
💭 ሙሉ በሙሉ የተከተበውና ቢል ጌትስ በኮቪድ ተያዘ። የ 66’6 ዓመቱ የማይክሮሶፍት መስራች ቀደም ሲል የኮቪድ ክትባቶች የወረርሽኙን ስርጭትን ያቆማሉ በማለት ብዙ ቅስቀሳ ያደርግ ነበር።
ይህ ስውየ፤ ነፍሳቸውን ይማርላቸውና፤ በአዲስ አበባ ተካሂዶ በነበረው በጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ የቀበር ሥነ ስርዓት ላይ መገኘቱ ምን ያህል በኢትዮጵያ ላይ ትኩረት አድርጎ እንደነበረ ነበር ሁሌ የሚታወሰኝ። ያው ዛሬ ፍሬውን እያየን ነው፤ ሌላው ዓለም ከክትባቱ ሲርቅ ኢትዮጵያ ግን ከእባብ መርዝ ተቀምሞ የተሰራውን አደገኛ ክትባት በማስገባት ላይ ትገኛለች።
እንግዲህ ልክ ክትባቱን ከየአቅጣጫው ወደ አገራችን መላክ በጀመሩበት ወቅት ነው ‘5G’ የተንቀሳቃስሽ ስልክ ግኑኝነት ቴክኖሎጂ ወደ ኢትዮጵያ እንዲገባ የተደረገው። እስኪ ይታየን፤ ይህ ውድ ቴኮኖሎጂ ወደ ሃገራችን የሚገባው ሕዝባችን በሚጨፈጨፍበትና በብዙ ሚሊየን የሚቆጠሩ ወገኖች ለረሃብና በሽታ በተጋለጡበት ወቅት ነው። በተለይ በከፍተኛ ተራራማ ቦታዎች የሚኖሩ የመንፈስ ማንነትና ምንነት ያላቸው ደገኞች የዚህ ቴክኖሎጂ ሰለባ ይሆናሉ። አልትራቫዮሌት ጨረሩ ወደ ሥውሩ የመንፈሳዊ ሕይወት ዓይናቸው ሰርጎ በመግባት በመንፈስ እንዲዳከሙ ያደርጋቸዋል። ትልልቅ ሳንባዎች ያሏቸውና እስከ ዛሬ ድረስ ጤናማ የሆነ ቀይ የደም ሕዋስ ያላቸው (የሯጮቻችን ስኬታማነት አንዱ ምስጢር) እነዚህ ደገኞች አሁን ለኦክስጅን እጦት በይበልጥ ይጋለጣሉ።
💭 “የኮሮና ክትባት ስለ ጽዮን ዝም ላሉት? | የኢትዮጵያ ነፍሰ ጡሮች ልጃቸውን ላያቅፉ?”
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 6, 2021
💭 “የጸሎት አባቶቻችንን ነጮቹ ይተናኮሏቸው ይሆን? | “አሸጎዳ” በገዳማት እና ዓብያተ ክርስትያናት የተከበበ ነው”
💭 “በጨረር እየጠበሱን ነው | ራዕይ ዮሐንስ ይህን ጠቁሞን ይሆን?”
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 19, 2020
💭 “አመጹ ጀምሯል | የተንቀሳቃሽ ስልክ ግንኙነት ማማዎች በእሳት በመጠረግ ላይ ናቸው“
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 4, 2020
የ5 ጂ ሴል ማማዎች ኮሮና ቫይረስን ያሰራጫሉ አደገኞች ናቸው በሚል ጨረሩን የመለካት ብቃቱ ያላቸው ግለሰቦች በመላው ዓለም ብዙ የ5ጂ ማማዎችን በእሳት በማጋየት ላይ ናቸው።
ለነገሩማ 5ጂ ብቻ ሳይሆን እያንዳንዱ የተንቀሳቃስሽ ስልክ ግኑኝነት ቴክኖሎጂ ትውልድ 1ጂ፣ 2ጂ፣ 3ጂ ፣ 4ጂ መዘዝ ይዞብን ነው የመጣው። እንዲያውም የራዲዮና ቴሌቪዥን ማይክሮዌቭና ሳተላይት ቴክኖሎጂ ገና እንደጀመረ ነው ሕዝብን በሰፊው የመቆጣጠሪያ፣ የግለሰቦችንና ሕዝቦችን ባሕርያትን የመቀየሪያ ባጠቃላይ ዲያብሎሳዊ ተግባራታን የመፈጸሚያ ሁኔታዎች የተፈጠሩት።
ይህን አስመልክቶ እ.አ.አ ከ2005 ዓ.ም አንስቶ እኔ በግሌ ገና በዩርኒቨርሲቲ እያለሁ የልዑል እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እየመራኝ ብዙ አስገራሚ የሆኑ ነገሮችን ለማየት መብቃቴን በጦማሬ ላይ በጊዜው አስፍሬው ነበር። አንቴናዎቹ ገና ሳይስፋፉ ግርግዳን አልፈው ለማዳማጥ፣ ለማየትና ሰዎችን ለመቆጣጠር የሚያስችላቸውን ተንቀሳቃሽ ቴክኖሎጂዎችን በመኖሪያ አካባቢዎች በየጎረቤቱ አስገብተዋል፤ ይህንም ለማንቀሳቀስ በተለይ መጀመሪያ ላይ ቺፑ የተቀበረባቸውን ግብረ–ሰዶማውያንን ይጠቀሙባቸው እንደነበር በጊዜው አውስቻለሁ።
በተለይ መንፈሳዊ የሆኑ ሰዎች፤ በተለይ ተዋሕዶ ኢትዮጵያውያን (ከዚህ ጉዳይ ጋር የተያያዘ ሊሆን ይችላል መምህራን፣ ካህናት ወዘተ ያልተለመደ የባሕርይ መቀያየር እያሳዩ ነው፤ + “NileSat”, “EthioSat”) ይህን በደንብ ተረድተው አስፈላጊውን መንፈሳዊ ሥራ በመስራት እራሳቸውንና ወገኖቻቸውን ሁሉ መከላከል ይኖርባቸዋል። “አባቶች ባካችሁ ወደ ውጩ ዓለም ለህክምና አትሂዱ!” እላለሁ ደጋግሜ። ውጭ ያለን ኢትዮጵያውያንም ይህን አውቀርን ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል፤ ምስጢሩ ከገባን ምንም የሚያስፈራ ነገር አይኖርም!
❖ ይህን የቅዱስ ዮሐንስ ራዕይ ምዕራፍ በደንብ እናጥናው። 1ጂ፣ 2ጂ፣ 3ጂ፣ 4ጂ፣ 5ጂ፣ መጪዎቹ 6ጂ እና 7ጂ የሰባቱ መላዕክትን ቦታዎች የሚይዙ ይሆኑ? በጣም አስደናቂ ነገር ነው!
❖❖❖[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፮]❖❖❖
- ፩ ለሰባቱም መላእክት። ሄዳችሁ የእግዚአብሔርን ቁጣ ጽዋዎች በምድር ውስጥ አፍስሱ የሚል ታላቅ ድምፅ ከመቅደሱ ሰማሁ።
- ፪ ፊተኛውም ሄዶ ጽዋውን በምድር ውስጥ አፈሰሰ፤ የአውሬውም ምልክት ባለባቸው ለምስሉም በሚሰግዱ ሰዎች ክፉኛ የሚነዘንዝ ቍስል ሆነባቸው።
- ፫ ሁለተኛውም ጽዋውን በባሕር ውስጥ አፈሰሰ፤ እንደ ሞተም ሰው ደም ሆነ፥ በባሕርም ከሚኖሩት ሕይወት ያለበት ነፍስ ሁሉ ሞተ።
- ፬ ሦስተኛውም ጽዋውን በወንዞችና በውኃ ምንጮች ውስጥ አፈሰሰ፤ እነርሱም ደም ሆኑ።
- ፭ የውኃውም መልአክ። ያለህና የነበርህ ጌታ ሆይ፥ ቅዱስ ሆይ፥ እንዲህ ስለፈረድህ ጻድቅ ነህ፤
- ፮ የቅዱሳንና የነቢያትን ደም ስላፈሰሱ ደምን ደግሞ አጠጥተሃቸዋል፥ የሚገባቸው ነውና ብሎ ሲናገር ሰማሁ።
- ፯ ከመሰዊያውም። አዎን፥ ሁሉን የምትገዛ ጌታ አምላክ ሆይ፥ ፍርዶችህ እውነትና ጽድቅ ናቸው ብሎ ሲናገር ሰማሁ።
- ፰ አራተኛውም ጽዋውን በፀሐይ ላይ አፈሰሰ፤ ሰዎችንም በእሳት ልታቃጥል ተሰጣት።
- ፱ ሰዎችም በታላቅ ትኵሳት ተቃጠሉ፥ በነዚህም መቅሠፍቶች ላይ ሥልጣን ያለውን የእግዚአብሔርን ስም ተሳደቡ፥ ክብርንም እንዲሰጡት ንስሐ አልገቡም።
- ፲ አምስተኛውም ጽዋውን በአውሬው ዙፋን ላይ አፈሰሰ፤ መንግሥቱም ጨለማ ሆነች ከስቃይም የተነሳ መላሶቻቸውን ያኝኩ ነበር፥
- ፲፩ ከስቃያቸውና ከቍስላቸውም የተነሳ የሰማይን አምላክ ተሳደቡ፥ ከስራቸውም ንስሐ አልገቡም።
- ፲፪ ስድስተኛውም ጽዋውን በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ ላይ አፈሰሰ፤ ከፀሐይም መውጫ ለሚመጡ ነገሥታት መንገድ እንዲሰናዳላቸው ውኃው ደረቀ።
- ፲፫ ከዘንዶውም አፍና ከአውሬው አፍ ከሐሰተኛውም ነቢይ አፍ ጓጕንቸሮች የሚመስሉ ሦስት ርኵሳን መናፍስት ሲወጡ አየሁ፤
- ፲፬ ምልክት እያደረጉ የአጋንንት መናፍስት ናቸውና፥ በታላቁም ሁሉን በሚገዛ በእግዚአብሔር ቀን ወደ ሚሆነው ጦር እንዲያስከትቱአቸው ወደ ዓለም ሁሉ ነገሥታት ይወጣሉ።
- ፲፭ እነሆ፥ እንደ ሌባ ሆኜ እመጣለሁ፤ ራቁቱን እንዳይሄድ እፍረቱንም እንዳያዩ ነቅቶ ልብሱን የሚጠብቅ ብፁዕ ነው።
- ፲፮ በዕብራይስጥም አርማጌዶን ወደሚባል ስፍራ እስከተቱአቸው።
- ፲፯ ሰባተኛውም ጽዋውን በአየር ውስጥ አፈሰሰ፤ ከመቅደሱም ውስጥ። ተፈጽሞአል የሚል ታላቅ ድምጽ ከዙፋኑ ወጣ።
- ፲፰ መብረቅና ድምጽም ነጎድጓድም ሆኑ፥ ትልቅም የምድር መናወጥ ሆነ፤ ሰው በምድር ከተፈጠረ ጀምሮ እንዲህ ያለ ታላቅ መናውጥ ከቶ አልነበረም፤ ከሁሉ በለጠ።
- ፲፱ ታላቂቱም ከተማ በሦስት ተከፋፈለች፥ የአሕዛብም ከተማዎች ወደቁ። ታላቂቱም ባቢሎን የብርቱ ቍጣው ወይን ጠጅ የሞላበትን ጽዋ እንዲሰጣት በእግዚአብሔር ፊት ታሰበች።
- ፳ ደሴቶችም ሁሉ ሸሹ ተራራዎችም አልተገኙም።
- ፳፩ በሚዛንም አንድ ታላንት*ፍ1* የሚያህል ታላቅ በረዶ በሰዎች ላይ ከሰማይ ወረደባቸው፤ ሰዎቹም ከበረዶው መቅሰፍት የተነሳ እግዚአብሔርን ተሳደቡ፥ መቅሰፍቱ እጅግ ታላቅ ነውና።
💭 Microsoft co-founder and global vaccine proponent Bill Gates announced Tuesday he has tested positive for COVID and is experiencing mild symptoms despite being vaxxed and boosted. The 66’6-years-old Gates made the announcement via a Twitter thread:
“I’ve tested positive for COVID. I’m experiencing mild symptoms and am following the experts’ advice by isolating until I’m healthy again…I’m fortunate to be vaccinated and boosted and have access to testing and great medical care…The Gates Foundation is coming together today for the first time in two years, and I am lucky to be on Teams to see everyone and thank them for their hard work…We will continue working with partners and do all we can to ensure none of us have to deal with a pandemic again.”
______________