Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • April 2022
    M T W T F S S
     123
    45678910
    11121314151617
    18192021222324
    252627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for April 26th, 2022

‘ብጹዕ’ አቡነ አረጋዊ በ666ቱ ክትባት በመከተባቸው ታመው በዕለተ ጻድቁ አቡነ አረጋዊ በባቢሎን ዱባይ ለመታከም ሲያስቡ ምን ገጠማቸው?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 26, 2022

😇ገብርኤል 👉 ማርያም 👉 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 👉 ዮሴፍ 👉መድኃኔ ዓለም

ይህ ክስተት ገጠማቸው…

❖❖❖[የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፬፥፳፬]❖❖❖

ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ።

እንግዲህ ልክ በእባቡ ክትባት ከተከተቡና፣ ለእባቡ መርዝም ቅስቀሳ ባደረጉ በዓመቱ፤ ያውም በፃድቁ አባታችን በአቡነ አረጋዊ ዕለት! ያውም የፃድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ ልጆች በትግራይ እየተጨፈጨፉ፣ እየተራቡና ሐኪም ቤቶቻቸው ሁሉ ፈራርሰው በሕክምና ዕጦት እየረገፉ ባሉበት ወቅት፣ ያውም ጥቃት የደረሰበት የፃድቁ አቡነ አረጋዊ ደብረ ዳሞ ገዳም ሁኔታ ምን ላይ እንዳለ በማናውቅበት በዚህ የጨለማ ዘመን፤ ዋው!

እግዚአብሔር ይማራቸው፤ ግን የእግዚአብሔርን ክብር መቀነስ ይሆንብኛልና ‘አባት’ አልላቸውም። ምናልባት አውሬው እንደ እነ አቡነ አብርሃም፣ አቡነ ኤርምያስ፣ አቡነ ናትናኤል፣ ኢሬቻ በላይ፣ አቡ ፋና a.k.a አቡነ ፋኑኤል ቤተ ክህነት ውስጥ ሠርገው እንዲገቡ ያደረጋቸው ‘ዶ/ር ፈሪሳውያን’ መካከል አንዱ ይሆናሉ የሚል ጥርጣሬ ለረጅም ጊዜ ነበረኝ። በጣም አዝናለሁ፤ እነዚህን ሰዎች በደንብ ለተመለከተ ምንም ዓይነት የአባትነትን ማንነት አያሳዩም።

ማንም በሕመም እንዲሰቃይ አንሻም፤ ግን ለመሆኑ ስለሚጨፈጨፉት ጽዮናውያን ተቆርቁረውና አልቅሰው ከማውራትና ከመስበክ ይልቅ ለማይመለከታቸውና ብቃት ለሌላቸው የሕክምናው ሳይንስ የዲያብሎስ ጠበቃ ሆነው አሳፋሪ የ”ተከተቡ” ቅስቀሳ የሚያደርጉት እንደ ዶ/ር አቡነ አረጋዊ + ዶ/ር ዘበነ ለማ ወዘተ የመሳሰሉ ፈሪሳውያን ዛሬም ለእባቡ ክትባት ቅስቀሳ በማድረጋቸውና ሚሊየኖች ምዕመናንን በማሳታቸው ተጸጽተውና እራሳቸውን ዝቅ አድርገው ኢትዮጵያንና እግዚአብሔር አምላኳን በይፋ ይቅርታ ለመጠየቅ የትሕትና ብቃት አላቸውን? ይቅርታ ሳይጠይቁ እንዴት በአደባባይ መታየት፣ መናገር ወይም መስበክ ይቻላቸዋል?

ቪዲዮው ላይ በበቂ ማስረጃ የሳይንስ ልሂቃኑ ሳይቀሩ እንደሚጠቁሙን የኮቪድ ወረርሽኝ ገና ከጅምሩ ከእባብ ነው የተገኘው፤ ክትባቱም የእባብ መርዝ ነው! መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበትን መስቀል አስመልክቶ በስቅለት ዕለት የሚከተለውን ጽፌ ነበር፤

መስቀል ለክርስቲያኖች የሕይወትና የድኅነት ምልክት የሆነው መድኅኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ከተሰቀለበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ሁለቱ ከእንጨት የተገኙት የመስቀሉ ክፍሎች (አግድም እና ቀጥታ) በጣም ትልቅ የሆን ትርጉም ነው ያላቸው።

በኦሪት መስቀል የመርገምና የመቀጫ መሣሪያ ሆኖ ይቆጠር ነበር፡፡ ”ማንም ሰው ለሞት የሚያበቃውን ኃጢአት ቢሠራ እንዲሞትም ቢፈረድበት በእንጨትም ላይ ብትሰቅለው በእንጨት ላይ የተሰቀለ በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና ሬሳው በእንጨት ላይ አይደር”[ዘዳ ፳፩፥፳፪፡፳፫]

የጥንት ሮማውያን ወንጀለኞችን በመስቀል ተሰቅለው እንዲሞቱ ማድረግ ልማዳቸው ነበር፡፡ ክርስቶስ ኢየሱስ ለድኅነተ ዓለም ከመሰቀሉ በፊት የእርግማን ምልክት የነበረው የመስቀል ታሪክ ጌታችን ከተሰቀለበት በኃላ ግን ታሪኩ ተቀይሯል፡፡

  • ቀኝ (በግ – ፍያታዊ_ዘየማን )እና 😈ግራ (ፍዬል – ፍያታዊ ዘፀጋ)
  • ቀኝ (የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዝሙር) እና 😈 ግራ (የዋቄዮ-አላህ-ሉሲፈር ጭፍራ)

ጌታም ቆላተ ዮሳፍጥ ከሚባል በረሀ አውርዶ መናውን ውሀውን ከወትሮ አብልጦ አወረደላቸው። ኃይሉን ክሂሎቱን አሳያቸው። መርዛማ እባብ አስነሥቶ ጐድናቸውን እያስቀደደ አስፈጃቸው። ሙሴም “አቤቱ ጌታዬ ሕዝበ እስራኤልን የሚመግባቸው ቢያጣ ከበረሀ አውርዶ አስፈጃቸው እንዳይሉህ መድኃኒት ፈልግላቸው” ብሎ ጸለየ። ጌታም የወዳጁን ጸሎት ፈጥኖ ይሰማልና “ብረቱን እባብ አስመስለህ በተራራ ላይ ተራዳ ተክለህ ብረቱን በዚያ ላይ ሰቅለህ አሳያቸው። ያን አይቶ ሰምቶ ያመነ ይዳን፤ ያላመነ ይፈጸም፤” አለው። ተራራው የቀራንዮ አምሳል ነው፣ ተራዳው የመስቀል፣ ብረቱ የወልደ እግዚአብሔር፣ እባብ የዲያብሎስ፣ ቍስሉ የኃጢአት፣ መርዙ የመርገመ ሥጋ የመርገመ ነፍስ፣ በረኃው የገሃነመ እሳት አምሳል ነው። ያን አይተው ሰምተው ይዳኑ ማለቱ፤ ስቅለተ ክርስቶስን አይተው ያመኑ ሐዋርያት ሰምተው ያመኑ ምዕመናን የመዳናቸው አምሳል ነው። ያላመኑ ይፈጸሙ ማለቱ፤ ስቅለተ ክርስቶስን አይተው ያላመኑ አይሁድ ሰምተው ያላመኑ አሕዛብ ያለመዳናቸው አምሳል ነው።

ጽዮናውያን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ይህን ሁሉ ዘመን የጠበቃቸውንና ከዘመን ወደ ዘመን በድልና ያሸጋገራቸውን እግዚአብሔር አምላካቸውን ዛሬ ሁሉም ነገር ባለቀበት የፍጻሜ ዘመን በ666ቱ መጫወቻ የእባብ ምራቅ ክትባት ፈጣሪያቸውን እንዳያሳዝኑት አደራ እላለው ፥ ክትባቱ በፍጹም ለጽዩናውያኑ ኢትዮጵያውያን አይሆነንም በተለይ የተዋሕዶ ልጆች እንንቃ፥ ባቢሎን ኤሚራቶች እየተቅበዘበዙ ነው፤ ዛሬም “የእርዳታ ምግብ” ወደ ትግራይ ላክን” ሲሉ ነበር። በተጨማሪ ትውልደ አክሱማዊት ኢትዮጵያ የሆኑትን እነ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖምን፣ ዶ/ር ሊያ ታደስን፣ አቶ ተወልደን(ሹልክ ብለው በመልቀቅ ተሠውረዋል) እንዲሁም አቡነ ማትያስን ይህን ጉዳይ በሚመለከቱ የሥልጣን ወንበሮች ላይ በዚህ ዘመን ማውጣታቸው ዝም ብሎና በአጋጣሚ አይደለም፤ ዋናው ትኩረታቸው የክቡር መስቀሉ አንዱ ክፍል (ቀጥታ) የሚያመላክተውን የሕይወት ዛፍንና የቃልኪዳኑ ታቦት የሚገኙባትን ጽዮናዊቷን ኢትዮጵያ ላይ ነው፤ ስለዚህ አሁን ባለቀ ሰዓት ክትባቱን ወደ ትግራይ እንዳያስገቡ፤ ዋ! ዶ/ር ቴድሮስና ዶ/ር ሊያ! የኮሮና ክትባት በሚል መርፌ በጭራሽ የጽዮናውያንን ሰውነት እንዳታስነኩ ምክሬና ማስጠንቀቂያዬ ነው። የፃድቁ አባታችንን የአቡነ አረጋዊን መጠሪያ የያዛችሁ (አቡነ አረጋዊ + አረጋዊ በርሄ + ሄርሜላ አረጋዊ) ወዮላችሁ! ጥይቱና ረሃቡ ይበቃናል!

❖❖❖

የኢየሱስ ደም ክትባቴ ነው፤

ስጋ ወደሙ መድኃኒቴ ነው!

[ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ ፶፫፥፬፡፭]

“በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።”

______________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith, Health, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: