደግሞ ለእስክንድር ነጋ ድጋፋቸውን እንዲሰጡ ግልጽ የሆነ ቅስቀሳ ማካሄድ አለባቸው።
ሜዲያው ሁሉ በኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ላይ አሉታዊ በሆነ መልክ 24 ሰዓት ቅስቀሳ በሚያደርጉባት ሃገራችን ለሕዝበ ክርስቲያኑ በጣም አመች የሆነው የቅስቀሳ እና የትምህርት መድረክ በቤተክርስቲያን ነው የሚገኘው።
_________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: መስከረም ፪ሺ፲፪ ዓ.ም, መንፈሳዊ ውጊያ, ስላሴ, ቅድስት ሥላሴ, ቅድስት ቤተክርስቲያን, ትምህርት, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን, ኢየሱስ ክርስቶስ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሐዶ እምነት, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 17, 2019
[መጽሐፈ መክብብ ምዕራፍ ፫፥፩፡፰]
“ለሁሉም ነገር ጊዜ አለው፤ ከሰማይ በታች ለሚከናወነው ለማንኛውም ነገር ወቅት አለው፤ ለመወለድ ጊዜ አለው፤ ለመሞትም ጊዜ አለው፤ ለመትከል ጊዜ አለው፤ ለመንቀልም ጊዜ አለው፤ ለመግደል ጊዜ አለው፤ ለማዳንም ጊዜ አለው፤ ለማፍረስ ጊዜ አለው፤ ለመገንባትም ጊዜ አለው፤ ለማልቀስ ጊዜ አለው፤ ለመሣቅም ጊዜ አለው፤ ለሐዘን ጊዜ አለው፤ ለጭፈራም ጊዜ አለው፤ ድንጋይ ለመጣል ጊዜ አለው፤ ድንጋይ ለመሰብሰብም ጊዜ አለው፤ ለመተቃቀፍ ጊዜ አለው፤ ለመለያየትም ጊዜ አለው፤ ለመፈለግ ጊዜ አለው፤ ለመተው ጊዜ አለው፤ ለማስቀመጥ ጊዜ አለው፤ አውጥቶ ለመጣልም ጊዜ አለው፤ ለመቅደድ ጊዜ አለው፤ ለመስፋትም ጊዜ አለው፤ ለዝምታ ጊዜ አለው፤ ለመናገርም ጊዜ አለው፤ ለመውደድ ጊዜ አለው፤ ለመጥላትም ጊዜ አለው፤ ለጦርነት ጊዜ አለው፤ ለሰላምም ጊዜ አለው።“
የሰይፈ ሥላሴ ፀሎት ከክፉ ነገር ይጠብቀን!
___________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: መስከረም ፪ሺ፲፪ ዓ.ም, መንፈሳዊ ውጊያ, ስላሴ, ቅድስት ሥላሴ, ቅድስት ቤተክርስቲያን, ቅድስት ድንግል ማርያም, ትምህርት, ኃጢአት, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን, ኢየሱስ ክርስቶስ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሐዶ እምነት, ፀሎት, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 20, 2019
________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: መስከረም ፪ሺ፲፪ ዓ.ም, ስላሴ, ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን, ኢየሱስ ክርስቶስ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሐዶ እምነት, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith | Leave a Comment »