Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • January 2022
    M T W T F S S
     12
    3456789
    10111213141516
    17181920212223
    24252627282930
    31  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for January 4th, 2022

ቅዱስ ዮሴፍ | በሚቀጥሉት ቀናት በመላው ዓለም ትልቅ ትኩረት ልንሰጣቸው የሚገቡንን ክስተቶችን እናያለን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 4, 2022

👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 👉 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 😇 ዮሴፍ 👉 መድኃኔ ዓለም

💭 የመጭውን የጌታችንን የልደት በዓል ተከትሎ በሚቀጥሉት ቀናት በመላው ዓለም ትልቅ ትኩረት ልንሰጣቸው የሚገቡንን ክስተቶች እናያለን

ኢትዮጵያ = የአዲስ ኪዳን ርስት ምድር = እስራኤል ዘነፍስ❖

💭 “ቅዱስ ጳውሎስ” ከሚለው ፊልም የተወሰደው ምስል የሚያሳየን ትክክለኛው ክርስቲያናዊ አለባበስ ኢትዮጵያኛው አለባበስ መሆኑን ነው።

[የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ፲፩፥፳፫]

ከእኔ ጋር ያልሆነ ይቃወመኛል ከእኔ ጋርም የማያከማች ይበትናል።”

ሰባዓሰገል መጥተው ለጌታ ሲሰግዱ ዮሴፍ አየ አምላክ ነህ ሲሉ እጣን ንጉሥ ነህ ሲሉ ወርቅ ፍቅር ነህ ሲሉ ከርቤ ለጌታ ሲገብሩ ዮሴፍ አየ ለካ ይሔ የተወለደው ሕፃን ተራ አይደለም ነገሥታት የሰገዱለት የነገሥታት ንጉሥ ቢሆን ነው ብሎ ድንግል ማርያም የንጉሥ እናት ኢየሱስን የነገሥታት ንጉሥ አምላክ መሆኑን የበኩር ልጅዋን ስትወልደው አወቀ።

ዮሴፍ ታላቅ ነገር ተመለከተ ደማቅ ኮከብ ከሰማይ ዝቅ ከምድር ከፍ ብሎ በቤተልሔም ዋሻ ፊት ለፊት ሲቆም አየ አሀ ልክ ኢያሱ አሞራውያንን በገባዖን ሲዋጋ በጸሎቱ ፀሐይን እንዳቆማት ኢየሱስ ገና በሕፃንነቱ በቤተልሔም ኮኮብን አቁሟል ስለዚህም ይህ ኮከብ የተገዛለት የጌቶች ጌታ ቢሆን ነው ብሎ ኢየሱስ ጌታ ፈጣሪ ድንግል ማርያም እመ ፈጣሪ የጌታ እናት መሆንዋን አወቀ።

________________

Posted in Ethiopia, Faith, Saints/ቅዱሳን, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

አስተዋይዋ እኅታችን | “’ኢትዮጵያውያን’ ፈውሱን ከፈለጉ የትግራይ ወገናቸውን ተንበርክከው ይቅርታ መጠየቅ አለባቸው”

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 4, 2022

👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 👉 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 😇 ዮሴፍ 👉 መድኃኔ ዓለም

💭 የመጭውን የጌታችንን የልደት በዓል ተከትሎ በሚቀጥሉት ቀናት በመላው ዓለም ትልቅ ትኩረት ልንሰጣቸው የሚገቡንን ክስተቶች እናያለን

፻/100% ትክክል! ጽዮናውያን እንደ ዋቄዮ-አላህ ባሪያዎች በአደባባይ ወጥተው ማለቃቀስ፣ መጮኽ፣ በዳያቸውን ለመወንጀልና ተጠያቂ ለማድረግ ድራማ መስራት አይችሉበትም፤ ለራሳቸው ከሚያስቡት አብልጠው ለሌላው ያስባሉ። በዚህም የተሠራባቸውን ተወዳዳሪ የሌለው ግፍና በደል በኢትዮጵያ ዘ-ስጋም ሆነ በመላው ዓለም ዘንድ በአግባቡ ለማሳወቅ አልቻሉም። የተበዳይነት ድምጽ/እሮሮ ከፍተኛ ኃይል ነው ያለው። ይህች ዓለም አንድ ሕዝብ ወይንም ግለሰብ ወይ ሙሉ በሙሉ ተበዳይ ሆኖ ከእንባ ጋር ካልቀረበ አሊያ ደግሞ ጥንካሬውን አሳይቶ በዳዮቹን ካልቀጣ በቀር ተገቢውን ትኩረት አትሰጠውም፤ እርዳታ ከማድረግም ትቆጠባለች። “እራሳችሁ መታገል የምትሹ ከሆነማ ቀጥሉበት” ብላ ዓይኖቿንም፣ ጆሮዎቿንም አፏንም ትከድናለች።

በትግራይ የተፈጸመውን ግፍና ወንጀል በተለይ ምዕራባውያኑ በደንብ አይተው መዝግበውታል። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ብሊንከን “በምዕራብ ትግራይ የዘር ማጽዳት ሥራ ተሠርቷል” ብለው ከጠቆሙን እኮ ዓመት ሊሆነው ነው። ምን እንደተሠራ እኮ በደንብ አይተውታል። እስከ አሁን ግን ሁሉም ነገር ተደባብሶ በ ጦር ሜዳ፤ “አወት” ዜና ተሸፋፍኗል። የዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ከተጋሩ የጠበቀው እንዲህ ዓይነት ዝምታ አልነበረም። የተፈጸመውን ዕልቂትና ውድመት ሁሉ ለመላው ዓለም በጩኸት እንዲያጋልጡ፤ የበቀል እርምጃዎችን እንዲወስዱ ይጠብቃል። እስላማውያኑ ሽብርተኞች ወይንም ከአራት ዓመታት በፊት ያዙን ልቀቁን ሲሉ የነበሩት የቄሮ በጥባጮች እኮ በትግራይ ላይ ዛሬ ከተሠራው ግፍ አንድ ሚሊዮነኛውን ያህል ግፍ ሳይደርስባቸው ነው ወደ አጥፍቶ ጠፊነት የተቀየሩት። ዓለም ተበዳዮችን ለመርዳትና ለማዳመጥ የሚሻው በሽብር ፈንጅ የታጀበ ጩኸት ሲከተል ብቻ ነው።

ሕወሓቶችም የአረመኔውን ግራኝ አብዮት አህመድ አሊን ወንጀል ለመሸፈን የሚሠሩ ይመስላሉ፤ ከአንዲት መንደር ወደ ሌላ መንደር ጦራቸውን እያንሸራሸሩ የዘር ማጥፋት ወንጀሉና ውድመቱ ሁሉ በጊዜው ለዓለም እንዳይወጣ በተዘዋዋሪ መልክ አፍነውት ይገኛሉ። ምርኮኞቹ ልደታቸውን በኬክ እና ማንጎ ጭማቂ ሲያከብሩ ያሳዩናል፤ ሕዝባችን ግን ምን ዓይነት ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ፣ ምን እየበላ እንደሆነ፣ የፋሺስቱ ኦሮሞ አገዛዝ ለኦሮሙማ ፕሮጀክቱ ሊፎካከሩትን የሚችሉትን ጽዮናውያንን እንዴት እንዳዳከማቸው፣ የትግራይን ከተሞችንና መንደሮችን በስንት ዓመት ወደ በሻሻነት እንደለወጣቸው፣ ገዳማቱንና ዓብያተክርስቲያናቱን አውድሞ በሕዝብ ክርስቲያኑ ላይ ምን ያህል ጉዳት ማድረሱን እንኳን ሊነግሩን አልፈለጉም። ስለ አክሱም ጽዮን እና ደብረ ዳሞ ውድመት ከሚነግሩን ይልቅ “አልነጃሽ” ስለተሰኘው መስጊድ ውድመት ደጋግመው መናገሩን ሲመርጡ እየሰማናቸው ነው።

ይህ ማለት ግን የጽዮናውያን አምላክ እግዚአብሔር፣ ጽዮን ማርያምና ቅዱሳኑ ሁሉንም ዲያብሎሳዊ ተግባር በቪዲዮ አልቀረጹትም ማለት አይደለም፤ እያንዳንዱን ወንጀል 24/7 በመመዝገብ ላይ ይገኛሉ።

ጭፍጨፋውን ያካሄደውና የደገፈው የተቀረው ኢትዮጵያዊ (፺/90% የሚሆነው፣ በተለይ ኦሮሞው + አማራው + ሶማሌው + ቤን አሚሩ) በዳይ ሆኖ ድራማ በመሥራት የተበዳይነት ሚና ለመጫወት መሞከሩ ዲያብሎሳዊ ድፍረት፣ ትልቅ ቅሌትና ከባድ ሃጢዓት ስለሆነ ለመዳን የሚሻ ከሆነ አሁን ያለው አማራጭ ጽዮናውያንን ከልቡ ይቅርታ ጠይቆና የፋሺስቱን ኦሮሞ አገዛዝ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በማስወገዱ ዘመቻ ላይ ተገቢውን የላብና ደም ካሳ ከፍሎ ለንስሐ እራሱን ማዘጋጀት ብቻ ነው። ይህን ባፋጣኝ ካላደረገ ግን ከኢትዮጵያ ምድር ተጠራርጎ ይወገድ ዘንድ እርስበርስ እየተላለቀ ወደ ጥልቁ ይጣላል።

____________________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: