Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • April 2023
    M T W T F S S
     12
    3456789
    10111213141516
    17181920212223
    24252627282930
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ሊሲፈራውያን’

የኢትዮጵያን ቀለማት በመረጠችው ቦሊቪያ በአ’ማራ ዜጎች ላይ የዘር ጭፍጨፋ እየተካሄደ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 20, 2019

ቦሊቪያ እንደ ጋና የሉሲፈራውያኑ ኮከብ ያረፈበትን አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ባንዲራ ስላልመረጠች ጥንታውያኑ አማራ ነዋሪዎቿ የኢትዮጵያን ሕዝቦች ስቃይ በመጋራት ላይ ናቸው።

በጥንታዊው ክርስትና፣ በጥንታውያን ሕዝቦች እና በኢትዮጵያ የማርያም መቀነት ቀለማት ላይ የሚካሄድ የቀለም አብዮት

በጣም የሚያስገርም ዘመን ላይ እንገኛለን ፥ በርግጥ ዓለማችን ትንሽ ሆናለች።

የኢትዮጵያን ቀለማት የያዙት ቦሊቪያውያን የሉሲፈራውያኑ ተቋም ሲ.አይ.ኤ ያካሄደውን መንፈቅለ መንግሥት በጥብቅ በመቃወም ላይ ይገኛሉ። ሆን ተብሎ በርዕዮተ ዓለም እንድትከፋፈል የተደረገችው ደቡብ አሜሪካዋ ቦሊቪያ ልክ እንደ ቺሌና ቬኔዝዌላ ታይቶ በማይታወቅ የእርስበርስ ጦርነት ተናውጣለች። ብዙዎች ተገድለዋል። ሉሲፈራውያኑም በአጭር ጊዜ ውስጥ እራሳቸው ያስቀመጡትን አብዮታዊ ዲሚክራሲያዊፕሬዚደንት ኢቮ ሞራሌስን ከስልጣን እንዲወገድና እራሳቸው በመረጧት ሴት እንዲተካም አድርገዋል።

ተመሳሳይ ሁኔታም በአረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ቀለማቱ ባለቤት በሃገረ ኢትዮጵያ በመታየት ላይ ነው።

ከሰባት ዓመታት በፊት(መለስ ዜናዊን ሲገድሉት) በኢትዮጵያ ሃገራችንም ተመሳሳይ መፈንቅለ መንግስት(መፈንቅለ ሥርዓት) በሉሲፈራውያኑ ተካሄዶ ነበር። 666ቱ ገዳይ አብዮትም የዚህ መፈንቅለ ሥርዓት ልጅ ነው። የሁለቱ መፈንቅለ ሥርዓታት ዓላማም ሃገራዊ፣ ብሔራዊ፣ ክርስቲያናዊ እና የጥንት የሆነውን ነገር ሁሉ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ ነው። በኢትዮጵያ አማራ እና ትግሬየተባሉትን ጥንታውያን ኢትዮጵያውያንን ፥ በቦሊቪያ ደግሞ ጥንታዊ የሆነውን የአማራ ነገድ ከእናት ሃገራቸው ማጥፋት ነው። ልክ መለስ ዜናዊን እና አብዮት አህመድን በኢትዮጵያ እንዳዘጋጇቸው ፥ በቦሊቪያም ከአማራ ነገድ የሆነውን የቀድሞ ፕሬዚደንትን ኢቮ ሞራሌስን ሤረኛ በሆነ መልክ አዘጋጅተውታል።

በደቡብ አሜሪካዎቹ ቦሊቪያ፣ ቺሌ እና ፔሩ የሚገኙትና “Pueblos Indiginas / ፑዌብሎስ ኢንዲኺናስበመባል የሚታወቁት ጥንታውያኑ የአገሬው ሕዝቦች መጠሪያቸው አይማራነው። 11 ሚሊየን ነዋሪዎች ባሏት ቦሊቪያ የአይማራ ሕዝብ ቁጥር 1.5 ሚሊየን ወይም 20% ይጠጋል። አብዛኛው የቦሊቪያ ነዋሪ ከአውሮፓውያን ጋር የተካለሰ ሲሆን ለረጅም ጊዜ ስልጣኑንም የያዘው እነዚህ ሜስቲዞስ / ክልሶችየሚባሉት ናቸው። ቦሊቪያን እንደ አይማራ ከመሳሰሉት ያገሬው ጥንታውያን ነዋሪዎች ለማጽዳት ዘር ከመከለስ እስከ ምግብና ውሃ መበከል ያልተሞከረ የዘር ማጥፋት ዘመቻ አልነበረም።

ከአሥር ዓመታት በፊት ሉሲፈራውያኑ የዓለማችን ፈላጭ ቆራጮች ለመጀመሪያ ጊዜ ከዚሁ የአይማራ ነገድ የወጣውን የአገሪቷን መሪ ኢቮ ሞራሌስንሥልጣን ላይ አወጡት። ምንም እንኳን ኢቮ ሞራሌስ የአይማራ ነገድ ይሁን እንጅ ተጠሪነቱ ግን ለሉሲፈራውያኑ ነው። የአሜሪካ ተቀናቃኝ እንዲሆን (የሚቆጣጠሩት ተቀናቃኝ / Controlled Opposition) ብሎም የሶሺያሊስታዊ ሥርዓት አራማጅ እንዲሆን አዘዙት። አሁን ልክ ጊዜው ሲደርስ ከስልጣን አስወገዱት፤ በከፊሉ የቦሊቪያ ሕዝብ ዘንድ ተወዳጅነትንም እንዲያተርፍ ስላደረጉት አሁን እየታየ ያለው ህውከት ሊፈጠር ቻለ።

በሃገራችንም ከዚህ የከፋ ህውከት ከመጪው ግንቦት ምርጫበኋላ ሊፈጠር እንደሚችል ለማወቅ ሊቅ መሆን አይጠበቅብንም።

ከሃያ ዓመታት በፊት በኦርቶዶክስ ክርስቲያኗ ሰርቢያ (የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ) የጀመረው የሉሲፈራውያኑ የቀለም አብዮትጥንታውያን እና ኦርቶዶክስ ክርስቲያን በሆኑት ሕዝቦች ዘንድ እንዲቀጣጠል ነው እየተደረገ ያለው። ከኦርቶዶክስ ሰርቢያ ወደ ኦርቶዶክስ ጆርጂያ፣ ዩክሬይን እና ሩሲያ እንዲቀጥል ተደርጓል።

አዎ! የሳጥናኤል ግብ ኢትዮጵያ ነው። ዲያብሎስ ተዋሕዶ ክርስትናን እና ሰንደቅ ዓላማችን በጣም ይጠላቸዋል፣ ይፈራቸዋል። ይህን በሃገራችን እያየን አይደለም?! የክርስቶስ ተቃዋሚዋ ቱርክ እንኳን የኩርድ ሕዝብን በመጨፍጨፍ ላይ ያለቸው ኩርዶች የኢትዮጵያን ቀለማት በመያዛቸው ነው።

የአንድን ሕዝብን ዘር ሙልጭ አድርጎ በማጥፋት የሺህ ዓመታት ልምዱ ያላቸው ቱርኮች እና አረቦች ወደ ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ወደ ቦሊቪያ እና ቬኔዝዌላም ርቀው በመጓዝ እየሠፈሩ ነው። እነዚህ የመጥፎ ዜና እና ጥፋት መልዕክተኞች ከምዕራባውያኑ ረዳቶቻቸው ጋር በማበር የኢትዮጵያን ክርስቲያኖች ደም አፍስሰው ለዋቄዮአላሃቸው እንደሚገብሩት በቦሊቪያም ማራ የተሰኘውን ጥንታዊ ሕዝብ ለዚሁ ሰይጣናዊ ተግባር መፈጸሚያ ለማድረግ በመዘጋጀት ላይ ናቸው።

ኢቮ ሞራሊሰ ከስድስት ወራት በፊት ቱርክን በመጎብኘት የመጀመሪያው የቦሊቪያ ፕሬዚደንት ለመሆን በቅቶ ነበር።

የሚገርም ነው፤ በሃገራችን አማራ፤ በቦሊቪያ አማራ። ሁለቱም በአሁኑ ሰዓት የተዳከሙ ሕዝቦች ናቸው። ልዩነቱ ግን የኢትዮጵያ አማራ የደከመው ኢትዮጵያዊነቱ ስላልጠነከረ/ በኢትዮጵያዊነት ስላልተጠናከረ፣ የአባቶቹን ነፍጠኛነት በመርሳቱ ሲሆን የቦሊቪያዎቹ አማራዎች ግን በአማራነታቸው ስላልጠነከሩ/ስላልተጠናከሩ ነው። ከአማራ በፊት ኢትዮጵያ ስትቀድም ከቦሊቪያ በፊት ግን አማራ ይቀድማል።

በኢትዮጵያ በአማራ ላይ እየተካሄደ ያለው ጥቃት ነዋሪዎቹ አማራበመሆናቸው ሳይሆን አማርኛ በመናገራቸው፣ ተዋሕዶ ክርስቲያን በመሆናቸው፣ አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ሰንደቅ ዓላማ በማውለብለባቸው፤ ባጠቃላይ ኢትዮጵያዊ በመሆናቸው ነው። ትግሬየሚባለውም በትግሬነቱ ሳይሆን ጥቃት የሚፈጸምበት በጥንታዊው ኢትዮጵያዊነቱ እንጂ። እነዚህ ኢትዮጵያውያን ከዚህ ኢትዮጵያዊነታቸው እስካልተላቀቁ ድረስ ጥቃቱ ይቀጥላል። ስለዚህ በተቻለ መጠን አማራነት ኢትዮጵያዊ ባልሆነ አማራነት፣ ትግሬነት ኢትዮጵያዊ ባልሆነ ትግሬነት እንዲቀየሩና እንዲዳብሩ ይደረጋሉ። ትናንትና ኤርትራ ዛሬ ደግሞ ትግራይ እና ኦሮሞ በተባሉት የኢትዮጵያ ክፍለሃገራት የተደረገው ነገር ይህ ነው።

አብንየተባለው ፓርቲ ገና ሲቋቋም ! ! ዋይ! ዋይ!” ብዬ ነበር። በዘውግ የተደራጀ አማራየተሰኘው ሕዝብ በአማራነት ከኢትዮጵያ የሚነጥል ሤር መጠንሰሱን ከውዲሁ ይታየኝ ነበር። የደከመው አማራ ላይ ቶሎ ጥቃት የፈጸሙት፣ መሪዎችየሚሏቸውን ልሂቃን የገደሉትን እና የአብን አመራራትን ወደ እስር ቤት የከተቱት አማራ የሚሉት ነዋሪ ተቆጭቶና ተነሳስቶ ኢትዮጵያዊነቱን እንዲተውና ኢትዮጵያን የከዳ የአማራ ሃገር እንዲገነባ ነው።

አብንየተሰኘው ፓርቲ ሰሞኑን ከኢትዮጵያ ቀንደኛ ጠላት ከሆኑ ኦነጎች ጋር በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ መቀመጡ ይህን የፀረኢትዮጵያ የሆነ አካሄድ ነው የሚጠቁመን። ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ፓርቲዎች ሁሉም በፀረኢትዮጵያ ኃይሎች የተደራጁና በጠላቶቻችን ባትሪ የሚሞሉ ሃገር አጥፊዎች ናቸው። አሁን በአብን እና በኦነጎች መካከል የተፈጠረው ግኑኝነት ከሰላሳ ዓመታት በፊት በህዋሃት እና ኦነግ መካከል ተካሂዶ የነበረውን ጋብቻ ያስታውሰኛል። ያኔም የጥፋት ኦርኬስትራውን ሲመሩ የነበሩት ምዕራባውያኑ ሉሲፈራውያን ነበሩ ፥ ዛሬም እየመሩ ያሉት እነርሱው ናቸው።

በሠላሳ ዓመት ውስጥ ኦሮሞው እና ትግሬው ከኢትዮጵያዊነት እንዲርቅ ተደርጓል ፥ በመጭዎቹ ሰላሳ ዓመታት ደግሞ አማራው ኢትዮጵያዊነቱን እርግፍ አድርጎ እንዲተው ይደረጋል፤ ያኔ ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር እትኖርም፣ ተዋሕዶ ትጠፋለች፣ አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ቀለማቱም ወደ ጥቁርነት ይቀየራሉየሚል ነው እቅዳቸው። ግን ብዙ መስዋዕት ያስከፍለናል እንጂ ይህ እቅዳቸው አይሳካላቸውም።

ስቃዩና ዕልቂቱ እንዲቀነሱ ግን ባፋጣኝ አማራእና ትግሬየተባሉት ነገዶች ልሂቃቃናቶቻቸው ለዘመናት ለፈጸሙባቸው በደሎች ብድር ከመመላለስ በመቆጠብና እርስበርስ ይቅር በመባባል ባፋጣኝ መተባበር ይኖርባቸዋል። ይህ በአማሮችና ትግሬዎች ላይ የመጣ የህልውና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ ከምጽዋ እስከ ሞያሌ ያሉትን ሌሎቹን ደካማኢትዮጵያውያን ነገዶችን አንስፍስፎ ከመጣው የዋቂዮአላህ ሠራዊት መከላከል ብሎም ኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያንን ከዚህ አውሬ ኃይል ማዳን መቻል ስለሚኖርባቸው ነው።

በሃገራችን፣ በቤተክርስቲያናችን እና በሰንደቅ ዓላማችን ቀለማት ላይ የተነሱትን የዲያብሎስ ቡችሎች ቅዱስ ሚካኤል በሰይፉ ቆራርጦ ከእግራችን ስር ይጣልልን!

ኢትዮጵያውያንን በተበከለ የፈረንጅ ዶሮየሚመርዙት አላሙዲን እና ቢል ጌትስ በቦሊቪያም ተመሳሳይ ፕሮጀክት ለመፈጸም አቅደው እንደነበርና ቦሊቪያም ከልክላቸው እንደነበር ከሚከተለው ቪዲዮ ጋር በተያያዘ አውስቼ ነበር፦

________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ሉሲፈራውያኑ ልክ እንደ ጥቁር አሜሪካውያን በአገራችንም መጭውን ትውልድ በአደንዛዥ ዕጽ በማኮላሸት ላይ ናቸው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 3, 2019

ለ ”ለዘብተኛ ዲሞክራሲበሩን ክፈቱልን ገንዘብ እንሰጣችኋለን አሉን፤ ከዚያም ተሳለቁብን!

____________________

Posted in Conspiracies, Ethiopia | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

ካሊፎርኒያ ሰዶም እና ገሞራ | በኢትዮጵያ ፀበላት ላይ ሤራ የሚጠነስሱት የ እነ ዊል ስሚዝ ቤቶች በእሳት ጋዩ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 12, 2018

ካሊፎርኒያ (ካሊፍ + ኦርኒያ) እየነደደች ነው። በህይወቴ እንደዚህ የመሰለ ነገር አይቼ አላውቅም

ከጥቂት ወራት በፊት ባቀረብኩት ቪዲዮ ላይ “የአርቲስት ዊል ስሚዝና ባለቤቱ ጄዳ የኢትዮጵያ ጉብኝት

ክቡሩን ፀብል ፍለጋ ወይስ ውሃ ለመጠጥ?“ የሚል ጥያቄ ጠይቄ ነበር። ሁሉም በእርዳታ ስም ወደ አገራችን እየገቡ ዲያብሎሳዊ ሥራዎቻቸውን አሁንም ቀጥለዋል።

በጣና ሐይቅ ያሉትን ብርቅ ገዳማት ለማዘጋት እምቦጩን ተከሉ፣ በላሊበላ መኻን ለሆኑ እህቶቻችን ለመጸንስ እንዲችሉ የሚረዳቸውን ኩሬ “ቢልሃርዝያ” አለበት በማለት አዘጉት፣ በትግራይ ደግሞ ፈውስ የሚሰጡትን ድንቅ ፀበላት በ ”ኮሌራ” አምጭ ባክቴሪያ በመበከል ብዛት ያላቸውን ወገኖቻችን ከገደሏቸው በኋላ ነዋሪው ጸበል እንዳይጠቀም ተደረገ…. እንግዲህ፡ ይህ ለአለፉት ጥቂት ወራት ብቻ መሆኑ ነው። እግዚአብሔር አያይም፥ የያዕቆብ አምላክ አያስተውልም እያሉ እኮ ነው።

ጊዜውን ጠብቆ ልክ በኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ዕለት የወጣ ዜና፤ የኛዎቹ ፀጥ ብለው ነበር፥ ርዕሱ ላይ እናተኩር፦

+ ‘Holy Water’ Blamed for Cholera Outbreak In Ethiopia

+ Cholera Outbreak ‘sparked By Holy Water’ as Deadly Disease Kills 10 And Infects 1,200

+ Cholera Outbreak Spread By Holy Water Leaves 10 Dead And 1,200 Infected

ታዋቂ የሆኑት የሆሊውድ አርቲስቶች እና የሉሲፈር አምባሳደሮች፤ የእነ ካርዴሺያኖች፣ ሊሊ ፓምፕ፣ ማርቲን ኢጊ አዛሊያ፣ ኬንዳል ጄነር ካትሊን ጄነር ዊል ስሚዝ ሌዲ ጋጋ (ስሞቻቸው ሁሉ ልክ እንደ ጣዖት አምላኪዎቹ፡ ዲያብሎሳዊ ቃና ያላቸው ናቸው) እና የሌሎችም መኖሪያ ቤቶች፡ “ ውልሴይ እሳት” የሚል ቅጽል ስም በተሰጠው በካሊፎርንያው የዱር እሳት በመጋየት ላይ ናቸው። እነዚህ ትዕቢተኞች በእሳት ቃጠሎው ሳቢያ ቤቶቻቸውን ለመልቀቅ ተገደዋል። ይቅመሷት፤ ማሊቡ የተባለውን መንደር የምድር ገነት ለማድረግ አልመው ነበርና። ዊልሴይ እሳት = ዊል = ዊሎው = ዊል ስሚዝ

አሁን ድሃዎቹም ኃብታሞችም እኩል ናቸው፤ ሁሉም ቤት አልባ ሆነዋል!

እነዚህ ቅብጥብጥ ሀብታም ሰዎች አሁን ለድሆች እና ለቤት አልባዎች የበለጠ ይቆረቆሩ ይሆናል የሚል ተስፋ አለኝ።

የመጭው ዘመን ምን እንደሚመስል እግዚአብሔር እያሳየን ነው።

ከዚህ አሰቃቂ ሁኔታ የምናገኘው ጥልቅ ትምህርት አለሰዶም እና ገሞራም ድራሻቸው እስኪጠፋ ተቃጥለዋል፤ የዘመናችን የሰዶማውያን መናኽሪያ የሆነችው ካሊፎርኒያም ዳግም ሎጥ ለቅቆ ከወጣ በኋላ በመሬት መንቀጥቀጥ ትናወጣለች፣ በእሳትም ትጋያለች።

ካሊፎርኒያ እና ሳዑዲ ባቢሎን ለምንገኝ ወገኖች፡ ዳግም ሎጥ ለመሆን ቶሎ ያብቃን።

______

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ከሶሪያ በኋላ | ሮማውያኑ ሉሲፈራውያን በኢትዮጵያ ላይ ከባድ ሴራ እየጠነሰሱ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 3, 2017

[1 ዜና መዋዕል 12:32]

ዘመኑን የተረዱና እስራኤላውያንም ምን ማድረግ እንደሚገባቸው የተገነዘቡ የይሳኮር ሰዎች ሁለት መቶ አለቆች፤ በእነርሱም ሥር ሆነው የሚታዘዙ ዘመዶቻቸው

ምንም በአጋጣሚ ወይም በድንገት የሚከሰት ነገር የለም። ነገሮች ሁሉ እርስበርስ የተገናኙ ናቸው። እያንዳንዱ ሀሳብ ቃል እና ድርጊት በማይታየው የኃይል ድር ላይ በየቦታው ተጽእኖ ይፈጥራል። እንደ፡ ጥሩ ወይም መጥፎ፣ ጤና ወይም በሽታ፣ ደስታ ወይም ሃዘን፣ ፍቅር ወይም ጥላቻ፣ ብርሃን ወይም ጨለማ የመሳሰሉት ተቃራኒ ጥንዶች፡ ተቃራኒ ውጤት ያላቸው የሚመስሉትን ምርጫዎችን ወይም ሁኔታዎችን ይፈጥሩልናል። ምንም እንኳን በጥንድዮሽ ግዛት ውስጥ መንቀሳቀስ እንደሌለብን ብናውቅም፣ እነዚህ ተቃራኒ ሁኔታዎች መኖራቸውን ልንክድ ግን አንችልም። ዋናው ቁምነገር ምርጫችን ነው፤ ወይ ቅዱሱን ወይ ርኩሱን ነው መያዝ የምንችለው፤ ወይ እግዚአብሔር ለሰጠን ለጥሩው፣ ለጤናማው፣ ለደስተኛው፣ ለአፍቃሪውና ብርሃናማው ዓለም እንታገላለን ወይም ለተቃራኒው የዲያብሎስ ዓለም እጃችንን እንሰጣለን፤ ሌላ ምርጫ ሊኖረን አይችልም።

ሰይጣን በትእቢቱ ምክንያት ከገነት ከመባረሩ በፊት የንጋት ልጅ፣ ብርሃን ያዥ ይባል ነበር፣ [ትንቢተ ኢሳይያስ 1412] ይህ ማዕረጉ መገፈፉ ግን ለተከታዮቹ አልተዋጠላቸውም፣ አሁንም ድረስ እውቀት ይሠጣል፣ “ብርሃኑን ይዞ ነው ከገነት የወጣው” ብለው ያስተምራሉ፡፡ ይህም ሉሲፈራዊነት ይባላል።

ለተቃራኒው የዲያብሎስ የጨለማ ዓለም እራሳቸውን አሳልፈው የሰጡት እነዚህ ኃይሎች (ሉሲፈራውያን) የተሰጣቸው ጊዜና ኃይል ውሱን በመሆኑ ተልዕኮዎቻቸውንና ሥራዎቻቸውን በደንብ አድርገው ያውቃሉ፤ እያንዳንዷ ዕለት የትግልና የፍልሚያ ዕለት መሆኗንም ይገነዘባሉ። እግዚአብሔርን በመካዳቸው ትግላቸው ሁልጊዜ ከእግዚአብሔር ልጆች ጋር ነው፤ ተጣድፈዋል፤ ፍልሚያውንም ከመቼውም በላይ በማጧጧፍ ላይ ይገኛሉ።

እነዚህ ሉሲፈራውያን ሥራዎቻቸውን በተግባር ላይ የሚያውሉበት ጊዜና ቦታ እንዲሁ በአጋጣሚ ሳይሆን፡ በጥንቃቄ ተመረጦና አስፈላጊውን ውጤት ሊያመጣ እንዲችል ተደርጎ ነው።

እንደምሳሌ ብንወስድ፡ ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ አቅርቤዋለሁ፤ መስከረም ፩፤ የኢትዮጵያ አገራችን አዲስ ዓመት፣ የብዙ ቅዱሳን የልደት ዕለት ነው። ይህ ዕለት በሉሲፈራውያኑ ዘንድ ለሽብር መመረጡ ያለምክኒያት አልነበረም።

ባለፈው የብርሃነ ትንሳኤ በዓል ዕለታችንም ጸረክርስቶሱ የቱርክ መንግስት ቁልፍ የሆነ ሕዝባዊ ሬፈረንደም ለማካሄድ መምረጡ፡ አውሬው ከጉድጉዱ እየወጣ፡ እንዲሁም ኃይልና ድፍረትንም እያገኘ መሆኑን ለማሳየት በማሰብ ነበር።

ርኩስ የሆነው የሰይጣን ቀን መቁጠሪያ

ሚያዚያ 23 (May 1) ይህ ዕለት ከቀጰዶቅያ አገር (በአሁኒቷ ቱርክ ግዛት ሥር ነው የሚገኘው) የሆነው የኢትዮጵያ ጠባቂ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ እረፍት ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓል ነው። ይህን ዕለት የእግዚአብሔር ልጆች ከጥንት ጊዜ ጀምረን ሲያስቡት፤ ሉሲፈራውያኑ ደግሞ፤ በቅርብ ጊዜ “ሜይ ደይ” ወይም “ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን” ብለው ሰይመውታል። ሌላ ብዙ የማይታወቀው፤ እ..አ ከ April 30 (ሚያዚያ ፪፳ / May 1 ሚያዚያ ፳፫) እስከ May 6 (ሚያዝያ ፳፰) ድረስ ያሉት ቀናት (የቅዱሳን ዕለታት ጊዮርጊስ፣ ተክለ ሃይማኖት፣ መርቆርዮስ፣ ዮሴፍ፣ መድኃኔዓለም እና አማኑኤል (6) የሚውሉበት) ከጥንት ጀምሮ በሉሲፈራውያኑ ዘንድ በጣም ኃይለኛ የሆኑ ቀኖች ናቸው። እነዚህ ቀናት የ “ቤልታኔ በዓል” የሚል ስያሜ ተሰጥቷቸዋል። እነዚህ ቀኖች ሉሲፈራውያኑ በይበልጥ በጨለማ ቁጥጥር ሥር የሚገኙበትና ጨለማን ተገን አድርገው ርኩስ ተግባር የሚፈጽሙባቸው ርጉም ቀናት ናቸው።

እነዚህ ጥንታዊ ቀኖች በሉሲፈራውያኑ በአጋጣሚ የተመረጡ አልነበሩም፤ በጣም ኃይለኛ የሆኑ ቀናት በመሆናቸው እንጂ።

ከጥንት ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በ April 30 (ሚያዚያ ፪፳ / May 1 ሚያዚያ ፳፫) እና May 6 (ሚያዝያ ፳፰) ያሉት ቀናት ቀንዳማው ፍየል ባፎሜትን የሚያመልኩት ሉሲፈራውያን አምልኮታችውን፣ መሠዊያዎችን የሚሠሩበት እና ሰብዓዊ መሥዋዕት የሚያቀርቡባቸው ቀናት ናቸው።

ሶርያ እስክ ኢትዮጵያ ፡ ቁልፍ በሆኑ ቦታዎች ምን እየተካሄደ እንደሆነ እንመልከት። ሊሲፈራውያኑ ሰብዓዊ ስሜት ለማነሳሳት፣ ደም ለመፋሰስና ሞትን ለመፍጠር ግልጽ የሆኑ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ፦

1. ሴቶችን እንደ እንስሳት የትምትቆጥርዋ ሳዑዲ አራቢያ በተባበሩት መንግሥታት የሴቶች መብት አስከባሪ ኮሚቴ ውስጥ በሉሲፈራውያኑ ተመርጣለች። ለ እግዚአብሔር ፍጥረታት ግድ የሌላቸውን፣ በተለይ በእስራኤላውያንና ኢትዮጵያውያን ላይ እጅግ በጣም ከፍተኛ የሆነ ጥላቻ ያላቸውን ሰነፍ አረቦችን ስልጣን ላይ በማስቀመጥ ቁልፍ ዓለም አቀፋዊ ድርጅቶችን እንዲመሩ እየተደረጉ ነው። ከእነዚህም አንዱ የዮርዳኖሱ አረብ፡…. የተባበሩት መንግሥታት ሰብዓዊ መብቶች አስከባሪ ድርጅት አለቃ አል=ሁሴን ኢትዮጵያውያንን ለማስጠንቀቅ ወደ ኢትዮጵያ ተጉዟል። እስከ ነገ ይቆያል። ወቸውጉድ፡ እሳት እና ውሃ፡ አረብ እና የሰብዓዊ መብት!

2. በፈረንጆቹ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዕለት፡ በ 23 Apr 2017፡ በፈረንሳይ የመጀመሪያው ዙር የፕሬዚደንታዊ ምርጫ ተካሄደ። አሁን ደግሞ ሲፈራውያኑ ይህን ርኩስ ተግባር በሚያገባድዱበት ማግስት፡ በ 6 Apr 2017፡ ፈረንሳይ ፕሬዚደንቷን ትመርጣለች፤ ይህም በአጋጣሚ አይደለም። ልክ በመላው አውሮፓ እንደሚታየው ምርጫው በኮሌራና በወረርሽኝ መካከል ነው። የሚመረጠው ግን ማክሮን የተባለውና የጸረክርስቶሱ ርኩስ መንፈስ ያደረበት አውሬ እንደሚሆን የሚያጠራጥር አይደለም። በ25 ዓመት እድሜ የምትበልጠውን አስተማሪውን “አግብቷል” የተባለው ማክሮን ሰዶማዊ መሆኑ አፍንጫው ይናገራል። ጂቡቲን ከኢትዮጵያ የሰረቀችው ፈረንሳይ በመጪው ጊዜ ዋና የሽብር ፈጣሪዎች መናኽሪያ ትሆናለች

3. የተባበሩት መንግሥታትን፣ አውሮፓን እና አሜሪካን የሚመሩት ሮማውያን (ቫቲካን) ናቸው። የቫቲካን ጳጳሶች የምድራችን ቀዳሚ የክርስቲያኖች ሃገር የሆነችው ኢትዮጵያን አንዴም ጎብኝተው አያውቁም፤ ለዚህም ታላቅ ምስጢር አለ፡ በቅርቡ ይገለጥልናል። አድርባዩ የሮማው ጳጳስ ፍራንሲስ ባለፈው አርብ ወደ ግብጽ አምርተው ነበር። ግብጽን የጎበኙት በሙስሊሞች ከሚበደሉት ግብጻውያን ክርስቲያን ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን ጎን ለመቆም ወይም እነርሱን ለማበረታታት ሳይሆን በሮማውያን ቁጥጥር ስር ለሚገኘው ዲያብሎሳዊ የአረብ ግብጻውያን መንግስት ድጋፍ ለመስጠት ነው። ቀደም ሲል ወደ ግብጽ ከማምራታቸው በፊት ፓፓስ ፍራንሲስ አንድ አስገራሚ የሆነ ንግግር አሰምተው ነበር፦

With a heart full of joy and gratitude,” said Pope Francis, “I will soon visit your beloved country, the Cradle of Civilization, the Gift of the Nile, Land of the Sun and Hospitality

ደስታ እና ምስጋና በተሞላው ልቤ እኔ በቅርቡ የሥልጣኔ ምንጭ, የአባይ ስጦታ, የፀሐይ እና የእንግዳ ተቀባዮች ምድር ውዲቷን አገራችሁን እጎበኛለሁ…“

አባይ ስጦታ (አዎ! ግሪኮችም እንዲህ ይሉ ነበር) ሥልጣኔ ምንጭ እና የፀሐይ ምድር። እምም.. አይገርምም? እንደሚታወቀው ግብፃውያን “አሞፅ ራ” የተባለውን የፀሐይ አምላክ ያመልኩ ነበር፡ አሁን ደግሞ “አላህ” የተባለውን የጨረቃ አምላክን ያመልካሉ፤ እነዚህ አማልክት የጌቶች ጌታ እና የነገስታት ንጉሥ የሆነው እግዚአብሔር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አይደለም። ጳጳስ ፍራንሲስ እባቡን የግብጽ ሸህ ጥምጥም አድርገው ሲያቅፉት፤ “ወቸው ጉድ! ለፓትርያርክ ታዋድሮስ ይህን ያህል ሞቅታ አላሳዩም፡ አይ ቫቲካን ሁለት‘! (እዚህ አንብቡት)“ አልኩ።

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ቤል (አራሜይክ) ወይምበኣል የሐሰት አማልክት አምልኮ፡ እንዲሁም ስለ ኤልዛቤል እና ጥንቆላዊ ልምዶቿ በግልጽ ያስጠነቅቀናል።

ከግብፅ ምድርም ያወጣቸውን የአባቶቻቸውን አምላክ እግዚአብሔርን ተዉ፥ በዙሪያቸውም ካሉት ከአሕዛብ አማልክት ሌሎችን አማልክት ተከተሉ፥ ሰገዱላቸውም፤ እግዚአብሔርንም አስቈጡ።

13፤ እግዚአብሔርንም ትተው በኣልንና አስታሮትን አመለኩ[መጽሐፈ መሣፍንት 2: 1213]

በባቢሎንም ውስጥ ቤልን እቀጣለሁ የዋጠውንም ከአፉ አስተፋዋለሁ፤ አሕዛብም ከዚያ ወዲያ ወደ እርሱ አይሰበሰቡም፥ የባቢሎንም ቅጥር ይወድቃል። [ትንቢተ ኤርምያስ 5144]

የሚገርም ነው! አንዳንድ ሰዎች፡ ቫቲካን የእስልምና እምነት መስራች መሆንዋን ይጠቁሙናል። እንደ ኢንሳይክሎፒዲያ ስለሀይማኖት ዘገባአላህ ” የመጀመሪያ የኢስላም ስም ሲሆን ስያሜውን ያገኘው ከባቢሎናውያን “ቤል(በኣል) ነው ይለናል::

አላህ” እሱ የጨረቃ አምላክ ነው:: ከጸሀይ አምላክ ጋር ተጋብቶ አንድ ላይ በመሆን ሶስት የአማልክ ወልደዋል:: እነዚህ ሶስቱ አማልክት ባንድ ላይ ሲጠሩ አላህ ይባላሉ:: እነዚያ ሶስት አማልክት አልላት : አልዩዛ እና ማናት ይባላሉ:: ለዚህም ነው የማጭድ ቅርጽ ያለውን ጨረቃ እና ኮከብ የሚጠቀሙት።

ለማንኛውም፡ አገራችንን፣ ጥንታዊ እምነታችን እና ቅዱሱን የአባይ ውሃ በሚመለከት ግብጻውያን ብቻ ሳይሆኑ፣ ሁሉም በሮማውያን ሥር ያሉት ሉሲፈራውያን አገሮች ተጨንቀዋል። የቫቲካን ሰዎች በታሪክ ከገዳይ አረቦች ጋር በመተባበር ይሰሩ እንደነበር የሚታወቅ ነው፤ ፀረኢትዮጵያ ዘመቻዎችም በታሪክ አጋጣሚ ተደጋግመው ተከስተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ የኅዳሴ ግድብ ግንባታ የሚያከናውነው የጣሊያኑ ሳሊኒ ኩባንያ መሆኑ ይከነክነኝ ነበር፤ ኩባንያው በኢትዮጵያ ላይ በተጠነሰሰው ሴራ ምን ዓይነት ሚና እንደሚጫወት ባላውቅም፤ ግን የአባይ ጉዳይ ግብጽን ብቻ ሳይሆን፡ ወንዛችን የሚነካቸውን መላውን የሚዲቴራንያን ባሕር አገራት፡ ጣሊያንን ጨምሮ፡ በጥልቅና በጥብቅ የሚመለከት ጉዳይ ነው።

ትንቢት ዳንኤል 11÷ 4 ጋር በተያያዘ ሮማውያን በኢትዮጵያ ላይ ከባድ ሴራ እየጠነሰሱ ነው ይሉናል።
አይሁዱ የ ዩቱብ ሰባኪ Steven Ben-DeNoon ምን እንደሚሉ እናዳምጥ፦

__

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: