Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2022
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    27282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

የዛሬው የቅዱስ ዑራኤል ዕለት ድንቅ ተዓምር ፳፪ ሰኔ ፳፻፲፬ | አምላካችን ምልክቶቹን አሳይቶናል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 29, 2022

👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 😇 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 👉 ዮሴፍ 👉 መድኃኔ ዓለም

ክፍል ፩

ጸሎት ቤት ውስጥ፤ ፳፪ ሰኔ ፪ሺ፲፬ ዓ.ም ቅዱስ ዑራኤል ይህን የጌታችን መታሰቢያ ከ፭ ዓመታት በፊት አሳይቼው ነበር ዛሬ ከበታቹ ያሉት የሻማ ብርሃናት የጽዮንን ቀለማት/ የማርያም መቀነትን ሠርተው ይታያሉ።

በጽዮን ቀለማት የደመቀው የእናታችን የቅድስት ማርያም ስዕል ዛሬ ከበታቹ ያሉት የሻማ ብርሃናት የጽዮንን ቀለማት/ የማርያም መቀነትን ሠርተው ይታያሉ። ኢትዮጵያዊ ገጽታ ያለውን ስዕል

በጥሞና እንመልከተው!

ክፍል ፪

ጌታችን የተገኘበት የ፪ሺ፱ ዓ.ም መስቀል ደመራ በመስቀል ዓደባባይ” በሚል ከ፭ ዓመታት በፊት፤ ገና አረመኔው ግራኝ አብዮት አህመድ መኖሩንም ሳናውቅ አቅርቤው የነበረው ድንቅ ቪዲዮ ነው፤ የዋቄዮ-አላህ-ሉሲፈር ባሪያዎች ለጅሃዳቸው በደብረዘይት (ቢሸፍቱ-ሆራ) ዝግጅት ላይ ነበሩ።

✞ አምላካችን ምልክቶቹን አሳይቶናል ፥ ዳግም ምጽአት / ደብረ ዘይት ✞

እግዚአብሔርሰ ገሀደ ይመጽእ፣ ወአምላክነሂ ኢያረምም፣ እሳት ይነድድ ቅድሜሁ። እግዚአብሔር በግልጽ ይመጣል፤ አምላካችን ዝምም አይልም ከፊቱም እሳት ይነዳል”

✞ የምጽአት ምልክቶች ✞

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሳለ ደቀመዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው የዳግም ምጽአት ምልክትን ጠይቀውታል። እርሱም አስቀድሞ «ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ» ካለ በኋላ የሚከተሉትን ምልክቶች ገልጾላቸዋል።

💭 አስቀድሞ በነቢያት የተነገሩትም ምልክቶች ተጨምረዋል፤

  • ☆ ብዙ ሀሰተኛ ነቢያት ይነሳሉ ፣
  • ☆ ብዙ ሀሰተኛ ክርስቶሶች ይነሳሉ ፣
  • ☆ ታላቅ ክሕደት ይሆናል ፣
  • ☆ በብዙዎች ዘንድ ፍቅር ይቀዘቅዛል ፣
  • ☆ የጦርነት ፣ የርኃብ ፣ የቸነፈር የምድር መናወጥ ወሬ መሰማት፣
  • ☆ ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥት በመንግሥት ላይ መነሳሳት፣
  • ☆ ክርስቲያኖች በአሕዛብ የተጠሉ መሆን፣
  • ☆ የብዙዎች ለሞት ተላልፈው መሰጠት ፣
  • ☆ የብዙዎች ከእውነት መንገድ መሰናከል ፣
  • ☆ የጥፋት ርኲሰት በተቀደሰችው ስፍራ መታየት፣
  • ☆ የተመረጡት እስኪስቱ ድረስ ድንቅ ተአምራት መደረግ ፣ (ማቴ ፳፬ የመከራ ዘመን ይሆናል)
  • ☆ «ስለ ሕዝብ ልጆች የሚቆመው ታላቁ ሚካኤል ይነሳል።» (ዳን ፲፪ ፥ ፩ )
  • ☆ የአመጽ ሰው የክርስቶስ ተቃዋሚ መነሳት ፣ (፪ ተሰ ፪ ፥ ፫ )
  • ☆ የአውሬው የስድብ አፍ በገልጽ በብዙዎች ላይ መገለጽ (ራእይ ፲፫፥ ፭ ) ፣ ወዘተ

ከላይ የተገለጹት ምልክቶች በአሁኑ ዘመን በአብዛኛው የታዩ እና እየታዩ ያሉ ናቸው። ትንቢቱን የተናገረው ባለቤቱ ወልደ አምላክ ክርስቶስ በመሆኑ የበለጠ ትኩረት እንድናደርግበት ግድ ይለናል። ከዚህም ተነስተን የክፋት ትንቢት መፈጸሚያ እንዳንሆን መጠንቀቅ ይገባናል። ከምልክቶቹ ፍጻሜ አንጻር ግን እራሳችንን መታዘዝ በማስተማር ሕይወታችንን በንስሐ ወደ እግዚአብሔር ማቅረብ ብቸኛ መፍትሄ ነው።

✞ ምጽአት ✞

ከብዙ የምጽአት ምልክቶች በኋላ የክርስቶስ ዳግም ምጽአት ይሆናል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ እንዳረገ እንዲሁ ተመልሶ ይመጣል።

በአጠቃላይ ደብረ ዘይት ሁለት ተቃራኒ ነገሮች የሚፈጽሙበትን የነገረ ዳግም ምጽአት ሁኔታን ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምንማርበት የዓቢይ ጾም ሳምንት ነው። ይኸውም ትንሣኤ ዘለክብር እና ትንሳኤ ዘለሀሳር ነው። አንዱ ከእግዚአብሔር ጋር የሚሆንበት ሌላው ከሰይጣን ጋር ኑሮው የሚወሰንበትአንዱ መንግሥተ ሰማያትን የሚወርስበት ሌላው ገሀነመ እሳት የሚገባበት፣ አንዱ የሚደሰትበት ፣ ሌላው ዋይታ የሚያሰማበት፣ የበረከትና የመርገም ቀን፣ የተስፋና ተስፋ የመቁረጥ ቀን፣ የደስታና የጭንቅ ቀን፣ የእልልታና የዋይታ ቀን፣ አንዱ ሌላውን የማያድንበት፣ እናት ልጄን የማትልበት፣ ልጅ እናቴን የማይልበት፣ ባልና ሚስት የሚለያዩበት፣ ጓደኞች ዳግም የማይገናኙበት፣ ኃጥእ ከጻድቅ መተያየት የሚያበቁበት የመጨረሻ እለት ዳግም ምጽአት ናት።

ሰሚ ከሆንን የደብረ ዘይትን ጩኸት ልንሰማ ይገባናል። የምትነግረንን የምጽአትን ምልክቶች፣ የምጽአትን ትንቢቶች፥ «እግዚአብሔርሰ ገሀደ ይመጽእ፣ ወአምላክነሂ ኢያረምም፣ እሳት ይነድድ ቅድሜሁ። እግዚአብሔር በግልጽ ይመጣል፤ አምላካችን ዝምም አይልም ከፊቱም እሳት ይነዳል» ፣ ወዘተ የሚለውን ፣ ጌታ በወንጌሉ በፍርድ ቀን ለእያንዳንዱ እከፍለው ዘንድ በቁጣ እመጣለሁ ያለውን ፣.. ከደብረ ዘይት ልንማር ይገባናል። ያለዚያ ግን በመጨረሻው ቀን ዕጣ ፈንታችን ከዲያብሎስ ጋር እሳቱ በማይጠፋ እና ትሉ በማያንቀላፋ በገሃነመ እሳት ሥቃይ ይሆናል ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን !

💭 ክርስቶስ በደመራ ታየ – እኛን “አትፍሩ” – ጠላቶቻችንን “ተጠንቀቁ”! ይላል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 28, 2016

______________

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: