Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • November 2021
    M T W T F S S
    1234567
    891011121314
    15161718192021
    22232425262728
    2930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for November 6th, 2021

፴/30ቱ የጉዕተሎ መድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን ሰማዕታት እነዚህ ናቸው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 6, 2021

👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 👉 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 👉 ዮሴፍ መድኃኔ ዓለም

✞✞✞💭👉🔥 በቤተክርስቲያኗ የመድኃኔ ዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓል ዕለት፤ ማክሰኞ ታህሣሥ ፳፯/ ፪ሺ፲፫ ዓ.ም የሰማዕትነት አክሊልን የተቀዳጁት ፴/30 የጉዕተሎ መድኃኔ ዓለም ልጆችን ነፍስ በቅዱሳኑ እቅፍ ያኑርልን ከማህበረ ፃድቃን ይደምርልን። ✞✞✞

ከአንድ ሰዓት በፊት መልክአ መድኃኔ ዓለምን ለማንበበ በረንዳ ላይ ልክ ወጣ ስል አንዲት እርግብ ፀሐይዋን ሸፍና ከበላዬ ላይ ቀርባ በረረች። ከአምስት ሰከንድ በኋላ ያልነበረ ነፋስ “ዥውው!” ብሎ ሲያልፍና ፀጉሬንም ሲያራግበው በጣም የተለየ ስሜት ተሰማኝ። እኔን ለማሳመን መሰለኝ፤ እርግቧ ተመልሳ እንደዚሁ ባቅራቢየ በረረች አሁንም ነፋሱ ወዲያና ወዲህ ሲል ተገነዘብኩት። “የመድኃኔ ዓለም ሥራ ድንቅ ነው” ብዬ የሚከተሉትን የመልክአ መድኃኔ አለም ኃይለኛ ቃላትን አንበበኩ፤

“ለ ዕርገትክ መድኃኔ ዓለም ሆይ፤ በዓውሎ ነፋስና በእሳት ነበልባል አምሳል መንፈስ ቅዱስን ትልክልን ዘንድ በነጐድጓድና በመባርቅት የሠረገላ ዘባን ለተከናወነ ዕርገትህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤ ቅድመ ዓለም የነበርክ ዛሬም ያለህ ለዘለዓለሙም ጸንትህ የምትኖር አምላክ ስትሆን የታሠሩ አገልጋዮችሁን አንተ ታሥረህ ፈታሃቸው በሞትህም የሞቱትን ወገኖችህን አስነሣሃቸው።

ለኅጡእ ምግባ መድኃኔ ዓለም ሆይ፤ ሃይማኖት ስንኳ ቢኖረኝ በጎ ምግባር የሌለኝ አነስተኛው አገልጋይ ማደሪያ ቤቴ መኖሪያ ቦታዬ ከቅዱሳኖችህ ጋር ይሆን ዘንድ ፈቃድህ ይሁን አቤቱ!

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤ ከከንቱ ሞት አድነኝ። ሁሉ ከንቱ ነው። የዚህ ዓለም ንብረት የከንቱ ከንቱ ነው። ሁሉም ኃላፊ ጠፊ ነውና።

ስብሐት ለከ፤ አቤቱ በፍጥረቱ ሁሉ አንደበት የምትመሰገን ለአንተ ለመድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ክብር ምስጋና ይገባል። አቤቱ ለተራቆቱት ልብስ የምትሆናቸው ላእንተ ለኢየሱስ ክርስቶስ ክብር ምስጋና ይገባል።”

♰♰♰ በእውነት ድንቅ ድንቅ ድንቅ ነው!♰♰♰

እውነት ነው፤ አቤቱ ፈጣሪያችን ጸጋህን በምታድልበት መንፈስ ወገኖችሁን ጽዮናውያንን ደስ አሰኛቸው፤ የከበደውን የጨነቀውን ነገር የምታቃልል አንተ ነህ የተቸገረውን፣ የተጎሳቀለውንና የተበደለውን ሁሉ የምትረዳ አንተ ነህ፤ የሕዋርያት ጌጣቸው የነዳያን ገንዘባቸው ተስፋ ላጡ ሰዎች ተስፋቸው፣ አለኝታቸው አንተ ነህ፤ ሙታንንም የምታስነሣቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፤ ለአብ ኃይሉ ጥበቡ የምትሆን አንተን እናመሰግናለን። ዛሬም መቼም መች ለዘላለሙ አሜን።

👉 የ ፴/30ውን ሰማዕታት ስም እየጠራን ለመድኃኔ ዓለም “እልልል!” 😊😊😊 እንበል!!! ይብላን ለገዳዮቻቸው!👹 ወዮላቸው!

❤️ የሰማዕታቱ የስም ዝርዝር


ስምጾታማዕረግ
1ቄስ ገብረ ዮሐንስ ደስታወንድየቤተክርስቲያን ሊቅ
2ቄስ ነጋ ተስፋይወንድ
3መሪጌታ ኪዳነ ማርያም ተፈሪወንድየቤተክርስቲያን ዋና ሊቅ
4ቄስ ሐዱሽ ኃይለ ማርያምወንድቄስ ገበዝ የቤተክርስቲያን ሊቅ
5ቄስ ገብሬ አጽበሐወንድየቤተክርስቲያን ሊቅ
6.ሀጎስ ሃይሉወንድ
7ኪዳኔ ተክለ ሐይማኖትወንድ
8ብርሃኔ ገብረ አረጋዊ (አንገታቸው ተቀልቷል)ወንድ
9ግርማይ ንጉሤ (ከልጃቸው ሚኪያስ ጋር)ወንድ
10ሚኪያስ ግርማይ ንጉሤ (ከአባታቸው ግርማይ ጋር)ወንድ
11ዲያቆን በርሔ ደስታ ወልደ ገብርኤልወንድ
12ዲያቆን ብርሃኔ ገብረ ሥላሴወንድ
13ዲያቆን ጽጋብ አለም ፊትዊወንድ
14ደሳለኝ ተስፉ ሀጎስወንድ
15አታክልቲ መሰለ ገብረ ዮሐንስወንድ
16ሴት መነኩሴ እታይ ዘሀፍታሴት
17ምሕረት ገብረ እግዚሴት
18ሀደጋ ለማሴት
19ካሕሳ ገብሬሴት
20ኪዳን ወልዱሴት
21ኪዳን ረዳሴት
22ለታይ ገብረ ማርያም (ከሴት ልጃቸው ብርሃን ጋር)ሴት
23ብርሃን ገብረ ጻድቅ (ከእናታቸው ለታይ ጋር)ሴት
24በኩረ ጽዮን ደስታወንድ
25ደስታሰላም ግርማይወንድ
26ብርሃኔ ገብረ ኢየሱስወንድ
27መሪ ጌታ ደሳለኝ ካህሳይወንድየቤተክርስቲያን ሊቅ
28አብረኸት እቁባዝጊFemale
29ተስፋይ ገብረ ሥላሴወንድ
30አንገሶም ገብረ ሥላሴ ታደሰወንድ

____________________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: