Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • January 2022
    M T W T F S S
     12
    3456789
    10111213141516
    17181920212223
    24252627282930
    31  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for January 15th, 2022

Tiffany Haddish Arrested & Charged with DUI — Released after Posting a $1,666 bond

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 15, 2022

💭 Arrested for Driving Under The Influence (DUI ), authorities Said.

The actress and comedian was detained after Peachtree City Police got a call about 2:30 a.m. regarding a driver asleep at the wheel on a highway, Assistant Police Chief Matt Myers said in a news release. An officer saw a vehicle matching the caller’s description and stopped Haddish as she pulled into the yard of a residence, Myers said.

Haddish later posted $1,666 bond and was released from the Fayette County Jail, Myers said. He did not release any information about a possible court date.

A spokesman for Haddish did not immediately respond to an emailed request for comment.

Haddish was the breakout star of the smash comedy “Girls Trip” and has starred in such movies as “The Kitchen,” “Night School” and “Like A Boss.” She’s also written the New York Times best seller, “The Last Black Unicorn” and hosted the popular television show “Kids Say The Darndest Things.”

Peachtree City is located about 40 miles (63 kilometers) south of Atlanta.

😈 A $1,666 bond? Woow!

💭 Evil Isaias Afewerki’s Useful Idiot Tiffany Haddish Cries after Stuck in Antichrist Turkey | Sign of The Times

______________

Posted in Ethiopia, Infotainment, News/ዜና, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ተንኰለኞች በጥል ቃል ከበቡኝ፥ በከንቱም ተሰለፉብኝ። በወደድኋቸው ፋንታ አጣሉኝ፥ እኔ ግን እጸልያለሁ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 15, 2022

❖ ❖ ❖

ያለምንም ጉድለት በሥላሴ ስም ይህን ሦስትነት አምናለሁ፤ ወዳጅ መስለው ጽዮናውያንን በመጠጋት፣ እያታለሉና በየዋሕ እንግዳ ተመስለው አክሱም ጽዮንን ያጠቋትን የጽዮን ጠላቶች የሆኑትና በጽዮን ልጆች ላይ በጣም ብዙ ግፍ ያደረሱት የዋቄዮ-አላህ-አቴቴ ጭፍሮች እነ ግራኝ አብዮት አህመድ አሊ እና ተከታይ አህዛብ፣ እባብ ገንዳ መንጋው 😈 ሁሉ የእግዚአብሔር ቃል መቅ ያውርዳቸው፣ በተሣለ የመለኮት ሠይፍ አንገታቸውን ይረደው። አሜን! አሜን! አሜን!

❖❖❖ ጥንታዊው የደብረ ምሕረት ጨለቖት (ሀገረ ማርያም) ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ፣ ከባቢ መቐለ

፲፯፻፹፭/ 1785 ዓ.ም ተመሠረተ ❖❖❖

ጨለቖት ትግራይ ክፍለ ሀገር በእንደርታ አውራጃ የሚገኝ ታሪካዊ ቦታ ነው። ይህ ቦታ ከመቀሌ በስተደቡብ ከሕንጣሎ ከተማ በስተሰሜን የሚገን ሲሆን እንደ ሰንሰለት በተያያዙ ተራራዎች የተከበበ ነው። የቦታው አቀማመጥ ወይና ደጋ ስለሆነ የአካባቢው አየር እንደየወቅቱ ይለዋወጣል። በክረምት ቀዝቃዛ ሲሆን በበጋ ወራት ደግሞ በጣም ይሞቃል።

በሰሜንና በደቡብ ጨለቖትን እየከፈለ ከምስራቅ ወይም ምዕራብ የሚፈስ ወንዝ አለ። ወንዙ በክረምት ወራት ይሞላል። በበጋ ግን መጠኑ የቀነሰ ውሃ የሚወርድበት ሲሆን ከሁለት ቦታ እየተነፈሰ ለመስኖ ተግባር ትልቅ አገልግሎት ይሰጣል።

የጨለቖት ነዋሪ ህዝብ ወንዙን ገድቦ የሚዘራቸው የእህል ዓይነቶች በቆሎ፣ ገብስ፣ ጢፍ፣ ስንዴ…የመሳሰሉት ሲሆን ከአትክልትና ፍራ ፍሬ ዓይነትም ጌሾ፣ ሽንኩርት፣ በርበሬ፣ ሎሚና ብርቱካን ወዘተ ተክሎ እያሳደገ ይጠቀማል።

ሀገረ ማርያም ❖

ጨለቖት መጀመሪያ “ሀገረ ማርያም” ይባል ነበር። ሀገረ ማርያም የተባለበት ምክኒያትም በ፲፫/13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩት አፄ ዐምደ ጽዮን ከጨለቖት በላይ ወደ ምስራቅ ባለ በሁለት ዳገት የተከበበ ጉድጓድ ቦታ ቤተ ክርስቲያን ሰርተው ታቦተ ማርያምን አስገብተው ሲያበቁ በዙርያዋ ያለውን መሬት በመስቀልና በዕጣን አስከልለው ያም ማለት መስቀልና ማዕጠነት ተይዞ የተሰጠው ርስት እየተዞረ ለታቦቲቱ አገልጋዮች ካህናት ማደሪያ ሰጥተው ሌሎች ባላባቶቹ ርስታችን ነው ብለው እንዳይካፈሉ በአዋጅና በውግዘት ይህች “ሀገረ ማርያም” ናት ብለው ስለሰየሟት “ሀገረ ማርያም” ተብላለች። ዳግመኛም ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ግማደ መስቀሉን ይዘው ሲመጡ ጨለቖት ውስጥ ስላደሩ መስቀሉ ያረፈበት ቦታ እስካሁን ድረስ ቤተ መስቀል ይባላል።

ታላቅ ራእይ የተገለጸበት ሱባኤ ❖

መምህር ገብረ ሥላሴ ማዶ ጭኽ በሚባል የቅዱሳን መጸለያ ቦታ ሱባኤ ገብተው ሲጸልዩ ከሰማይ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን እስከሚሠራበት ቦታ ቀስተ ደመና ተተክሎ ሦስት ጌቶች ቅዱሳን መላእክትን አስከትለው ሲወርዱና ቀስተ ደመናው በቆመበት ቦታ ሲያርፍ በራዕይ አዶ እርሳቸውም በሱባኤያቸው ወጥተው ያዩትን አምላካዊ ራእይ ለደጃዝማች ወልደ ሥላሴ ለብቻቸው ነገሯዋቸው። ደጃዝማችም በነገሩ እየተደሰቱ ከመምህር ጋር ሆነው ከሕንጣሎ ከተማ ወደ ሰሜን አቅጣጫ አፍጎል ወደ ሚባለው ቦታ መጥተው ከአደጉበት ጀመሮ እስከ ባሕርያቱ ድረስ በጥድና፣ በወይራ፣ በዋንዛም… የተሸነፈ ታላቅ ወንዝ አገኙ። መምህሩ እየመሩ በጫካው ውስጥ ለውስጥ አብረው ሲጓዙ ወለል ያለ መልክ ባዩ ጊዜ “ዝየ ይትሐነጽ ቤተ እግዚአብሔር”…ማለት የእግዚአብሔር ማመስገኛ ቤተ መቅደስ ከዚህ ይሠራል፤ በዚህ መልክ መካከል ያለው ቆት የሚባለው ትልቅ ዛፍም በጠቅላላ ለቤተ ክርስቲያኑ መዝጊያና መስኮት ይበቃል ብለው ነገርዋቸው።

ያን ጊዜ ቆት በሚባለው ትልቁ ዛፍ ስርም ሁለት አንበሶች ተኝተውበት ነበርና ደጃዝማች ወልደ ሥላሴ ደንግጠው ጦር ወርውረው ሁለቱን ገደሉዋቸው። በዱሩ ውስጥ ተሰውሮ ሲጸልይ የነበረው ባሕታዊ ወጥቶ መላእክት ገደልህ እንጂ እናብስት አልገደልህም ንስሐ ግባ ብሏቸው ተሰወረ። እርሳቸውም መምህራን በወሰኑላቸው ቀኖና መሠረት ኃጢአታቸውን ለማስተሰረይ ንስሐ ገብተናል ከዚህ በኋላ በአዋጅ በተሰበሰበው ሕዝብ ጫካው ተመንጥሮ ቆት የሚባው ትልቁ ዛፍ ተቆረጠ። ቤተ ክርስቲያኑ የሚሠራበት ቦታ ተስተካክሎ ተደለደለ።

የቤተ ክርስቲያኑ ሕንጻ መመሥረት ❖

በዘመነ ማቴዎስ ሰኞ መስከረም ፱/9 ቀን 1785 ዓ.ም በጠቢባኑ መሪነት ከሦስት ክፍል ተከፍሎና ተለክቶ መሠረቱ ተቆፈረ የመሠረቱ ጥልቀት አስር ሜትር ሆኖ በጥቁር ድንጋይ ከተነጠፈ በኋላ በላይ ላይ አሞሌ ጨው እንደ ብሎኬት ተደርድሮ በንጣፍነት ተሠራ። እንዲህ የተደረገበት ምክንያትም ቤተ ክርስቲያኑ የተሠራባቸው ዕንጨት ነክ የሆኑ እቃዎችና ዐምደ ወርቆች በምስጥ እንዳይበሉ ለመከላከል ነው። የቤተ ክርስቲያኑ መቅንና መድረክ ገብን መዝጊያ እንዲሁ በልዩ ልዩ ጌጥ የተሠሩ አአማድ የተዘጋጁት ከተቆረጠው ትልቁ የቆት ዛፍ ስለሆነ አናጢዎቹና ሠራተኞቹ ሕዝቡም ሁሉ ዛፍን ጨለቖት እያሉ በትግርና ቋንቋ አደነቁት “ጨለቖት” ማለት በአማርኛ ቋንቋ መልካም ቆት ማለት ነው፤ በብዙ ቀን በኋላም ቃሉን መሠረት በማድረግ ያገሩ ስም ጨለቖት ተብሎ ተጠራ።

የቤተ ክርስቲያኑ ውስጣዊና አፍአዊ ቅርጽ ❖

የቤተ ክርስቲያኑ ዙሪያ ክብ ሆኖ በሦስት ክፍል የተከፈለ ነው። ውስጣዊ ክፍል ቤተ መቅደስ መካከለኛው ቅድስት ሦስተኛው ደግሞ ቅኔ ማኅሌት ይባላል። ቤተ መቅደሱ ጸሎተ ቅዳሴ የሚደርስበት ቅዱስ ቁርባንና መስዋዕት የሚቀርብበት ነው። ከቀዳስያን በቀር ሌላ ሰው አይገባበትም። ሁለተኛው ክፍል ቅድስትም ቀሳውስትና ዲያቆናት ሰዓታትና ስብሐተ ፍቁር የሚያደርሱበት ምዕመናንም የኅሊና ጸሎት የሚጸልዩበት ነው። ቅኔ ማህሌቱም ሊቃውንትና መዘመራን ያሬዳዊ ማኅሌት የሚያደርሱበት ምዕመናንም የሚጸልዩበት ነው። በጉልላት ላይም ታላቅ መስቀል አለበት።

ቤተ ክርስቲያኑ ሊሠራ ሲል ወልደ ሥላሴ ታመው ስለነበር ፍጻሜውን ሳያዩ እንዳይሞቱ ከመስጋታቸው የተነሳ ሥራው በተጀመረበት ዓመት እንዲያልቅ ስለወሰኑ ወደ ላይ ያለው ከፍታ ከስፋቱ ጋር የተመዛዘነ አይደለም። ስለዚህ የተፈለገውን ያህል ወደ ላይ ሳይረዝም ባጭሩ ጥራው አልቆ ማክሰኞ ሐምሌ ፬/4 ቀን 1785 .ም ታቦቱ ገባ። የቅዳሴ ቤቱ በዓልም በታላቅ ክብር ከተከበረ በኋላ የቤተ ክርስቲያኑ ስመ ማዕረግ “ደብረ ተድላ” ተብሎ ተሰየመ።

የቤተ መቅደሱ የግድግዳ ላይ ሥዕል ❖

የቤተ ክርስቲያኑ ስዕል የተሳለው ሠዓሊ አለቃ ኃይሉ በተባሉ ባለሙያ ነው። የተሳለውም ከሌላው ቦታ በተለየ መልኩ የመቅደሱና የቅድስቱ የውጭ ግድግዳ በሙሉ ሲሆን በቅድስቱ የውጭ ግድግዳ ዙሪያ የተሳለው አቡቀለምሲስ ዮሐንስ ያየው ራእይ ሁሉ ነው። በተለይም ከመቅደሱ ፊት ለፊት የምስለ ፍቁር ወልዳ ሥዕል ዕፁብ ድንቅ በሆነ ህብረ ቀለም የተሳለ ሲሆን በተለያዩ ጊዜ በመሰሉና ረዘም ያለ ጊዜ በመውሰዱ የራስ ወልደ ሥላሴ ስም አንዳንድ ጊዜ ደጃዝማች አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ራስ እየተባለ ተጽፎአል። በግድግዳው ላይ ብቻ ሳይሆን በየበሮቹ ላይ ያሉት ስዕሎች ሁሉ ሳይቀሩ ለተመልካች እጅግ የሚያስደንቁ ሆኖ ይታያል፡፤ የቤተክርስቲያኑ ሥ ዕልና በመስከረም ወር ፲፱፻፸፮/1976 .ም ተጀመሮ በ፯/7 ዓመታት ተፈጽሟል ይባላል።

የቤተ ክርስቲያኑ ንዋያተ ቅድሳት ❖

ከእንግሊዝ ንጉሥ ጊዮርጊስ ሣልሳዊ በስጦታ የተላኩት የሚከተሉት ናቸው፦

የወይን ዘለላ የተቀረፀበት ባለ መክደኛ ድምፅ

ትልቅ ቋሚ መስቀልና መዝሙረ ዳዊት

የቅዱስ ጊዮርጊስ ምስል ከነፈረሱ

መንገር ታቦት ዘውድና አክሊል

ልዮ ልዩ የዜማ ስልት የሚያሰማ ባለምት ኦርጋኖን

ልብሰ መንግስትና ሌሎችም በወርቅ ያጌጡ ብዙ አልባሳት

ብዙ መስቀሎችና ከዕረፈ መስቀሎቻቸው ጋር

ከእነዚህም አልባሳቱ በወርቅ ያጌጡ እቃዎቹም ከወርቅ የተሠሩ ናቸው። ራስ ወልደ ሥላሴም እነዚህን ስጦታዎች ሁሉ በምስጋና ተቀብለው በፊርማቸው ተረክበዋቸዋል። ከውጭ በመጡ አቡስትሊ በተባሉ ግብፃዊ ጠቢብ የተሠሩ ንዋያተ ቅድሳትም የሚከተሉት ናቸው፦

ክወርቅና ከብር የተሠሩ ዘውዶች

መስቀሎች፣ ፃህልና ጽዋዕ

ከበሮ፣ መቋሚያና ጸናጽል

ልዩ ልዩ ያጌጡ አልባሳትና መነሳነስ

የወይን ማጣሪያ ወንፊት

የወርቅ ዙፋንና ወንበር፣ የሐር ምንጣፎች

ጠቢባኑ እነዚህን ሁሉ ሠርተው ለራስ ወልደ ሥላሴ አስረክበዋቸዋል። እርሳቸውም አይተው እጅግ ደስ ስላላቸው በሚልዮን የሚቆጠር ወርቅ ሸልመዋቸዋል ይባላል።

በቤተ ክርስቲያኑ ቤተ መጻሕፍትም ብዙ መጻሕፍት ይገኛሉ። በተለይም ከመጻሕፍቱ መካከል ሽፋኑ ወይም ገሉ በወርቅ የተለበሰ ወርቅ ወንጌልና የሦስት መቶ ዐስራ ስምንት ሊቃውንት ሥዕል ያለበት ሃይማኖት አበው ይገኙበታል።

መደምደሚያ ❖

የጨለቖት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የተሠራው በተደረገው ተአምራትና በተለገጸው ራዕይ መሠረት ነው። በተደረገው ተአምራት መባሉ መምህር ገብረ ሥላሴ የሁለት ቀን ሬማ ጸልየው ካስነሱ በኋላ ደጃዝማች ወልደ ሥላሴን ከእንግዲህ ወደዚህ አይምጡ በከተማዋ የሥላሴን ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ከዚያ ይጸልዩ ብለው ስለመከርዋቸው ነው።

በአሁን ጊዜ የሃገር ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መርሐ ክርስቶስ በቦታው ላይ ያሉትን በርካታ የታሪክ ቅርሶች የዝመነ መሳፍንት ታሪክና ቅርስ ዝክር እና በዚያ ዝመን ቤተ ክርስቲያን የነበራትን ሕይወት ማስታዋሻ የሆኑ ሐብቶች መጠበቂያ የሚሆን ቤተ መዘክር የማሠራት እቅድ ያላቸው ሲሆን ይኽውም ከፍተኛ ድጋፍና ማበረታቻ የሚያስፈልገው ነው። (በረከታቸው ይደርብንና ብፁዕ አባታችን ከማረፋቸው በፊት የተጻፈ ነው)

በተገለጸው ራእይ መባሉም መምህር ገብረ ሥላሴ የሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የሚሠራበት ቦታ እንዲገለጽላቸው ሱባኤ በገቡ ጊዜ በቀስተ ደመና ምልክት ቦታው ስለታያቸው ነው። (የሉሲፈርን ባለ ሁለት ቀለማት ብቻ እና ባለ አምስት ፈርጥ ኮከብ ያረፈባቸውን ባንዲራ የምትይዙ ትግራዋይን ልብ በሉ! ዋ!)በተአምራትና በራእይ እየተመሩ እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነው የሥላሴ ቤተ ክርስቲያን እንዲሠራ ጥረት ያደረጉ ሁለቱ ሰዎች ራስ ወልደ ሥላሴና መምህር ገብረ ሥላሴ በዘርፍና ባለቤት ሙያ በስመ ሥላሴ መጠራታቸው ቤተ ክርስቲያኑን ለማሠራት መመረጣቸውን ስለሚያመለክት እጅግ ያስደንቃል። ስምን መልአክ ያወጣዋል እንዳሉ (ሉቃ. ፩፥፴፩) ብለው መምህር ያሬድ የታርክ ሐተታቸውን አጠቃሏል።

✞✞✞[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፻፰]✞✞✞

፩ አምላክ ሆይ፥ ምሥጋናዬን ዝም አትበል፥

፪ የኃጢአተኛ አፍና የተንኰለኛ አፍ በላዬ ተላቅቀውብኛልና፤ በሽንገላ አንደበትም በላዬ ተናገሩ፤

፫ በጥል ቃል ከበቡኝ፥ በከንቱም ተሰለፉብኝ።

፬ በወደድኋቸው ፋንታ አጣሉኝ፥ እኔ ግን እጸልያለሁ።

፭ በመልካም ፋንታ ክፉን በወደድኋቸውም ፋንታ ጠላትነትን መለሱልኝ።

፮ በላዩ ኃጢአተኛን ሹም፤ ሰይጣንም በቀኙ ይቁም።

፯ በተምዋገተም ጊዜ ተረትቶ ይውጣ፤ ጸሎቱም ኃጢአት ትሁንበት።

፰ ዘመኖቹም ጥቂት ይሁኑ፤ ሹመቱንም ሌላ ይውሰድ።

፱ ልጆቹም ድሀ አደግ ይሁኑ፥ ሚስቱም መበለት ትሁን።

፲ ልጆቹም ተናውጠው ይቅበዝበዙ ይለምኑም፥ ከስፍራቸውም ይባረሩ።

፲፩ ባለዕዳም ያለውን ሁሉ ይበርብረው፥ እንግዶችም ድካሙን ሁሉ ይበዝብዙት።

፲፪ የሚያግዘውንም አያግኝ። ለድሀ አደግ ልጆቹም የሚራራ አይኑር።

፲፫ ልጆቹ ይጥፉ፤ በአንድ ትውልድ ስሙ ይደምሰስ።

፲፬ የአባቶቹ ኃጢአት በእግዚአብሔር ፊት ትታሰብ፤ የእናቱም ኃጢአት አትደምሰስ።

፲፭ በእግዚአብሔር ፊት ሁልጊዜ ይኑሩ፤ መታሰቢያቸው ከምድር ይጥፋ።

፲፮ ምሕረትን ያደርግ ዘንድ አላሰበምና ችግረኛንና ምስኪንን ልቡ የተሰበረውንም ሰው ይገድል ዘንድ አሳደደ።

፲፯ መርገምን ወደደ ወደ እርሱም መጣች፤ በረከትንም አልመረጠም ከእርሱም ራቀች።

፲፰ መርገምን እንደ ልብስ ለበሳት፥ እንደ ውኃም ወደ አንጀቱ፥ እንደ ቅባትም ወደ አጥንቱ ገባች።

፲፱ እንደሚለብሰው ልብስ። ሁልጊዜም እንደሚታጠቀው ትጥቅ ይሁነው።

፳ ይህ ሥራ ከእግዚአብሔር ዘንድ በሚያጣሉኝ በነፍሴም ላይ ክፉን በሚናገሩ ነው።

፳፩ አንተ ግን አቤቱ ጌታዬ፥ ስለ ስምህ ምሕረትህን በእኔ ላይ አድርግ፤ ምሕረትህ መልካም ናትና አድነኝ።

፳፪ እኔ ችግረኛ ምስኪንም ነኝና፥ ልቤም በውስጤ ደነገጠብኝ።

፳፫ እንዳለፈ ጥላ አለቅሁ፥ እንደ አንበጣም እረገፍሁ።

፳፬ ጕልበቶቼ በጾም ደከሙ፤ ሥጋዬም ቅቤ በማጣት ከሳ።

፳፭ እኔም በእነርሱ ዘንድ ለነውር ሆንሁ፤ ባዩኝ ጊዜ ራሳቸውን ነቀነቁ።

፳፮ አቤቱ አምላኬ፥ እርዳኝ፥ እንደ ምሕረትህም አድነኝ።

፳፯ አቤቱ፥ እጅህ ይህች እንደ ሆነች፥ አንተም ይህችን እንዳደረግህ ይወቁ።

፳፰ እነርሱ ይራገማሉ አንተ ግን ባርክ፤ በእኔ ላይ የሚነሡ ይፈሩ፥ ባሪያህ ግን ደስ ይበለው።

፳፱ የሚያጣሉኝ እፍረትን ይልበሱ፤ እፍረታቸውን እንደ መጐናጸፊያ ይልበሱአት።

፴ እግዚአብሔርን በአፌ እጅግ አመሰግነዋለሁ። በብዙዎችም መካከል አከብረዋለሁ፤

፴፩ ነፍሱን ከሚያሳድዱአት ያድን ዘንድ በድሀ ቀኝ ቆሞአልና።

_______________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ሥሉስ ቅዱስ የናምሩድ ባቢሎን ግንብን እንዳፈረሱት የዋቄዮ-አላህ ወረርሽኝንም ቶሎ ያጥፋልን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 15, 2022

✞✞✞ስብሃት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፡፡ አሜን፡፡✞✞✞

ጥር ፯/7-ሥሉስ ቅዱስ የባቢሎንን ግንብ ያፈረሱበት ዕለት ነው፣ በሀገራችንም ቅዳሴ ቤታቸው የከበረበት ዕለት ነው።

❖❖❖

ሥሉስ ቅዱስ፡ምሥጢራት በእምነት ለማይኖር በትሕትናም ለማይቀርብ የሚገለጡ አይደሉም፡፡ እግዚአብሔር አንድም ነው ሦስትም ነው፡፡ ጊዜ ሣይሠፈር ዘመንም ሳይቆጠር እግዚአብሔር በስም በአካል በግብር ሦስትነቱ በባሕርይ በሕልውና በመለኮትና በሥልጣን አንድነቱ የጸና አምላክ ነው፡፡ ከዓለም መፈጠር በፊት ስለ ነበረው ነገር የሚያውቅ ራሱ ሥላሴ ብቻ ነው፡፡ ዓለምን ከፈጠረ በኋላም ምሥጢረ ሥላሴ (መለኮት) ብለን የምንማረው ትምህርት እንድንና እንጠቀም ዘንድ እርሱ የገለጠልንን ያህል ብቻ ነው፡፡ ይኸውም በየጊዜው እርሱ ለወደዳቸውና ደስ ላሰኙት ቅዱሳኑ የገለጠው ምሥጢር ነው፡፡ ከዚህ አልፈን በሥጋዊ አዕምሯችን ጌታን እንመርምርህብንለው ግን ፍጻሜአችን ሞት፣ ማደሪያችንም ገሃነመ እሳት ነው፡፡

ልዑል እግዚአብሔር በአንድነቱና በሦስትነቱ ሳለ ይህንን ዓለም ፈጠረ፡፡ እግዚአብሔር ዓለምን ለምን ፈጠረ ቢሉ ስሙን ቀድሰን ክብሩን እንድንወርስ ነው፡፡ ከዚህ የተረፈውን ምክንያት እርሱ ራሱ ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡ በአንድነቱ ምንታዌ (ሁለትነት) በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት) የሌለበት የዘለዓለም አምላክ የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር ነው፡፡ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም በአካል በግብር ሦስትነት በባሕርይ በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ተገኙ፣ በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና፡፡ ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት ቅድስት ሥላሴእንላቸዋለን፡፡ የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም። የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል፣ በቤቱም መጥተው ያድራሉ፡፡ ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም፡፡ አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል፡፡ አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኳናቸው አስተናገዱ፡፡ አብርሃም እግራቸውን አጠበ፡፡ በጀርባውም አዘላቸው፡፡ ምሳቸውንም አቀረበላቸው፡፡ እነርሱም እንደሚበሉ ሆኑለት፡፡ በዚያው ዕለትም የይስሃቅን መወለድ አበሠሩት፡፡ ሥላሴን ያስተናገደች ድንኳን (ሐይመት) የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡፡ በድንግል ላይ አብ ለአጽንኦ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ ወልድ በተለየ አካሉ ለሥጋዌ በእርሷ አድረዋል፡፡ በዓለ ሥላሴ በዚህ ቀን የሚከበረው ስለ ሁለት ምክንያቶች ነው፡፡ ቀዳሚው ሕንጻ ሰናዖርን ማፍረሳቸው ሲሆን 2ኛው ደግሞ ቅዳሴ ቤታቸው ነው፡፡

ሰናዖር ከሺዎች ዓመታት በፊት በአሁኗ ኢራቅ አካባቢ እንደነበረ የሚነገርለት ግዛት ሲሆን ስሙ ለሃገሪቱም ለንጉሡም በተመሳሳይ ያገለግል ነበር፡፡ ከናምሩድ ክፋት በኋላ ሰናዖርና ወገኖቹ ከሰይጣን ተወዳጁ፡፡ ከጥፋት ውሃ (ከኖኅ ዕረፍት) በኋላ በሥፍራው በአንድነት ይኖሩ ነበርና እርስ በርሳቸው ኑ ሳንበተን ስማችን የሚጠራበትን ሕንጻ እንሥራ፣ በዚያውም አባቶቻችንን በውኃ ያጠፋ እግዚአብሔርን እንውጋውተባባሉ፡፡ ቀጥለውም ሰማይ ጠቀስ ፎቅን ገነቡ፡፡ ከሕንጻው መርዘም የተነሳ በጸሐይ አብስለው በልተዋል ይባላል፡፡ ቀጥለውም ጦር እያነሱ ፈጣሪን ሊወጉ ወርውረዋል፡፡ መቼም የእነዚህን ሰዎች ክፋትና ቂልነት ስንሰማ ይገርመን ይሆናል፡፡ ግንኮ ዛሬ ሰለጠንኩ በሚለው ዓለም እየተሠራ ያለው ከዚህ የከፋ ነው፡፡ ቸርነቱ ቢጠብቀን እንጂ እንደ ክፋታችንስ በጠፋን ነበር፡፡ ርሕሩሐን ሥላሴ ግን የሰናዖር ሰዎች የሠሩትን አይተው ማጥፋት ሲችሉ አላደረጉትም የባሪያቸውን የኖኅን ቃል ኪዳን አስበዋልና፡፡ ይልቁንም “ኑ እንውረድ ቋንቋቸው እንደባልቀው” አሉ እንጂ፡፡ በመሆኑም ከለዳውያን ልሳናቸው ተደበላልቆ 71 ቋንቋዎች ተፈጠሩ፡፡ እነርሱም ስምምነት አጥተው ተበተኑ፡፡ ሥላሴም ያን ሕንጻ በነፋስ ትቢያ አድርገው በተኑት፡፡ ስለዚህም እስከ ዛሬ ሥፍራው “ባቢሎን” ሲባል ይኖራል፡፡

😈 የአርዮስ ክህደት (Arianism): ይህ ደግሞ የወልድን ፍጹም አምላክነት የሚክድ ትምህርት ነው፡፡ ወልድ በአብ በልዕልና የተፈጠረ ነው ይላል፡፡ ፈጥሮ ፈጠረበት ይላል፡፡ አብ ወልድን ስለፈጠረው አብ ይቀድመዋል ይላል፡፡ስለዚህም ወልድ ያልነበረበት ጊዜ ነበር የሚል ክህደት ነው፡፡ ለዚህም ክህደቱ በምሳ 8፡22-25 ቆላ 1፡15 ዮሐ 14፡28 ያሉትን በተሳሳተ መንገድ በመተርጎም ተጠቅሞባቸዋል፡፡ የአርዮስ ክህደትም በኒቅያ ጉባዔ (በ325 ዓ.ም) የተወገዘ ትምህርት ነው፡፡ እኛም እንደ አባቶቻችን “ቃልም እግዚአብሔር ነበረ “የሚለውን መሠረት አድርገን “የተወለደ እንጂ ያልተፈጠረ” የሚለውን የኒቅያ ጉባዔ ድንጋጌ እንከተላለን፡፡

________________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የእግዚአብሔርን ፍጹም አንድነትና ልዩ ሦስትነት ማመን ከሁሉ ይቀድማል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 15, 2022

❖ ❖ ❖

ያለምንም ጉድለት በሥላሴ ስም ይህን ሦስትነት አምናለሁ፤ ወዳጅ መስለው ጽዮናውያንን በመጠጋት፣ እያታለሉና በየዋሕ እንግዳ ተመስለው አክሱም ጽዮንን ያጠቋትን የጽዮን ጠላቶች የሆኑትንና በጽዮን ልጆች ላይ በጣም ብዙ ግፍ ያደረሱትን የዋቄዮ-አላህ-አቴቴ አጋንንቶችን እነ ግራኝ አብዮት አህመድ አሊ እና ተከታይ አህዛብ፣ እባብ ገንዳ (አባ ገዳ) መንጋውን 😈 ሁሉ የእግዚአብሔር ቃል መቅ ያውርዳቸው፣ በተሣለ የመለኮት ሠይፍ አንገታቸውን ይረደው። አሜን! አሜን! አሜን!

✞✞✞ምስጢረ ሥላሴ፡ የእግዚአብሔርን ፍጹም አንድነትና ልዩ ሦስትነት ማመን ከሁሉ ይቀድማል✞✞✞

በዐይነ ሥጋ የማይታይና የማይመረመር፣ ሁሉን ማድረግ የሚችል፣ የሰው ህሊና አስሶ የማይደርስበት፣ ሁሉን የፈጠረ፣ መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው፣ ለዘላለም የሚኖር አምላክ መኖሩን እናምናለን፡፡ እርሱም በአካል፣ በስም፣ በግብር ሦስት፤ በባሕርይ፣ በመለኮት፣ በሕልውና፣ በፈቃድ አንድ ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር በመስጠት በመንሳት፣ በመፍጠር በማሳለፍ፣ በመግዛትና በአኗኗር አንድ ነው፡፡

ሥላሴ” የሚለው ቃል “ሠለሰ” ሦስት አደረገ ካለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ሦስትነት ማለት ነው፡፡ ቅድስት ሥላሴ ስንል ለሥላሴ ቅድስት ብለን እንቀጽላለን፡፡ ቅድስት ሥላሴ ማለት ልዩ ሦስትነት ማለት ነው፡፡ ይህም ሦስት ሲሆኑ አንድ፣ አንድ ሲሆን ሦስት ስለሚሆኑ ልዩ ሦስትነት ተብሏል፡፡ ሥላሴ የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ያለና የሚኖረውን አምላክ ለመግለጽ የተጠቀመው የአንጾኪያው ቴዎፍሎስ በ169 ዓ.ም ነው፡፡ኋላም በኒቅያ ጉባዔ 318ቱ ሊቃውንት አጽንተውታል፡፡ እነዚህ ሊቃውንት በቅዱሳት መጻሕፍት የተመሰከረውን የእግዚአብሔርን ፍጹም አንድነትና ልዩ ሦስትነት ለእኛ በሚረዳ ቋንቋ ገለጡት እንጂ አዲስ ትምህርት አላመጡም፡፡ ይልቁንም ነገረ ሥላሴን ሳይረዱ በሥላሴ መካከል የክብርና የተቀድሞ ልዩነት ያለ አስመስለው በክህደት ትምህርት የተነሱ መናፍቃንን ክህደት ለማስረዳት፣ የሐዋርያዊት ቤተክርስቲያንን የቀናች ሃይማኖት ለመግለጥ ምሥጢረ ሥላሴን አብራርተው አስተምረዋል፡፡

ምስጢረ ሥላሴ ማለት የአንድነት የሦስትነት ምስጢር ማለት ነው፡፡ ምሥጢር መባሉም በእምነት የተገለጠ፣ ያለ እምነትም የማይመረመር ስለሆነ ነው፡፡ ይኸውም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም፣ በአካል፣ በግብር ሦስት ሲሆኑ በባሕርይ በሕልውና፣ በመለኮት ደግሞ አንድ ናቸው፡፡ እንደዚህ ባለ ድንቅ ነገር አንድ ሲሆኑ ሦስት፣ ሦስት ሲሆኑ አንድ ይባላሉና፣ ይህም ልዩ ሦስትነት ረቂቅ እና በሰው አእምሮ የማይመረመር ስለሆነ ምስጢር ይባላል፡፡ ስለዚህም በአንድ አምላክ፣ በሦስቱ አካላት እናምናለን፡፡

የክርስትና ዶግማ (መሠረተ እምነት) በምስጢረ ሥላሴ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ምስጢረ ሥላሴ የእምነታችን ዋነኛው ምሰሶ ነው፡፡ በመዳን ትምህርት ውስጥ የመጀመሪያውን ደረጃ የሚይዘው ምስጢረ ሥላሴ ነው፡፡ ለመዳናችንም መሠረት ነው፡፡ ክርስቲያኖች ሁላችን የተጠመቅነው በሥላሴ (በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ) ስም ነው (ማቴ 2819)፡፡ የሥራችን ሁሉ መጀመሪያም አድርገን በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ስንልም በሥላሴ ማመናችንን እየመሰከርን ነው፡፡ በሥራችን መጨረሻም “ምስጋና ይሁን አንድ አምላክ ለሚሆን ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን” ብለን ሥራችንን በሥላሴ ስም ጀምረን በሥላሴ ስም እንፈጽማለን፡፡ሆኖም ግን ምስጢረ ሥላሴ ለሰው አእምሮ እጅግ የረቀቀ ስለሆነ የሰው አእምሮ ሊያውቅ የሚችለው እግዚአብሔር በገለጠለት መጠን ብቻ ነው፡፡

የአንድነት ምስጢር – አንድ አምላክ

ስለ ሥላሴ አንድነትና ሦስትነት ስናነሳ ቀድመን የምንመለከተው ”አንድነትን” ነው። ይህም የሆነበት ምክንያት ለአንድነታቸውና ለሦስትነታቸው መቀዳደም ኑሮበት ሳይሆን የቁጥር መሠረት አንድ ስለሆነ በዝያው ለመጀመር ነው /እንዘ አሐዱ ሠለስቱ ወእንዘ ሠለስቱ አሐዱ/፡፡ ሥላሴ ሦስት ናቸው ስንል እንደ አብርሃም፣ እንደ ይስሐቅ እንደ ያዕቆብ የተነጣጠለና በክብርም ሆነ በዘመን የሚበላለጥ የሚቀዳደም ማለታችን አይደለም፡፡ ሦስት ሲሆኑ አንድ ናቸው እንጂ፡፡ አንድ ናቸውም ስንል ከሰው ሁሉ ቀዳሚ ሆኖ እንደተፈጠረው እንደ አዳም ሦስትነትን የሚጠቀልል መቀላቀል ማለታችን አይደለም፡፡ አንድ ሲሆኑ ሦስት ናቸው እንጂ፡፡ /ቅዳሴ ማርያም/፡፡ ሥላሴ ቅድስት ተብሎ በሴት አንቀጽ መጠራታቸው ወላድያነ ዓለም (ዓለምን ያስገኙ) መሆናቸውን ለማጠየቅ ነው፤ እናት ለልጇ ስለምታዝንና ስለምትራራ ሥላሴም ለፍጥረታቸው ምሕረታቸው ዘለዓለማዊ ነውና ቅድስት ይባላሉ፡፡

ባህርይ ማለት ምንነትን የሚያሳይ ሲሆን የእግዚአብሔር ባህርይ የሚባሉትም የመለኮትነቱ ባህርያት ናቸው፡፡ አካል የምንለው ደግሞ ማንነትን የሚገልጽ ሲሆን ሦስቱ አካላት የምንላቸው የአምላክን ማንነት የሚገልጹ ናቸው፡፡ ባሕርይ ማለት “ብሕረ ተንጣለለ፥ ሰፋ፥ ዘረጋ” ከሚለው ግስ የወጣ ነው። በቲኦሎጂ /በነገረ መለኮት/ ቋንቋ ሲፈታም ባሕርይ ማለት ሥርው፥ ነቅዕ አዋሃጅ /የሚያዋሕድ/ አስተገባኢ ማለት ነው። ባሕርይ አካል ሥራውን የሚሠራበት መሣሪያ ነው። ባሕርይና አካል እንደ አጽቅና እንደ ሥር አንድ ናቸው፤ አይለያዩም፣ አንዱ ያለ አንዱ መኖር አይችልም። እግዚአብሔር በአንድነቱ የሚታወቅበት ስሞች ፈጣሪ፣ አምላክ፣ ጌታ፣ መለኮት፣ እግዚአብሔር፣ ጸባኦት፣ አዶናይ፣ ኤልሻዳይ የመሳሰሉት ናቸው፡፡ ሥላሴ በባሕርይ ረቂቅ ናቸው፡፡ ርቀታቸውስ እንዴት ነው? ቢሉ ከፍጥረት ሁሉ ነፋስ ይረቃል፡፡ ከነፋስ የሰው ነፍስ ትረቃለች፡፡ ከነፍስ መላእክት ይረቃሉ፡፡ ከነፍሳትና ከመላእክት ደግሞ ኅሊናቸው ይረቃል፡፡ ይህ የኅሊናቸው ርቀት በሥላሴ ዘንድ እንደ አምባ እንደ ተራራ ነው፡፡ በዚህም ርቀታቸው በፍጥረት ሁሉ ምሉዓን፣ ኅዱራን ናቸው፡፡ ባሕርያቸውም የማይራብ፣ የማይጠማ፣ የማይደክም፣ የማይታመም፣ የማይሞት ሕያው ነው፡፡ «ስምከ ሕያው ዘኢይመውት ትጉህ ዘኢይዴቅስ ፈጣሪ ዘኢይደክም» እንዳለ /ቅዲስ ባስልዮስ በማክሰኞ ሊጦን/፡፡

እግዚአብሔር አንድ መለኮታዊ ባህርይ፣ ዘላለማዊ የሆነ አምላክ ነው፡፡ መለኮት ማለት “መለከ – ገዛ” ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሆኖ ”ግዛት” ማለት ነው። መለኮት (ወይም ማለኹት) በዕብራይስጥ ቋንቋ መንግሥት ማለት ነው፡፡ በግዕዝ ግን ባሕርይ፣ አገዛዝ፣ ሥልጣን ማለት ነው፡፡ እንግዲህ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በመለኮት ይህም ማለት በግዛት በመንግስት አንድ ናቸው። አብ አልተፈጠረም፣ ወልድም አልተፈጠረም፣ መንፈስ ቅዱስም አልተፈጠረም፡፡ ሦስቱም አካላት ከዚህ ጀምሮ ነበሩ የማይባልላቸው ዘላለማዊ ናቸው፡፡ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ የሚለው የተለያዩ ክፍሎች ስም አይደለም የአንድ አምላክ ስም እንጂ፡፡ ሦስቱ አካላት በህልውና ተገናዝበው ይኖራሉ እንጂ አይከፋፈሉም አይነጣጠሉም፡፡ እያንዳንዳቸው አካላት በመለኮታዊ ባህርይ አንድ ናቸው፡፡ ሐዋርያው ይህንን ሲያስረዳ ‹‹ከአንዱም በቀር ማንም አምላክ እንደሌለ እናውቃለን›› በማለት ገልጾታል (1ኛ ቆሮ 84)። በአጠቃላይ ሥላሴ አንድ ሲሆኑ ሦስት፣ ሦስት ሲሆኑ አንድ ናቸው፡፡ አንድነቱ ሦስትነቱን ሳይጠቀልለው፣ ሦስትነቱ አንድነቱን ሳይከፋፍለው በሕልውና ተገናዝበው የሚኖሩ ናቸው፡፡ ሥላሴ በአካላት ሦስት ሲሆኑ በባሕርይ በመለኮት አንድ ናቸው፡፡ አንድ እግዚአብሔር፤ አንድ አምላክ ናቸው፡፡ ይህን ሲያስረዱ መጻሕፍት እንዲህ ይላሉ፤ እስራኤል ሆይ ስማ እግዚአብሔር አምላካችን አንድ እግዚአብሔር ነው፡፡ ዘጸ.6÷4 እግዚአብሔር አንድ ነው፡፡ ኤፌ. 4÷5 ሦስት ስም አንድ እግዚአብሔር ነው፡፡

ሥላሴ በሕልውና አንድ ናቸው፡፡ ሕልውና ማለት “ነዋሪነት፥ ኑሮ፥ አነዋወር” ማለት ነው። በነገረ መለኮት ቋንቋ አፈታት ግን አብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ኅልው ሆኖ፣ ወልድም በአብና በመንፈስ ቅዱስ ኅልው ሆኖ፣ መንፈስ ቅዱስም በአብና በወልድ ኀልው ሆኖ በመኖር አንድ ናቸው ማለት ነው። በሌላ አባባልም ህልውና ሦስትነታቸውን ሳይጠቀልለው፣ ሦስትነትም አንድነታቸውን ህልውናውን ሳይከፍለው አንዱ ከአንዱ ጋራ ተገናዝቦ ባንድነት መኖር ነው። ይህም በኲነት የበለጠ ይብራራል፡፡ የኩነት /የሁኔታ/ ሦስትነታቸውን በተመለከተም በህልውና /በአኗኗር/ እያገናዘቡ በአንድ መለኮት የነበሩ፣ ያሉ፣ የሚኖሩ ናቸው፡፡

የሦስትነት ምስጢር -ሦስት አካላት

ሥላሴ በግብር ሦስት ናቸው፡፡ የአብ ግብሩ መውለድ፣ ማስረጽ ሲሆን የወልድ ግብሩ መወለድ፣ የመንፈስ ቅዱስ ግብሩ መስረጽ ነው፡፡ አብ ወላዲ፣ ወልድ ተወላዲ፣ መንፈስ ቅዱስ ሠራፂ /የወጣ፣ የተገኘ/ ነው፡፡ አብ አባት ነው፣ ወልድ ልጅ ነው፣ መንፈስ ቅዱስ ከአብ ብቻ የሠረፀ ነው፡፡ /ዮሐ.14-26/፡፡ ሦስቱ አካላት አንድ መለኮት ናቸው፡፡ ሠለስቱ ስም አሐዱ እግዚአብሔር እንዳለ /አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው/፡፡ አብ ወልድን የወለደ መንፈስ ቅዱስን የሚያሰርጽ (አስገኛቸው) ነው፡፡ እንዲህ ቢሆንም ግን አይቀድማቸውም፤ አይበልጣቸውምም፡፡ መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው መጀመሪያውና መጨረሻው እርሱ የሆነ ዘላለማዊ ነው፡፡ አብ ይወልዳል እንጂ አይወለድም፣ ያሰርጻል እንጂ አይሰርጽም፡፡ አብም ‹‹ከእኛ በላይ ያለው አምላክ›› ተብሎ ይታወቃል፡፡ ወልድ የእግዚአብሔር (የአብ) ልጅ፣ ቃል ተብሎ ይጠራል፡፡ ሊቃውንትም ‹‹የአብ ክንዱ/እጁ›› ይሉታል፡፡ ቅድመ ዓለም ከአብ የተወለደ ነው፡፡ ተወለደ ሲባልም አብ ቀድሞት የነበረበት ጊዜ አለ ማለት አይደለም፡፡ ከእኛ ጋር ያለው አምላክ ይባላል፡፡ መወለዱም እንደሰው መወለድ ሳይሆን ‹‹ከብርሃን የተገኘ ብርሃን›› ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስም አምላክ ጌታ ነው፡፡ ሕይወትን የሚሰጥ አምላክ ነው፡፡ ከአብ የሠረፀ ከአብ ከወልድ ጋራ በአንድነት የምንሰግድለትና የምናመሰግነው አምላክ ነው፡፡ እርሱም በነቢያት አድሮ የተናገረ ነው። መንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ ይባላል፡፡ ሊቃውንት አባቶችም ‹‹የአብ ምክሩ›› ብለውታል፡፡ መንፈስ ቅዱስ የሚሰርጸውም ከአብ ብቻ ነው፡፡ የሚሰርጸውም ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነው አይባልለትም፡፡ ከአብ ቢሰርጽም አብ ከእርሱ ቀድሞ የነበረበት ጊዜ የለም፡፡ መንፈስ ቅዱስ ‹‹በውስጣችን ያለው አምላክ›› ይባላል፡፡

የአካል ሦስትነታቸውም ለአብ ፍጹም አካል፣ ፍጹም መልክ፣ ፍጹም ገጽ አለው፤ ለወልድም ፍጹም አካል፣ ፍጹም መልክ፣ ፍጹም ገጽ አለው፤ ለመንፈስ ቅዱስም ፍጹም አካል፣ ፍጹም መልክ፣ ፍጹም ገጽ አለው፡፡ነገር ግን አይከፋፈሉም፣ አይነጣጠሉም፣ ፍጹም አንድ ናቸው፡፡ አካል የተባለውም ምሉእ ቁመና ነው፤ ገጽ ከአንገት በላይ ያለው ፊት ነው፤ መልክዕ ልዩ ልዩ ሕዋሳት ዓይን ጆሮ፣ እጅ፣ እግር ከዚህም የቀሩት ሕዋሳት ሁሉ ናቸው፡፡ እንዲህ ሲባል ግን የሥላሴ አካል አንደ ሰው አካል ውሱን፣ ግዙፍ፣ ጠባብ አይደለም፡፡ ምሉዕ፣ ስፉሕ፣ ረቂቅ ነው እንጂ፡፡ ምሉዕነታቸውና ስፋታቸው እንዴት ነው? ቢሉ ከአርያም በላይ ቁመቱ፣ ከበርባኖስ በታች መሠረቱ፣ ከአድማስ እስከ አድማስ ስፋቱ ተብሎ አይነገርም፣ አይመረመርም፡፡ ምክንያቱም ሥላሴ ዓለሙን ይወስኑታል እንጂ ዓለሙ ሥላሴን አይወስናቸውምና፡፡

በኩነትም የአብ ከዊንነቱ ልብነት ነው፤ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ልባቸው እርሱ ነው፤ የወልድ ከዊንነቱ ቃልነት ነው፤ ለአብ ለመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው እርሱ ነው፤ የመንፈስ ቅዱስ ከዊንነቱ ሕይወትነት ነው፡፡ የአብ የወልድ ሕይወታቸው እርሱ ነው፡፡ ይህም በአብ መሠረትነት ለራሱ ለባዊ /አዋቂ/ ሆኖ ለወልድ፣ ለመንፈስ ቅዱስ ልብ፣ ዕውቀት መሆን ነው፡፡ ወልድ በአብ መሠረትነት ለራሱ ነባቢ /ቃል/ ሆኖ ለአብ፣ ለመንፈስ ቅዱስ ቃል መሆን ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስም በአብ መሠረትነት ለራሱ ሕያው ሆኖ ለአብ፣ ለወልድ ሕይወት መሆን ነው፡፡ ስለዚህ በአብ ልብነት ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ህልዋን ናቸው ያስቡበታል፤ በወልድ ቃልነት አብ፣ መንፈስ ቅዱስ ህልዋን ናቸው ይናገሩበታል፤ በመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት አብ፣ ወልድ ህልዋን ናቸው ሕያዋን ሆነው ይኖሩበታል፡፡

ሥላሴ (3ቱ አካላት) በአንድ ልብ በአብ ያውቃሉ፣ በአንድ ቃል በወልድ ይናገራሉ፣ በአንድ ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ ሕያዋን ሁነው ይኖራሉ፡፡ ጌታችን ይህን ምስጢር “እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ”፤ ሲል ለሐዋርያት አስተምሯል (ዮሐ. 1411)፡፡ ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፤ እግዚአብሔርም ቃል ነበረ፤ ይህ አስቀድሞ በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ ሲል ገልጾልናል (ዮሐ. 11-2)፡፡ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ ቃል በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ በማለቱ ወልድ በቃልነቱ በአብ ህልውና መኖሩን ያስረዳል፡፡ ይህ አስቀድሞ በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ በማለቱ በመንፈስ ቅዱስ ህልው ሆኖ መኖሩን ያስረዳል፡፡ ዮሐንስ ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ ቃልን በቃልነት በአብና በመንፈስ ቅዱስ አለ በማለቱ ሁለቱን አብ በልብነት በወልድ በመንፈስ ቅዱስ እንዳለ፤ መንፈስ ቅዱስ በሕይወትነት በአብና በወልድ እንዳለ ይታወቃል፡፡ እግዚአብሔር በሦስትነቱ የሚታወቅባቸው ስሞች ደግሞ አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ እግዚአብሔር በግብር ሦስትነቱ የሚታወቀው አብ ወላዲ፣ አሥራፂ በመባል፣ ወልድ ተወላዲ በመባል፣ መንፈስ ቅዱስ ሠራፂ በመባል ነው፡፡

የእግዚአብሔርን አንድነት የምናምነው በፈጣሪነት፣ በአምላክነት፣ በአገዛዝ፣ በፈቃድ፣ በሥልጣን እነዚህን በመሳሰሉት የመለኮት ባሕርያት ነው፡ ሦስትነቱን የምናምነው ደግሞ በስም፣ በግብር /በኩነት/ በአካል ነው፡፡ «እንዘ አሐዱ ሠለስቱ ወእንዘ ሠለስቱ አሐዱ፣ ይሤለሱ በአካላት ወይትዋሐዱ በመለኮት» እንዳለ /ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ/፡፡ ታላቁ ሐዋርያ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ 10-17 ላይ «እምነት ከመስማት ነው፣ መስማትም ከእግዚአብሔር ቃል ነው» ብሎ እንደተናገረው ከላይ የተጠቀሱትን መጠነኛ ማስረጃዎች በሙሉ ለመገንዘብ እንዲቻል የእግዚአብሔር እስትንፋስ የሆኑትን የቅዱሳት መጻሕፍት ማስረጃዎችን መመልከት ያስፈልጋል፡፡ ሥላሴ የሚለው ስም እንዲያው የመጣ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር በአንድነቱና በሦስትነቱ የሚጠራበት የከበረና ከስም ሁሉ በላይ የሆነ ስም ነው፡፡ ለዚህም የመጽሐፍ ቅዱስ /ዐሥራው ቅዱሳት መጻሕፍት/ ማስረጃዎችን በዝርዝር እንመለከታለን፡፡

ምስጢረ ሥላሴ በብሉይ ኪዳን

እግዚአብሔር ሰውን ሲፈጥር፡ እግዚአብሔርም አለ፡– «ሰውን በመልካችን እንደምሳሌአችን እንፍጠር» ዘፍ.1-26 እዚህ ላይ «እግዚአብሔርም አለ» ሲል አንድነቱ፣ «እንፍጠር» ሲል ከአንድ በላይ መሆኑን ግሱ /ቃሉ/ ያመለክታል፡፡ በዚህ ንባብ እግዚአብሔር የሚለው ሥመ አምላክ ከአንድ በላይ የሆኑ አካላትን የሚመለከት መሆኑን ከተረዳን ስለ ሥላሴ ኃልወት በሌሎች የቅዱሳት መጻሕፍት ከተጻፉት ምንባባት ጋር በማገናዘብ ይህ ጥቅስ ፍጹም አንድነቱንና ልዩ ሦስትነቱን እንደሚመሰክር በግልጽ መረዳት ይቻላል፡፡ በዚህ አንቀጽ እንፍጠር በመልካችን እንደምሳሌያችን የሚለው ንግግር የሦስት ተነጋጋሪዎች ነው እንጂ ያንድ ተናጋሪ ቃል አይደለም፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር፤ ሰውን እንፍጠር በመልካችን እንደምሳሌያችን፤ ሲል ሦስትነቱን ማስተማሩ ነው፡፡ ሙሴም ይህን የእግዚአብሔርን ነገር ሲጽፍልን ሰውን እንፍጠር በመልካችን እንደ ምሳሌያችን ያለውን የብዙውን አነጋገር ለአንድ ሰጥቶ፤ እግዚአብሔር አለ፤ ብሎ መጻፉ በአካል ሦስት ሲሆን በባሕርይ በህልውና አንድ ስለሆነ በአንድ ቃል መናገሩን ከእግዚአብሔር ተረድቶ ለእኛ ሲያስረዳን ነው፡፡

እግዚአብሔርም ለሰው ልጅ ቃል ኪዳን ሲሰጥ፡ እግዚአብሔር አምላክ አለ፡– «እነሆ አዳም መልካሙንና ክፉውን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ» ዘፍ.3-22 በማለት ባለቤቱን አንቀጽን አንድ፣ አሳቡን ዝርዝሩን የብዙ አድርጐ ይናገራል፡፡ «እግዚአብሔር አለ» ሲል አንድነቱን፣ «ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ» ሲል ደግሞ ከአንድ በላይ መሆኑን ያመለክታል፡፡ እግዚአብሔር ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ በማለቱ ሦስትነቱን ያስረዳል፡፡ ምንአልባትም እግዚአብሔር አለ፤ አዳም ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ፤ የሚለው ቃል ሦስት ተነጋጋሪዎች በአንድ ቦታ ቢኖሩ አንዱ ሁለቱን ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ ብሎ ሲነገር ከአንድ የበዙ ተናጋሪዎች ቃል መሆኑን ነው የሦስትነት ተነጋጋሪዎች መሆኑን ስለሚያስረዳ እግዚአብሔር ሦስት አካል መሆኑ በዚህ አነጋገር ግልጽ ነው፡፡

በባቢሎን ግንብ ወቅት፡ እግዚአብሔርም አለ፡– «ኑ እንውረድ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው፡፡» ዘፍ.11.6-8፡፡ «እግዚአብሔር አለ» ብሎ አንድነቱን፣ «ኑ እንውረድ» ብሎ ደግሞ ከአንድ በላይ መሆኑን ያመለክታል፡፡በዚህ አንቀጽ እግዚአብሔር ኑ እንውረድ ብሎ በመናገሩ ከሁለትነት የተለየ ሦስትነቱን ያስረዳል፡፡ መረጃውም ሦስት ተነጋጋሪዎች በአንድ ቦታ ሁነው ሲነጋገሩ ሦስተኛው ሁለቱን ኑ እንውረድ ሊላቸው ይችላል፤ ምክንያቱም ሁለት ሆነው ግን አንዱ ሁለተኛውን ና እንውረድ ቢለው እንጂ ኑ እንውረድ ሊለው ስለማይችል ነው፡፡ ከዚህ በላይ የተጠቀሱት የእግዚአብሔር ቃላት ተገልጸው ሲተረጐሙ፤ አካላዊ ልባቸው አብ አካላዊ ቃሉ ወልድንና አካላዊ ሕይወቱ (እስትንፋሱ) መንፈስ ቅዱስን፤ ሰውን እንፍጠር በመልካችን እንደ ምሳሌያችን፤ እነሆ አዳም ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ፤ እንዲሁም ኑ እንውረድ፤ ብሎ እንዳነጋገራቸው ይታወቃል፡፡

ለአብርሃም በተገለጠለት ጊዜ፡ የአንድነቱና የሦስትነቱ ማስረጃ ሁነው የታመኑ እነዚህ ሦስቱ ቃላት ከአንድ የበዙ የሁለት ተነጋጋሪዎች፤ ከሁለትም የበዙ ተነጋጋሪዎች ቃላት መሆናቸው ይታወቃል እንጂ ከሦስት ያልበለጡ የሦስት ብቻ ተነጋጋሪዎች ቃላት እንደ ሆኑ ቃላቶቹ በማያሻማ ሁኔታ ስለማያስረዱ፤ እግዚአብሔር በእነዚህ አነጋገሮች ከሦስት ያልበዛ ሦስት አካላት ብቻ መሆኑ አይታወቅም የሚል አሳብም ቢነሳ፤ መጽሐፍ ቅዱስ ከዚህም በሌላ አንቀጽ ይመልሳል፡፡ «በቀትርም ጊዜ እግዚአብሔር ለአብርሃም ተገለጠለት አብርሃም ሦስት ሰዎችን በፊቱ ቆመው አየ» ዘፍ.18.1-15 በማለት እግዚአብሔር አንድ መሆኑንና ሦስት አካል ያለው መሆኑን ወስኖ ያስረዳናል፡፡

የነቢያት ምስክርነት፡ እግዚአብሔር ለሙሴ በተገለጠለት ጊዜ «እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅም አምላክ፣ የያዕቆብም አምላክ እግዚአብሔር ነኝ» ዘጸ.3-6 ሲል «አምላክ፣ አምላክ፣ አምላክ» ብሎ ሦስትነቱን፣ «እኔ እግዚአብሔር ነኝ» ብሎ ደግሞ አንድነቱን ገልጾ ተናግሯል፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ክቡር ዳዊትም «የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች፣ በእግዚአብሔርም ቃል ሰማዮች ጸኑ፣ ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ» በማለት የሥላሴን ምስጢር ተናግሯል (መዝ.32-6)፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስም «ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት እግዚአብሔርን በልዑል ዙፋኑ ላይ ተቀምጦ አየሁት… ሱራፌልም ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያሉ ይጨሁ ነበር፡፡» ኢሳ.6.1-8 በማለት ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ ብሎ ሦስትነቱን፣ የሠራዊት ጌታ እግዚአበሔር ብሎ ደግሞ አንድነቱን አይቶ መስክሯል፡፡ እንዲሁም “የጌታንም ድምፅ ‘ማንን እልካለሁ? ማንስ ወደዚያ ሕዝብ ይሄድልናል’ ሲል ሰማሁ” (ኢሳ. 6፡8) በማለት ፍጹም አንድነቱንና ልዩ ሦስትነቱን አመልክቷል፡፡ የእግዚአብሔር ቀራቢዎች አገልጋዮች ሱራፌል በምስጋናቸው ሦስት ጊዜ ብቻ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ማለታቸው የሦስትነቱን አካላት መጥራታቸው ነው፤ እግዚአብሔር የሠራዊት ጌታ በማለት በአንድ ስም ጠርተው ምድር ሁሉ ምስጋናህን መልታለች በማለት ያንድ ተመስጋኝ ምስጋናን መስጠታቸው ሦስቱ አካላት አንድ ሕያው እግዚአብሔር፤ አንድ ገዥ፤አንድ አምላክ፤ አንድ ተመስጋኝ አምላክ መሆኑን መመስከራቸው ነው፡፡ ሱራፌልም በዚህ ምስጋናቸው እግዚአብሔር በአካል ከሦስትነት ያልበዛ ሦስት ብቻ እንደ ሆነ በባሕርይ በህልውና ከአንድነት ያልበዛ ሦስት አካል አንድ አምላክ ብቻ መሆኑን ይመሰክሩልናል፡፡

ምስጢረ ሥላሴ በሐዲስ ኪዳን

በሐዲስ ኪዳንም የእግዚአብሔር አንድነትና ሦስትነት /ምስጢረ ሥላሴ/ በምስጢረ ሥጋዌ (በጌታችን በተዋህዶ ሰው መሆን) በሚገባ ታውቋል፡፡

በብስራት ጊዜ፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም እመቤታችንን ባበሠራት ጊዜ «መንፈስ ቅዱስ በአንች ላይ ይመጣለ፣ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንች የሚለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል፡፡» ብሎ የሥላሴን ሦስትነት በግልጽ ተናግሯል፡፡ሉቃ.1-35፡፡

በጥምቀት ጊዜ፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተለየ አካሉ /ሰው ሆኖ/ በዮርዳኖስ ሲጠመቅ፣ አብ በደመና ሆኖ «የምወደው ልጄ ይህ ነው የሚላችሁን ስሙት» ሲል፣ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ በራሱ ላይ በርግብ አምሳል ሲወድቅበት ታይቶአል፡፡ /ማቴ.3.16-17፣ ማር.1.9-11፣ ሉቃ.3.21-22፣ ሉቃ.1.32-34/ በዚህም እግዚአብሔር በአካል ሦስት እንደሆነ ተገልጿል፡፡

በደብረ ታቦር፡ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን በገለፀበት በደብረ ታቦር ተራራም ምስጢረ ሥላሴ ተገልጿል፡፡ ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋን ተዋህዶ በደብረ ታቦር ተገኝቶ፣ አብ በሰማያት ሆኖ “በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ እርሱ ነው፤ እርሱን ስሙት” የሚል ቃል ተናግሮ፣ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ በደመና ጋርዷቸው ተለግጠዋል፡፡ (ማቴ 171-10)

ሐዋርያዊ ተልዕኮ ሲሠጥ፡ እራሱ ባለቤቱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የማዳን ሥራውን ፈጽሞ ከማረጉ በፊት ለደቀመዛሙርቱ ቋሚ ትዕዛዝ ሲሰጥ «እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ደቀመዛሙርት አድርጓቸው» ብሏል ማቴ.28.19-20፡፡ በዚህም ‹‹ስም›› ብሎ አንድነታቸውን ‹‹አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ›› ብሎ ሦስትነታቸውን ገልጿል፡፡ ስለመንፈስ ቅዱስም ሲናገር «ዳሩ ግን እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ እርሱ ስለ እኔ ይመሰክራል፡፡» በማለት አንድነትና ሦስትነቱን በግልፅ ተናግሯል (ዮሐ.15.2614.16-1725-26)፡፡

በሐዋርያት አንደበት፡ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች በጻፈው መልእክቱ የሥላሴን ሦስትነት ገልጾ «የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ የእግዚአብሔርም ፍቅር፣ የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን» (2ኛ ቆሮ.13-14) በማለት ተናግሮአል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ በጻፈው መልእክቱ በማያሻማ ሁኔታ «በሰማይ የሚመሰክሩ ሦስት ናቸው፡፡ እነርሱም አብ፣ ልጁም፣ መንፈስ ቅዱስም ናቸው፡፡ 1.ዮሐ.5-7፡፡ እነዚህ ሦስቱም አንድ ናቸው፡፡» በማለት የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት በግልጽ ያስረዳናል፡፡ ወንጌላዊው ቅድስ ዮሐንስም «በራእዩ እነሆም በጉ በጽዮን ተራራ ቆሞ ነበር፣ ከእርሱም ጋር ስሙና የአባቱም ስም የመንፈስ ቅዱስም ስም በግምባራቸው የተጻፈላቸው መቶ አርባ አራት ሺህ ነበሩ» ራእ.14-1፡፡ በማለት በገጸልቡናቸው ስመ ወላዲ፣ ስመ ተወላዲና ስመ ሠራፂ የተጻፈባቸውን የሥላሴን ልጆች አይቷል፡፡ በዚህም የሥላሴን ልዩ ሦስትነት በግልጽ መስክሯል፡፡ ከላይ በዝርዝር የተገለጹትና እነዚህን የመሳሰሉት ሁሉ እግዚአብሔር አንድነቱንና ሦስትነቱን የገለጸባቸው ምስክሮች ናቸው፡፡

የምስጢረ ሥላሴ አስረጂ ምሳሌዎች

ምስጢረ ሥላሴ በሊቃውንትም ትምህርት የአብ ወላዲነት፣ የወልድ ተወላዲነትና የመንፈስ ቅዱስ ሠራፂነት ነው፡፡ አብ ተወላዲ አይባልም፣ ወልድ ወላዲ አይባልም፡፡ ወላዲ፣ ተወላዲ፣ ሠራፂ የሚባሉት ቃላት ሦስት አካላት ለየብቻ የሚታወቁባቸው የግብር ስሞች ናቸው፡፡ ሊቃውንት አባቶቻችን በሃይማኖተ አበው ምሳሌ ሲመስሉ ምሳሌ ዘይሐጽጽ /ጎደሎ ምሳሌ/ በማለት አንዳንድ ምሳሌዎችን ያቀርባሉ፡፡ ምሳሌውንም ጎደሎ የሚሉበት ምክንያት ለምስጢረ ሥላሴ ሙሉ በሙሉ ምሳሌ የሚሆን ሲያጡ ነው፡፡ ይሁንና ምሳሌ ከሚመሰልለት ነገር እንደሚያንስ ቢታወቅም ለማስተማር ግን ይጠቅማልና ቤተክርስቲያን ነገረ ሃይማኖትን በምሳሌ ታስረዳለች፡፡ ይህንንም የሥላሴን ሦስትነትና አንድነት ሐዋርያት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ በተማሩት መሠረት በሚከተሉት ሦስት ምስሌዎች በሚገባ ገልጸውታል፡፡

የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በሰው ምሳሌ ይገለጻል፡፡ ሰው በነፍሱ ሦስትነት አለው፡፡ የኸውም ልብነት፣ ቃልነት፣ ሕይወትነት ነው፡፡ ስለዚህ በሰው ነፍስ በልብነቷ አብ፣ በቃልነቷ ወልድ፣ በሕይወትነቷ መንፈስ ቅዱስ ይመስላሉ፡፡ የነፍስ ልብነቷ፣ ቃልነቷን፣ ሕይወትነቷን ከራሷ ታስገኛለችና፡፡ ቃልና ሕይወት ከአንዷ ልብ ስለተገኙ በከዊን /በመሆን/ ልዩ እንደሆኑ በመናገርም ይለያሉ፡፡ እንዲሁም አብ ወልድን በቃል አምሳል ወለደው፣ መንፈስ ቅዱስንም በእስትንፋስ አንጻር አሰረጸው፡፡ ነፋስ ስትገኝ በሦስትነቷ በአንድ ጊዜ ተገኘች አንዷ ልብነቷ ቀድሞ ቃልነቷና እስትንፋስነቷ በኋላ አልተገኙም፡፡ ሰው በዚህ አኳኋን በነፍሱ የሚመስለው ስለሆነ እግዚአብሔር «ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር» ዘፍ.1-26 ብሎ ተናገረ፡፡ ስለዚህ ነፍስ ልብ፣ ቃል፣ እስትንፋስ /ሕይወት/ መሆን የከዊን /የመሆን/ ሦስትነትን ነገር በተናገረበት ድርሳን እንዲህ አለ፡፡ «አምላክ ውእቱ አብ፣ ወአምላክ ውእቱ ወልድ፣ ወአምላክ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ወኢትበሀሉ ሠለስተ አማልእክተ አላ አሐዱ አምላክ ብሏል፡፡ ይህም ማለት አብ አምላክ ነው፣ ወልድም አምላክ ነው፣ መንፈስ ቅዱስም አምላክ ነው ነገር ግን ሦስት አማልክት አይባሉም፣ አንድ አምላክ እንጂ፡፡» ማለት ነው፡፡

የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በፀሐይ ይመሰላል፡፡ ፀሐይ አንድ ሲሆን ሦስትነት አለው፡፡ ይኼውም ክበቡ ብርሃኑ፣ ሙቀቱ ነው፡፡ በክበቡ አብ፣ በብርሃኑ ወልድ፣ በሙቀቱ መንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉ፡፡ «አብ ፀሐይ፣ ወልድ ፀሐይ፣ መንፈስ ቅዱስ ፀሐይ አሐዱ ውእቱ ፀሐየ ጽድቅ ዘላዕለ ኩሉ» እንዳለ /ቅዱስ አባ ሕርያቆስ/፡፡ እነዚህ ሦስቱ በአንድ ላይ መኖራቸው አንድ ፀሐይ እንጂ ሦስት ፀሐዮች አያስብላትም፡፡ ከፀሐይ ክበብ ብርሃኗና ሙቀቷ ያለመቀዳደም እንደሚገኝ እንዲሁ ከአብ ወልድ ተወለደ፣ መንፈስ ቅዱስም ሰረጸ፤ ይህም ያለመቀዳደም ያለመበላለጥ ነው፡፡ ከፀሐይ ሦስት ኩነታት ብርሃኗ ብቻ ከዓይናችን ጋር እንደሚዋሀድ ከሥላሴም ብርሃን ዘበአማን (እውነተኛ ብርሃን) የተባለ ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ በተለየ አካሉ የሰውን ባህርይ ተዋህዷል፡፡

የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በእሳት ይመሰላል፡፡ እሳት አንድ ሲሆን ሦስትነት አለው፡፡ ይኼውም አካሉ፣ ብርሃኑ፣ ዋዕዩ /ሙቀቱ/ ነው፡፡ በአካሉ አብ፣ በብርሃኑ ወልድ፣ በዋዕዩ መንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉ፡፡ «አብ እሳት ወልድ እሳት ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ እሳተ ሕይወት ዘእምአርያም፡፡» እንዳለ /አባ ሕርያቆስ/ «አምላክህ እግዚአብሔር የሚባላ እሳት ቀናተኛም አምላክ ነው፡፡» ዘዳ. 4-24፡፡ሥላሴ በፀሐይና በእሳት መመሰላቸውንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ለሐዋርያት «እኔና አባቴ መንፈስ ቅዱስም እሳትና ነበልባል ፍሕምም ነን» በማለት አስተምሮአቸዋል፡፡ ሐዋርያትም ይህንን ጽፈውት ቀሌመንጦስ በተባለው መጽሐፍ ይገኛል፡፡ /ቅዳሴ ሠለስቱ ምእትን/ ይመልከቱ፡፡

የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በባህር ከዊን ይመሰላል፡፡ ባህር አንድ ባህር ሲሆን ሦስት ከዊን አለው፡፡ ይህም ስፍሐት (Sphere)፣ ርጥበት (Moisture) እና እንቅስቃሴ (Tide) ነው፡፡ በስፍሐቱ አብ፣ በርጥበቱ ወልድ፣ በእንቅስቃሴው መንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉ፡፡ ሰው ከባህር ገብቶ ዋኝቶ ሲወጣ በአካሉ ላይ ርጥበት ይገኛል እንጂ ስፍሐትና እንቅስቀሴ አይገኝም፡፡ ወልድም በቃልነቱ ከዊን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ በተለየ አካሉ ሰው በሆነ ጊዜ በመለኮት አንድ ስለሆነ አብና መንፈስ ቅዱስ ሥጋ ለበሱ አያሰኝም፡፡ ሊቃውንትም ‹‹የሁሉ መገኛ አብን ነፋስ በሚያማታት ባህር ባለች ውኃ እንደመሰሉት እወቅ፡፡ በሁሉ ዘንድ የሚመሰገን ወልድንም በውኃ ርጥበት እንደመሰሉት በሁሉ ዘንድ የሚመሰገን መንፈስ ቅዱስንም በውኃ ባለ ባህር እንቅስቃሴ ይመሰላል›› በማለት አስረድተዋል፡፡

ነገር ግን እነዚህ ሁሉ አንድ ነፍስ፣ አንድ ፀሐይ፣ አንድ እሳት፣ አንድ ባህር እንጂ ሦስት ነፍስ፣ ሦስት እሳት፣ ሦስት ፀሐይ፣ ሦሰት ባህር አይባሉም፡፡ ሥላሴም በአካል፣ በስም፣ በግብር ሦስት ቢባሉ በባሕርይ፣ በሕልውና፣ በፈቃድ፣ በመለኮት አንድ ናቸው አንጂ አማልክት አይባሉም፡፡ የቂሣርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ባስልዮስ «እንዘ አሐዱ ሠለስቱ ወእንዘ ሠለስቱ አሐዱ ይሤለሱ በአካላት ወይትዋሐዱ በመለኮት» እንዳለ፡፡ ይህም ማለት አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ሲሆኑ ሦስት ሦስት ሲሆኑ አንድ ናቸው፡፡ በአካል ሦስት ሲሆኑ በመለኮት አንድ ናቸው፡፡ ማለት ነው፡፡ ይህም ሰው በሚረዳው መጠን ለመግለጽ ያህል ነው እንጂ ከፍጥረት ወገን ለሥላሴ የሚሆን በቂ ምሳሌ የለም፡፡ የተመሰለ ቢመስል ሕጹጽ /ጎደሎ/ ምሳሌ ነው፡፡

😈 ምስጢረ ሥላሴ ላይ የሚነሱ የስህተት ትምህርቶች

መለዋወጥ (Modalism): ይህ ስህተት የሰባልዮሳውያን ነው፡፡ ስህተቱም አንድ እግዚአብሔር አለ በማለት የአካል ሦስትነትን አይቀበልም፡፡ በዚያ ፈንታ አንዱ እግዚአብሔር ራሱን በተለያየ መንገድ ይገልጻል በማለት ይናገራል፡፡ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ የሚባሉት አካላት ሳይሆኑ ራሱን የገለጠባቸው መንገዶች ናቸው ይላል፡፡ ስለዚህም እግዚአብሔር አንድ ጊዜ አብ፣ ሌላ ጊዜ ወልድ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ መንፈስ ቅዱስ ሆኖ ተገለጠ በማለት የሥላሴን ምስጢር አዛብቶ ያቀርባል፡፡ ምሳሌም ሲሰጥ ይህም ውኃ ፈሳሽ፣ በረዶ፣ እንፋሎት እንደሚሆነው ነው በማለት ያቀርባል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር በባህርይው አይለወጥምና (ሚል 3፡6) ይህ የተወገዘ የስህተት ትምህርት ነው፡፡

መነጣጠል (Tri-theism):ይህ ስህተት የሥላሴን አንድነት ካለመረዳት የሚመጣ ነው፡፡ አመለካከቱም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ሦስት አማልክት ናቸው ይላል፡፡ ልዩ በሆነ መንገድ የተጣመሩ አማልክት ናቸው በማለትም ኅብረት አላቸው ይላል፡፡ ይህ ስህተት ሦስት አካላት የሚለውን በትክክል ባለመረዳት አንዳንዶች ‹‹ክርስቲያኖች ሦስት አማልክት ያመልካሉ›› የሚሉት አይነት ስህተት ነው፡፡ ነገር ግን ሥላሴ የተለያዩ/የተነጣጠሉ/ አይደሉም፡፡ ሊቃውንት አባቶችም ‹‹አንድ አምላክ እንጂ ሦስት አማልክት አንልም›› ብለው በግልጽ መልስ ሰጥተውበታል፡፡

መከፋፈል (Partialism): ይህ ስህተት ደግሞ አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ አንድ ላይ ሲሆኑ አምላክ ይሆናሉ ይላል፡፡ ይህም ማለት እያንዳንዳቸው የአምላክ ክፍል ናቸው እንጂ ሙሉ አምላክ አይደሉም የሚል ትርጉም አለው፡፡ ሦስቱ በአንድ ላይ ሲሆኑ ብቻ ሙሉ አምላክ ይሆናሉ ማለትም እያንዳንዳቸው አካላት አምላክ ሳይሆኑ ‹‹የአምላክ ክፍል›› ናቸው የሚል ፍጹም የክህደት ትምህርት ነው፡፡ እኛ ግን ሥላሴ ግን አይከፋፈሉም እንላለን፡፡ቅዱስ አትናቴዎስ እንደተናገረውም ‹‹“አብ አምላክ ነው፣ ወልድም አምላክ ነው፤ መንፈስ ቅዱስም አምላክ ነው፡፡››

የአርዮስ ክህደት (Arianism): ይህ ደግሞ የወልድን ፍጹም አምላክነት የሚክድ ትምህርት ነው፡፡ ወልድ በአብ በልዕልና የተፈጠረ ነው ይላል፡፡ ፈጥሮ ፈጠረበት ይላል፡፡ አብ ወልድን ስለፈጠረው አብ ይቀድመዋል ይላል፡፡ስለዚህም ወልድ ያልነበረበት ጊዜ ነበር የሚል ክህደት ነው፡፡ ለዚህም ክህደቱ በምሳ 8፡22-25 ቆላ 1፡15 ዮሐ 14፡28 ያሉትን በተሳሳተ መንገድ በመተርጎም ተጠቅሞባቸዋል፡፡ የአርዮስ ክህደትም በኒቅያ ጉባዔ (በ325 ዓ.ም) የተወገዘ ትምህርት ነው፡፡ እኛም እንደ አባቶቻችን ‹‹ቃልም እግዚአብሔር ነበረ›› የሚለውን መሠረት አድርገን ‹‹የተወለደ እንጂ ያልተፈጠረ›› የሚለውን የኒቅያ ጉባዔ ድንጋጌ እንከተላለን፡፡

የመቅዶንዮስ ክህደት (Mecedonianism): የመቅዶንዮስ ክህደት ከአርዮስ ክህደት የቀጠለ ሲሆን የመንፈስ ቅዱስን ፍጹም አምላክነት የካደ ትምህርት ነው፡፡ ክህደቱም መንፈስ ቅዱስ ፍጡር (ሕፁፅ) ነው ይላል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ያንሳል ይላል፡፡ እኛ ግን በሦስቱ አካላት መበላለጥ የለም ብለን እናምናለን፡፡ የመቅዶንዮስ ትምህርት በቁስጥንጥንያ ጉባዔ (381 ዓ.ም) የተወገዘ ትምህርት ነው፡፡ የቀናችውን ሃይማኖት ያስተማሩ አባቶችም በዚህ ጉባዔ ‹‹በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን፤ እርሱ ጌታ ሕይወትን የሚሠጥ ከአብ የሰረፀ ከአብና ከወልድ ጋር እንሰግድለታለን፤ እናመሰግነለዋለን፤ እርሱም በነቢያት አድሮ የተናገረ ነው›› በማለት የመንፈስ ቅዱስን አምላክነት በተረዳ ነገር መስክረዋል፡፡

የሁለት ሥርፀት ትምህርት (Dual procession): ይህ የስህተት ትምህርት ቆይቶ በምዕራባውያኑ ዘንድ የተጨመረ ነው፡፡ እርሱም መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ይሰርፃል የሚል የስህተት ትምህርት ነው፡፡ የኒቅያ ጉባዔ ድንጋጌ ላይ ከጊዜ በኋላ የተጨመረ ነው፡፡ በጥንታዊያን አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ያልነበረ ምዕራባዊያኑ ያስገቡት ነው፡፡ መሠረታዊ ነገሩም ከምስጢረ ሥላሴ ጋር ይጣረሳል፡፡ ጌታችንም ያስተማረው መንፈስ ቅዱስ ከአብ እንደሚሰርፅ እንጂ ከአብና ከወልድ እንደሚሰርፅ አይደለም፡፡

ስለ ምሥጢረ ሥላሴ ከቀደሙ ሊቃውንት ምስክርነቶች ጥቂቶቹ

እግዚአብሔር አንድ ነው፤ የማትከፈል የማትፋለስ መንግስትም አንዲት ናት፤ ከሥላሴ ምንም ምን ፍጡር ደኃራዊ የለም፤ በእነርሱ ዘንድ አንዱ ለአንዱ መገዛት የለም፡፡ አብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፣ ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፤ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፤ ሥሉስ ቅዱስ በዘመኑ በቀኑ ሁሉ በግብርም በስምም ሳይለወጥ ሳይፋለስ ጸንቶ ያለ ነው እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘሠለስቱ ምዕት ምዕራፍ 195-6)

ወንድሞቻችን እኛስ እንዲህ እናምናለን፤ ያልተወለደ እግዚአብሔር አብ በተለየ አካሉ አንድ ነው፤ የተወለደ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኢየሱስ ክርስቶስም በተለየ አካሉ አንድ ነው፤ በወደደው የሚያድር የአብ የወልድ እስትንፋስ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም በተለየ አካሉ አንድ ነው እንላለን፡፡…አብ አምላክ ነው፤ ወልድም አምላክ ነው፤ መንፈስ ቅዱስም አምላክ ነው፡፡ ግን ሦስት አማልክት አይባሉም አንድ አምላክ እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ምዕራፍ 252-4)

ከሦስቱ ፍጡር የለም ፍጡራን አይደሉምና፡፡ ከዕውቀት ከሃይማኖት የተለዩ መናፍቃን ከቅድስት ሥላሴ መለኮት መከፈልን በአካላት መጠቅለልን ሊያመጡ አይድፈሩ ሦስት አማልክት ብለን አንሰግድም አንድ አምላክ ብለን እንሰግዳለን እንጂ፡፡ በስም ሦስት ናቸው እንላለን፤ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ባህርይ አንድ ሥልጣን ናቸው፤ በአንድ መለኮት በባህርይ አንድነት የጸኑ ሦስት አካላት ሲሆኑ ከሦስቱ አንዱ የሚበልጥ አንዱ የሚያንስ አይደለም፤ በማይመረመር በአንድ ክብር የተካከሉ ናቸው እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ምዕራፍ 606-7)

ወልድ ሳይኖር አብ ከአዝማን በዘመን ፈጽሞ አልነበረም፤ ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ በዘመን አልነበረም፤ ሳይለወጡ ሳይለዋወጡ በገጽ በመልክ ፍጹማን በሚሆኑ በሦስት አካላት ጥንት ሳይኖራቸው በዘመን ሁሉ የነበሩ፤ ፍጻሜ ሳይኖራቸው የሚኖሩ ናቸው እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎፍሎስ ምዕራፍ 685)

አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በአካል ሦስት በባህርይ አንድ ነው ብሎ ማመን ይህ ነው፤ የማይመረመር በቅድምና የነበረ አብ በገጹ በአካሉ ፍጹም ነው፤…የማይመረመር በቅድምና ነበረ ወልድም በገጹ በአካሉ ፍጹም ነው፤….የማይመረመር በቅድምና የነበረ መንፈስ ቅዱስም በገጹ በአካሉ ፍጹም ነው፤ ሐዋርያት ያስተማሩዋት ቅድስት ቤተክርስቲያን የተቀበለቻቸው ቅዱሳት መጻሕፍት እንደተናገሩ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቄርሎስ ምዕራፍ 7014-17)

እኛ ግን በሥላሴ ዘንድ በማዕረግ ማነሥና መብለጥ የለም በመለኮት አንድ ወገን ናቸው እንላለን” (አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ተግሳጽ ዘሰባልዮስ)

ማጠቃለያ

ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምስጢረ ሥላሴን በተረዳ ነገር ‹‹ሥላሴ አንድ ሲሆኑ ሦስት፣ ሦስት ሲሆኑ አንድ ናቸው፡፡ አንድነቱ ሦስትነቱን ሳይጠቀልለው፣ ሦስትነቱ አንድነቱን ሳይከፋፍለው በሕልውና ተገናዝበው የሚኖሩ ናቸው፡፡›› ብላ ታምናለች፤ ታስተምራለችም፡፡ ይህም እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ራሱን የገለጠበት፣ ነቢያት የመሰከሩት፣ ወልደ እግዚአብሔር በተለየ አካሉ ሰው ሆኖ ያስተማረው፣ ሐዋርያትም በዓለም ዞረው የሰበኩት ምስጢር ነው፡፡ ስለዚህ እኛም እንደ አባቶቻችን “ምንም እንኳን ሥላሴን በስም፣ በአካል በግብር ሦስት ናቸው ብንልም ሦስቱ በባህርይ፣ በመለኮት፣ በህልውና፣ በፈቃድ አንድ ናቸው፡፡ አንድ አምላክ እንጂ ሦስት አማልክት አንልም፡፡ አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ አላቸው፡፡ ነገር ግን በህልውና አንድ ናቸው፡፡” ብለን እናምናለን፤ እንታመናለን፡፡

ስብሃት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፡፡ አሜን፡፡

________________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

አባ ገዳ፤ ከእንግዲህ ሰሜናውያን “የኦሮሞን ምድር” በጭራሽ አይረግጧትም

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 15, 2022

💭 ይህ አባገዳየሚባል ተልካሻ፣ ሰነፍ፣ ምንም በጎ ነገር ለራሱም ለመላዋ ኢትዮጵያም አብርክቶ የማያውቅ ስራ ፈት ፣ ያረጀና ጥገኛ የዘላን ጥርቅም በራሱ ጎሳ ውስጥ ያለን ቀውስ በባሌና ወለጋ መፍታት እንኳን ያልቻለ ያልተማረ የጠላና የጠጅ ቤት ኦሮሞ መሪ ቡድን ነው።

በእነዚህ እባብ ገንዳዎች የሚመራው ኦሮሞ/ጋላ ነበር ሃያ ሰባት ጥንታውያኑን የኢትዮጵያ ነገዶች ከምድረ ገጽ ያጠፋው፤ ዛሬም ሰሜናውያን ወንድማቾችን እርስበርስ እያባላና እያዳከመ ዲያብሎሳዊ የወረራና የዘር ማጥፋት ተልዕኮውን ለማሟላት ተግቶ በመሥራት ላይ ይገኛል፤ ግን ጽዮናውያንን ለመድፈር በመሻቱ የራሱን መውደቂያ ጉድጓድ ነው በመቆፈር ላይ ያለው፤ እግዚአብሔር በቅርቡ እሳቱን እንደሚያወርድባቸው ምንም ጥርጥር የለኝም። የማይወራለትና እጅግ በጣም ብዙ የሠሩት ወንጀልና ግፍ አለና።

በእነዚህ እባብ ገንዳዎች የሚመራው ኦሮሞ ከአምስት መቶ ዓመታት በፊት ከክርስቶስ ተቃዋሚ ቱርክ ጋር አብሮ ሕዝበ ክርስቲያኑን ጨፈጨፈ፤ በማይገባው ግዛት እንደር ግራር ተስፋፋ፤ አሁን አክሱም ጽዮንን በድጋሚ በመድፈሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከሃገረ ኢትዮጵያ በእሳት ይጠራረጋል።

እስኪ እናስበው፤ ይህ “በቃኝ! ተመስገን!“ የማይል ምስጋናቢስ የእባብ ገንዳዎች መንጋ ግማሽ የኢትዮጵያን ግዛት ቆርሶ የሰጠውን የትግራይን ሕዝብ እያስራበና እየጨፈጨፈ ነው። በአርሜኒያውያን ወገኖቻችን ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈጸመውንና የፋሺስቶቹን “ወጣት ቱርኮች/ Young Turks ፈለግ የተከተለው ቄሮ የተጋሩ ደም ደሜ ነው!” ብሎ የፋሺስቱን ኦሮሞ አገዛዝ ለመቃወም ሰልፍ ሲወጣ አይተናልን? በጭራሽ! አያደርገውምም። ላለፉት መቶ ሃምሳ ዓመታት መጀመሪያ በኦሮሞው ምኒልክ፣ በጣይቱ፣ በኃይለ ሥላሴ፣ በመንግስቱ ኃይለ ማርያም፤ ዛሬ በዳግማዊ ግራኝ አብዮት አህመድ አሊ አገዛዝ(ሁሉም የአማራውን ባትሪ የሚጠቀሙ የኦሮሞ አገዛዞች ናቸው)የትግራይን ሕዝብ እያስርቡ፣ እያፈናቅሉ፣ እያሳድዱ፣ እየጨፈጭፉና በረሃብ እየቆሉ እስከዚህ እስከ መጨረሻው ዘመናቸው ድረስ ዘልቀዋል። አዎ! ዛሬም የትግራይን ሕዝብ ከምንግዜውም በከፋ እያሰቃየው ያለው አረመኔው ኦሮሞ ነው! የትግራይ ሕዝብ እየተራበ ነው፤ እያለቀ ነው! ለዚህ ደግሞ ቍ. ፩ ተጠያቂው ኦሮሞ ነው! የዛሬ ዓመት ወደ መቀሌ የተላኩትን እባብ ገንዳዎች (አባ ገዳ) እናስታውሳለን? ያው ዓላማቸውንና ፍላጎታቸውን በግልጽ አሳይተውናል! ግራኝም እኮ በግልጽ፤ “ተደመሩአልያቅብርጥሴ ብለናቸው ነበር” ብሎናል።

😈 እነዚህ አርመኔዎች እኮ እንዲህ ሲሉ በግልጽ ነግረውናል፤

የትግራይን ሕዝብ ከምድረ ገጽ ማጥፋት አለብን፤ እኛ በሕዝብ ቁጥር ብዙ ስለሆንን አንድ ሚሊየንም ሰው ቢሆን መስዋዕት አድርገን ትክክለኛ ኢትዮጵያውያን የሆኑትን ጽዮናውያንን ሙሉ በሙሉ ማጥፋት እንችላለን፣ እኛ ከዛ እንደለመድነው ሦስት አራት ሚስት አግብተን የተሰውትን የአባ ገዳ ልጆች እንተካቸዋለን፤ ኦሮሞዎች እኮ ነን፤ አሁን ለኦሮሞ ሕዝቤ ስል ኢትዮጵያን ማጥፋት አለበኝ፣ ኦሮሞ እስኪነቃ ነው እንጂ፣ እስኪነሳ ነው እንጂ ሲነሳ ሚዳቋ አትበላንም፤ እኛ ዝሆን ነን፤ እንሰብራለን፤ እንበላለን፤ እንገዛለን፣ ሃሳብ አለን፤ ድርጅት አለን፤ ከአለም ጋር (ከኤዶማውያኑ እና እስማኤላውያኑ ጋር)ግንኙነት አለን።”

እባብ ገንዳዎቹ ይህን ተከትለውነው ታይተው ተሰምተው የማይታወቁ ወንጀሎችን እና ግፎችን በመስራት ላይ ያሉትበኢትዮጵያ ስም እርዳታ እና ገንዘብ ይሰበስባ ነገር ግን የኢትዮጵያን ስም ለማጠለሸትና ለማጥፋት፣ ሕዝቡንም በመላው ዓለም እንዲዋረድ፤ በረሃብ ብቻ ሳይሆን በጭካኔ እና አረመኔነት እንዲታወቅ ለማድረግ ተግተውበመሥራት ላይ ናቸው

የኦርሞ እና የአማራ ሕዝቦች ይህን ሁሉ ግፍ ለአለፉት ሦስት ዓመታት በተለይ በዚህ አንድ ዓመት ውስጥመፈጸማቸውን እያዩናእየሰሙ፤ እንኳን ከትግራይ ሕዝብ ጎን ተሰልፈው ሊዋጉ ቀርቶእንደ አቅማቸው ከአረመኔው ግራኝ እና ኦሮሞ አገዛዙ ጎን ቆሞውና ከታሪካዊ እስማኤላውያን ጠላቶች ጋር አብረው፤ “ያዘው! በለው! ጨፍጭፈው!” በማለት ላይ ናቸው። ዛሬም ሳይቀር ይህ ሁሉ ሕዝብ በአሰቃቂ ሁኔታ እያለቀ እንኳን ባለፉት አሥሦስት ወራት ከሠሯቸውት ግልጽና ታሪካዊሆኑ ከባድ ስህተቶችና ኃጢዓቶች ታርመውና ንሰሐ በመግባት ተመልሰው፤ “ጦርነቱ ይቁም!” ለማለት እንኳ ፈቃደኞች አይደሉም። እስኪ “የኦሮሞ ተዋጊዎች” የተባሉት ግን የግራኝ Plan B ተጠባባቂ አርበኞች የሆኑት(OLA)የተባሉት አጭበርባሪዎች እውነት የፋሺስቱ ኦሮሞ አገዛዝ ተቃዋሚዎች ከሆኑ አንዱን አዲስ አበባ የሚገኘውን የግራኝ ባለ ሥልጣን ይድፉት! ምነው ከስድስት ወራት በፊት፤“ሱሉልታ ደረስን” ሲሉ አልነበረ እንዴ? ሻሸመኔን፣ አጣየና ከሚሴን በእሳት ሲያጋዩአቸው አልነበረ እንዴ? እነዚህ የዲያብሎስ ጭፍሮች ሁሉም አንድ ስልሆኑ በጭራሽ አያደርጉትም፤ ምክኒያቱም ይህ ጦርነት የሰሜኑን ተዋሕዶ ክርስቲያን ሕዝብ ጨፍጭፈው መጨረስ በእነ ጂኒ ጃዋር እና ቱርኮች በኩል እስላማዊቷን ኦሮሚያ ካሊፋትለመመሥረት እባብ ገንዳዎቹያቀዱትና ያለሙለትምኞት፣ ዕቅድና ተልዕኮ ነውና።

አሁን ከሊሲፈራዊው የባዕድ ርዕዮተ ዓለም ነፃ የሆኑት ጽዮናውያን፤ አማራ እና ኦሮሞ ከተባሉት ክልሎች ለእርዳታ ተብለው የተከማቹትን ምግቦችና መድኃኒቶች ብቻ ሳይሆን የጤፍ፣ የስንዴ፣ የገብስ እህሎችን እና ጥራጥሬዎችን ወደ ትግራይ መውሰድ ይኖርባቸዋል። ኦሮሞዎች እና አማራዎች “ወገን” የሚሉትን አንድን ክርስቲያን ሕዝብ አስርቦ ለመጨረስ ባለፉት ሦስት ዓመታት ያለምንም ተቃውሞ ሰርተዋልና ሁሉም ተፈርዶባቸዋል የፈለጉትን ያህል መጮኽና ማለቃቀስ ይችላሉ።

ትክክለኛዎቹ የአጼ ዮሐንስ ጽዮናውያን የትግራይ ኢትዮጵያውያንን አሳድደው፣ አስረበውና ጨፍጭፈው ከምድረ ገጽ ለማጥፋት የተነሳሱትን በተለይ በኦሮሞ እና አማራ ክልል የሚኖሩትን ነዋሪዎችን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የማንበርከክ ግዴታ አለባቸው። እስኪ እናስበው፤ አንድን ወገን በረሃብ ፈጅቶ ለመጨረስ ድንበር መዝጋት፣ እርዳታ መከልከል፣ ሰብል ማውደም፣ ምግብ መመረዝከዛ ይህ አልበቃ ብሎ የተራቡትን እና የታመሙትን ሕጻናት በአውሮፕላን/ በድሮን ቦምብ ማሸበርና መገደል። ምን ያህል እርኩሶች፣ ግፈኞችና አረመኔዎች ቢሆኑ ነው? 😈 ዓለም እኮ በመገረም እየታዘበቻቸው ነው፤ የሰይጣን ጭፍራው ግራኝ አብዮት አህመድ አሊና አጋሮቹ እኮ በቃላትም በድርጊትም አረመኔነታቸውን ደግመው ደጋግመው ለመላው ዓለም አሳውቀዋል። ይህ በትግራይ እና ተጋሩ ላይ እየተካሄደ ያለው ጥቃት የሰሜናዊውን ሕዝብ ቁጥር ቅነሳ/ማጥፊያ ዋቄዮአላህዲያብሎስ የጠራው ታሪካዊና ጂሃዳዊ ዘመቻ ነው።

ከንቱው የኤዶምውያኑ እና እስማኤላውያኑ ዓለም በትግራይ ሕዝብ ላይ የተሠራውን ወንጀል ሁሉ ባጭር ጊዜ ረስቶ፤ “ሰረቁ…ቅብርጥሴ” በማለት መቀበጣጠር ይችላል፤ ግን ዓለም መቼም የጽዮናውያን ወዳጅ ሆኖ አያውቅም፣ አይደለምም፣ ወደፊትም አይሆንም። ስለዚህ አሁን እኅሎች፣ ምግቦችና መጠጥ ከኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች ወደ ትግራይ በግድ መወሰድ ይኖርባቸዋል! እንዲያውም ለመጭዎቹ ሺህ ዓመታት ትግራይ የመንፈሳዊ ማዕከል ብቻ ነው መሆን ያለባት። እርሻዎቹን እና የኢንዱስትሪ ማዕከላቱን በተቀሩት የአክሱም ደቡብ ግዛቶች ብቻ ማድረጉ ተገቢ ነው። ላለፉት መቶ ሃምሳ ዓመታት በኦሮሞዎቹ አገዛዞች እንዲበላሽ፣ እንዲበከልና ደረቅ እንዲሆን የተደረገው የትግራይ ምድር ማገገም አለበት፣ ዝናቡ መመለስ አለበት፣ እጽዋቱ፣ የእጣን ዛፎቹ (የጦርነቱ አንዱ ተልዕኮ ይህን እንደ ኮሮና ያሉ ወረርሽኞችን የሚከላከለውን እጣን የሚያወጣውን የሕይወት ዛፍለሉሲፈራውያኑ አንጋፋ የዓለማችን መድኃኒት ዓምራች ኩባንያዎች ሲባል ማውደም ነው) አዕዋፋቱ መመለስ አለባቸው።

ኦሮሞዎች እና አማራዎች በትግራይ ላይ በፈጸሙት ወንጀል ሳቢያ የሺህ ዓመት እዳ ነው ያከማቹት፤ ስለዚህ ለሺህ ዓመታት እየገበሩ መኖር አለዚያ ደግሞ እስከ ሞቃዲሾ ድረስ ከሚዘልቀው ከመላው የአክሱማውያን ግዛት መጠረግ አለባቸው። ታላቁ ክርስቲያን ንጉሥ ነገሥት አፄ ዮሐንስ ፬ኛ ይህን ነበር የሚናገሩት፤ መጭው ዮሐንስ ፭ኛ ይህን ነው የሚያደርጉት!

❖ ❖ ❖

ያለምንም ጉድለት በሥላሴ ስም ይህን ሦስትነት አምናለሁ፤ ወዳጅ መስለው ጽዮናውያንን በመጠጋት፣ እያታለሉና በየዋሕ እንግዳ ተመስለው አክሱም ጽዮንን ያጠቋትን የጽዮን ጠላቶች የሆኑትንና በጽዮን ልጆች ላይ በጣም ብዙ ግፍ ያደረሱትን የዋቄዮ-አላህ-አቴቴ አጋንንቶችን እነ ግራኝ አብዮት አህመድ አሊ እና ተከታይ አህዛብ፣ እባብ ገንዳ (አባ ገዳ)መንጋውን 😈 ሁሉ የእግዚአብሔር ቃል መቅ ያውርዳቸው፣ በተሣለ የመለኮት ሠይፍ አንገታቸውን ይረደው። አሜን! አሜን! አሜን!

________________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

Actor Chris Tucker in Solidarity With The People of Tigray, Ethiopia

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 15, 2022

👏👏👏

______________

Posted in Ethiopia, Faith, Life, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: