👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 👉 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 😇 ተክለ ሐይማኖት 👉 ዮሴፍ 👉 መድኃኔ ዓለም
👉 ሙሉ ቪዲዮው ታች ይገኛል…
🐢 Tortoise – ♰ Tekle Haymanot ፤ ሁለቱም ስማቸው በ ‘T/ተ‘ ፊደል ነው የሚጀምረው። የዓለማችን ጥንታዊ ኤሊ የሚኖረው ደግሞ በንግሥት እሌኒ ስም (St.Helena) በምትጠራዋ ደሴት ላይ ነው። ቅድስት እሌኒ የታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ እናቱና እግዚአብሔር ለበጐ አገልግሎት የጠራት ቡርክት ሴት (ንግሥት) ናት።
ንግሥት ዕሌኒ የጌታችንን መስቀል መስከረም ፲፮/16 ቀን ፫፻፳/320 ዓ . ም በዕጣን ጢስ ምልክት ቁፋሮ አስጀምራ መጋቢት ፲/10 ቀን አግኝታ በማውጣት ታላቅ ቤተመቅደስ ጎልጎታ ላይ ሠርታ በክብር አስቀመጠችው። ይህ መስቀልም ከዚያ ዕለት ጀምሮ እንደ ፀሐይ እያበራ ድውይ እየፈወሰ አጋንንት እያባረረ ልዩ ልዩ ተአምራት እየሰራ ሙት እያነሳ ዕውር እያበራ ተአምራቱን ቀጠለ፡፡ ይህንንም ከኃያላን ነገሥታት መካከል የፋርስ ንጉሥ መስቀሉን ማርኮ ፋርስ ወስዶ አስቀመጠው፡፡ በዚህ ጊዜ የአየሩሳሌም ምዕመናን የድሉን ዜና ሰምተው ስለነበር የአንድ ቀን መንገድ ያህል ሄደው በመቀበል ካህናቱ በዝማሬና በቸብቸቦ ወንዱ በሆታ ሴቱ በእልልታ ሆ ! እያሉና ችቦ አብርተው ተቀብለዋቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያኖችም ለመስቀል ችቦእያበሩ በዓሉን በሆታ በእልልታ በስብሐተ እግዚአብሔር የሚያከብሩት ይህንን ታሪካዊ ትውፊት በመከተል ነው፡፡
ብዙ የቤተክርስቲያን አባቶች እንደሚሉት ንጉሡ ሕርቃል ይህንን ታላቅ ድል ለማግኘትና የጌታን ቅዱስ መስቀል ከአሕዛብ / ከፋርሶች / እጅ ለማስመለስ የቻለው በዚያን ጊዜ አብያተ ክርስቲያንናት ሁሉ ለአንድ ሳምንት / አንድ ሱባዔ / ባደረጉትጾም ጸሎት ነው፡፡ ይህንንም ለማስታወስና ጌታን ለማመስገን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንና የግብጽ ኮፕቲክቤተክርስቲያን በየዓመቱ የዐቢይጾም / የጌታ ጾም / ከመጀመሩ አስቀድሞ ” ጾመ ሕርቃል ” ብለው አንድ ሳምንት ይጾማሉ፡፡ ፓትርያርክ ተረክቦ ወስዶ በክብር አስቀመጠው፡፡
ይህ ግማደ መስቀልም ለብዙ ዘመን በእስክንድርያ ሲኖሩ በግብጽ ያሉ እስላሞች እየበዙ ኃይላቸው እየጠነከረ ሔደ በእስክንድርያ የሚኖሩትን ክርስትያኖች ላይ ሥቃይ ያጸኑባቸው ጀመር፡፡ ክርስቲያኖቹም አንድ ሆነው መክረው ለኢትዮጵያዊው ዓጼ ዳዊት እንዲህ የሚል መልእክት ላኩ ” ንጉሥ ሆይ ! በዚህ በግብጽ ያሉ እስላሞች መከራ አጽንተውብናል ኃይልህን አንሥተህ አስታግስልን ብለው ጠየቁት ዳግማዊ ዓጼ ዳዊትም ለመንፈሳዊ ኃይማኖት ቀንተው የክርስቶስ ፍቅር አስገድዷቸው ሃያ ሺህ ሠራዊት አስከትለው ወደግብጽ ዘመቱ በዚህ ጊዜ በግብጽ ያሉ ኃያላን ፈሩ ተሸበሩ ንጉሡ ዳግማዊ ዳዊትም እንዲህ የሚል መልዕክት ለእስላሞቹ ላከ በተፈጥሮ ወንድሞቻችሁ ከሆኑት ክርስቲያኖች ካልታረቃችሁ ሀገራችሁን መጥቼ አጠፋለሁ ” የሚል ማስጠንቀቂያ ላከ፡፡
የንጉሡ መልዕክትም ለእስላሞቹ እንደደረሳቸው ፈርተው እንደ ጥንቱ በየሃይማታቸው ጸንተው በሰላም እንዲኖሩ ከክርስቲያን ወንድሞቻቸው ጋር ታረቁ፡፡ መታረቃቸውን ዓጼ ዳዊት ሰሙ በዚህም ጉዳይ ንጉሡ ደስ አላቸው፡፡ እግዚአብሔር አመሰገኑ በግብጽ የሚኖሩ ክርስቲያኖችም ከ አስራ ሁለት ሺህ ወቄት ወርቅ ጋር ደስታቸውን ለኢትዮጵያዊው ንጉሥ ለዳግማዊ ዳዊት በደብዳቤ አድርገው ላኩላቸው፡፡ ንጉሡም የደስታውንደብዳቤ ተመልክተው ደስ አላቸው ወርቁን ግን መልሰው በመላክ እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጻፉ፡፡ በግብጽ የምትኖሩ የክርስቶስ ተከታዮች ሆኖ እንኳን ደስ አላችሁ የላካችሁልኝ 12,000 ወቄት ወርቅ መልሼ ልኬላችኋለሁ፡፡ የእኔ ዓላማ ወርቅ ፍለጋ አይደለም የክርስቶስ ፍቅር አስገድዶኝ በተቻለኝ ችግራችሁን ሁሉ አስወገድኩላችሁ አሁንም የምለምናችሁ በሀገሬ ኢትዮጵያ ረሀብና ቸነፈር ድርቅ ስለወረደብኝ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ቅዱስ መስቀልና የቅዱሳን አጽም ከሌሎች ክቡራን ዕቃዎች ጋር እንድትልኩልኝ ነው የሚል ነበር፡፡ በእስክንድርያም ያሉ ምዕመናን ይህ መልዕክት እንደደረሳቸው ከሊቃነ ጳጳሳትና ከኤጲስ ቆጶሳቱ ጋር ውይይት በማድረግ ይህ ንጉሥ ታላቅ ክርስቲያን ነው፡፡ ስለዚህ ልቡን ደስ እንዲለው የፈለገውን የጌታችንን ግማደ መስቀል ከቅዱሳን አጽምና ንዋየ ቅዱሳት ጋር አሁን በመለሰው ወቄት ወርቅ የብርና የነሐስ የመዳብና የወርቅ ሣጥን አዘጋጅተን እንላክለት ብለው ተስማምተው በክብር በሥነ ሥርዓት በሠረገላና በግመል አስጭነው ስናር ድረስ አምጥተው ባስረከቧቸው ጊዜ በእጃቸው እያጨበጨቡ በእግራቸው እያሸበሸቡ በግንባራቸው እየሰገዱ በክብር በደስታ ተቀበሏቸው፡፡ መስከረም 16 በኢትዮጵያ ታላቅ ብርሃን ሌሊትና ቀን ሦስት ቀን ሙሉ ሲበራ ሰነበተ፡፡
ግማደ መስቀሉ ወደ መካከለኛው ኢትዮጵያ ሳይደርስ በድንገት ዓጼ ዳዊት ስናር ላይ አረፉ፡፡ ግማደ መስቀሉም የግድ በዚያው በስናር መቆየት አስፈለገው፡፡ ከዚህ በኋላ የሟቹ የዳግማዊ ዳዊት ልጅ ዓጼ ዘርዓ ያዕቆብ እንደነገሠ ወደ ስናር ሔደ ግማደ መስቀሉን ከሌሎቹ ንዋያተ ቅዱሳት ጋር አምጥተው በመናገሻ ከተማቸው በደብረ ብርሃን ላይ ቤተመቅደስ ሠርተው ለማስቀመጥ ሲደክሙ በሕልማቸው አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል ወዳጄ ዘርዐ ያዕቆብ ሆይ መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ ላይ አስቀምጥ የሚል ሕልም አየ፡፡ ንጉሡም መስቀለኛ ቦታ እየፈለጉ በኢትዮጵያ አውራጃዎች ሁሉ በመፈለግ ከብዙ ቦታ አስቀምጠውት ነበር፡፡ ለምሳሌ በሸዋ በደርሄ ማርያም፣ በማናገሻ ማርያም፣ በወጨጫ መስቀሉን አሳርፈውት ነበር፡፡ ነገር ግን የመጨረሻውን ቦታ ባለማግኘታቸው በራዕይ እየደጋገመ መስቀሌን በመስቀለኛ ሥፍራ አስቀምጥ እያለ ይነግራቸው ነበር፡፡ ዓጼ ዘርዓ ያዕቆብም ለሰባት ቀን ሱባዔ ገቡ፡፡ በዚያም የተገለጸላቸው መስቀለኛውን ቦታ የሚመራህ ዓምደብርሃን ይመጣል አላቸው፡፡ እርሳቸውም ከዚያ እንደወጡ መስቀለኛውን ቦታ የሚመራ የብርሃን ዓምድ ከፊታቸው መጥቶ ቆመ፡፡ በዚያ መሪነት ወደ ወሎ ክፍለ ሀገር አምባሰል አውራጃ ውስጥ ግሸን ከምትባል አምባ መርቶ አደረሳቸው፡፡ በእውነትምይህች ግሸን የተባለችው አምባ ጥበበኛ ሰው እንደቀረጻት የተዋበች መስቀለኛ ቦታ ሆና ስላገኟት የልባቸው ስለደረሰ ደስ አላቸው፡፡ በዚያም አምባ ታላቅ ቤተመቅደስ ሰርተው መስቀሉንና ሌሎች ንዋየ ቅዱሳቱን በየመዓረጋቸው የክብርቦታ መድበው አስቀመጡዋቸው፡፡
ዘመኑም በ ፲፬/14 ኛው ክፍለ ዘመን ነው፡፡ ከእስክንድርያ ሀገር ከመስቀሉ ጋር በልዩ ልዩ ሣጥን ተቆልፈው የመጡትም ዝርዝር ስማቸው ጌታ በዕለተ ዓርብ ለብሶት የነበረው ቀይ ልብስ፣ ከሮም የመጣው ከለሜዳው፣ ሐሙት የጠጣበት ሰፍነግ / ጽዋ / ፣ ዮሐንስ የሳለውኩርዓተ ርዕሱ ስዕል እንዲሁም የተለያዩ የቅዱሳን አጽም፣ ከግብጽ ታላላቅ ገዳማት የተቆነጠረ አፈር፣ የዮርዳኖስ ውሃ ይገኛል፡፡
“የስምህ መነሻ ፊደል የመስቀል ምልክት (♰)ለሆነው እና ክቡር ገናና ለሆነው ስም አጠራርህ ሰላም እላለው ። የወንጌል ተቀዳሚ ስም ማቴዎስ የተባልክ ተክለ ሐይማኖት ሆይ እንደ ችሎታዬ አመሰግንህ ዘንድ አንደበቴ ትፈታልኝ ዘንድ ድንግል ማርያምን እማልዳለሁ።” ገድለ ተክለ ሐይማኖት።
😈አረመኔው ግራኝ ልክ በተክለ ሐይማኖት ዕለት በአክሱም ጽዮን ላይ የዘር ማጥፋት ጦርነቱን ከፈተ፤ ለዋቄዮ–አላህ–ሰይጣን የክርስቲያኖችን ደም የገበረበትን ዕለት እና ሥልጣኑን ለማደላደል ‘በዓለ ንግሥናውን‘ የሚያከብርበትን ዕለትም የመረጠው ሆን ብሎ በሰይጣናዊው ኢሬቻ ማግስት በዚሁ በዕለተ ❖ አቡነ ተክለ ሐይማኖት መሆኑን እናስታውስ።
🐢 በዚህ በዛሬው የአቡነ ተክለ ሐይማኖት ዕለት ሁለቱንም የዓለም ጦርነቶች ያየ የዓለማችን ጥንታዊው ኤሊ ፲፻፺/190ኛ የልደት ቀንን አክብሯል
በአዲስ አበባም ጥንታዊው አንጋፋ ዔሊ“ለቡ” ተብሎ በሚጠራው ሠፈር (እኔ ሠፈሩን “ተክልዬ” እለዋለሁ) በሚገኘው የአባታችን የጻድቁ አቡነ ተክለ ሐይማኖት ውብ ቤተ ክርስቲያን።
💭 ኤሊ በዛሬዋ ኢትዮጵያ ዘ–ስጋ በመታደን ላይ ነች
የፋሺስቱ ኦሮሞ አገዛዝ ሥልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ አንስቶ በኢትዮጵያ የተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ኤሊ ‘ብዙ ገንዘብ ታስገኛለች‘ በማለት ተዋሕዶ ክርስቲያኖችን በማደን ላይ ያሉት አረመኔዎቹ የዋቄዮ–አላህ ጭፍሮች ወደ ኤሊ አደንም እየገቡ መሆኑ እየተነገረ ነው።
በበርካታ የሃገራችን ክፍሎች ኤሊ በርካታ ሚሊዮን ብሮችን ታስገኛለች በማለት አድኖ በአንድ ቦታ ማከማቸት እና የኤሊ ሕገ–ወጥ ዝውውር እየተደረገ መሆኑ ተረጋግጧል።
አዲስ አበባን ጨምሮ፣ ሻሸመኔ፣ ሐረርጌ፣ ምዕራብ ኦሮሚያ እና አፋር ክልል ይህን መሰል ተግባር በስፋት እየተፈጸመ እንደሆነ መረዳት ተችሏል።
የዱር እንስሳዋን በተመለከተ በርካታ የተሳሳቱ መረጃዎች ይሰራጫሉ። ገንዘብ እናገኛለን በሚል በተሳሳተ መረጃ ኤሊ የሚያድኑት ሰዎች ”እጅግ ተፈላጊ” የምትባለዋን ኤሊ አድነው ካገኙ እስከ ፪፻/200 ሚሊዮን ብር ድረስ ዋጋ ታወጣለች ብለው ያምናሉ።
🐢 “እጅግ ተፈላጊ” የምትባለዋ ኤሊ የሚከተሉት ልዩ መለያዎች አሏት ተብሎ ይታመናል፤
- ☆ እንደ ማግኔት ብረቶችን የመሳብ አቅም አላት፣
- ☆ ንጹህ ውሃ ጎን ብትቀመጥ፤ ውሃው ይደፈርሳል፣
- ☆ ጭለማ ውስጥ አንገቷ አንጸባራቂ ብርሃን ያወጣል፣
- ☆ በካሜራ ምስሏ ሊነሳ አይችልም፣
- ☆ በኤሊ ውስጥ ሜርኩሪ ይገኛል፣
እርኩስ የዋቄዮ–አላህ መንፈስ በሰፈነባት በዛሬዋ ኢትዮጵያ ዘ–ስጋ ወራሪዎቹ የዘመናችን አማሌቃውያን እነዚህን ሐሰተኛ መረጃዎች በማሰራጨት የሰውን ልጅ ጨምሮ እነዚህንም ምስኪን እና ሰላማዊ የሆኑ የእግዚአብሔር ፍጥረታትን በማደን ላይ ናቸው።

ለፅንስትከ ተክለ ሐይማኖት ሆይ አስቀድሞ በማኅፀን ለተፀነስከው ፅንስትህና በታኅሣስ ፳፬/24 ቀን ለተውለድከው መወለድም ሰላም እላለሁ።
ለዝክረ ስምከ ተክለ ሐይማኖት ሆይ የስምህ የመነሻ ፌደሉ ትዕምርተ መስቀል ለሆነው ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ። እሱም ገናና የከበረ ስም ነው።
ቅዱሱ አባት ተክለ ሐይማኖት ሆይ፤ ከአረጋዊ ተክል የተገኘህ አዲስ የተክል አበባ ነህ። የሌዊና የይሑዳ ካህናት ይህ ሰማያዊ መልአክ ነውን ወይስ ምድራዊ ሰው እያሉ ስለ አንተ ይደነቃሉ።
ቅዱሱ አባት ተክለ ሐይማኖት ሆይ፤ ስግደትህ በማዕረገ መላእክት ደረጃ ነውና አከናውነህ የሠራሃት ጸሎትህ ባለ ዘመናችን ሁሉ ከጦርነትና ከጽኑ መከራ ሁሉ ጠባቂ ትሁነን።
ቅዱሱ አባት ተክለ ሐይማኖት ሆይ፤ መሥዋዕትን የምታሣርግ ታላቅ ካህን የእግዚአብሔር ባለሟል ነህና ቀንዶቹ ዓሥር ከሆኑ ከእባብ መተናኮልና አንደበቱ ሁለት ከሆነ ሰው ፀብ በክንፈ ረድኤትህ ሠውረህ አድነኝ።
ቅዱሱ አባት ተክለ ሐይማኖት ሆይ፤ ልጆችህ በዚህ ዓለም ብዙ መከራ ቢያገኛቸውም በአንተ ዘንድ ፍጹም ሰላምና እረፍትን እንደሚያገኙ አንተን ተስፋ ያደርጋሉ።
ቅዱሱ አባት ተክለ ሐይማኖት ሆይ፤ ከሐዲዎችን የምትበቀል ቄርሎስ የተባልክ አንተ ተክለ ሐይማኖት ነህ እኮን።
ቅዱሱ አባት ተክለ ሐይማኖት ሆይ፤ የሥላሴን አንድነት ሦስትነት በማስተማር ዓዋጅ ነጋሪነትህ ፍጹም ድንቅ ነው። እባቡን በእርግጫ አንበሳውን በጡጫ ብለው የሚያልፉ የሴትና የወንድ ደቀ መዛሙርት በጸጋ ወልድሃልና።
ያለምንም ተድኅሮ በሥላሴ ስም ይህን ሦስትነት አምናለሁ፤ በተንኮል ወንድማማቾችን እርስ በርስ የሚያባሉትን፣ ደንፍተው የሚያጠቁንን፣ ወዳጅ መስለው ሊያጠፉን የፈለጉትን የሚከተሉትን የጽዮንን ጠላቶች የእግዚአብሔር ቃል ይቅሰፋቸው፣ በተሣለ የመለኮት ሠይፍ አንገታቸውን ይቍረጣቸው፤ አሜን!!!
የአባታችን የአቡነ ተክለ ሐይማኖት ረድኤትና በረከት፡ ምልጃና ጸሎት በሀገራችን በኢትዮጵያ እንዲሁም በመላው ሕዝበ ክርስቲያን ላይ አድሮ ይኑር፡ ሀገራችንን ሊያጠፋ የተነሳውን እርኩስ የዋቄዮ–አላህ–አቴቴ መንፈስን ያጥፉልን፤ ጠላቶቻችንን በእሳት ይጠራርግልን፤ ለዘላለሙ አሜን!
❖❖❖ ተክለ ሐይማኖት ፀሐይ ❖❖❖
የክርስቲያኖች መመኪያ
ተክለ ሐይማኖት ጻድቅ
የእንባችን ማበሻ
ከፈጣሪ የምታስታርቅ
ሰባሊ ወንጌል መናኝ
ሰማያዊ አርበኛ
በጸሎትህ ትሩፋት
ፀሐይ ያበራህ ለእኛ
ቅዱስ አባትችን ሆይ
ሀጢአታችን ስለበዛ
በቃልኪዳንህ አማልደን
በነፍሳችን ሁናት ቤዛ።
አደራ!
______________