Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • July 2021
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    262728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ ይፈሩ፥ ወደ ኋላቸውም ይመለሱ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 11, 2021

...በሰገነት ላይ እንደ በቀለ ሣር፥ ሳይነቀል እንደሚደርቅ፥ ለሚያጭደው እጁን፥ ነዶዎቹን ለሚሰበስብ እቅፉን እንደማይሞላ ይሁኑ።

💭 አዎ! ኢትዮጵያ ማለት የአዲስ ኪዳኗ እስራኤል ዘ-ነፍስ ማለት ናት። የአክሱም ጽዮንን ልጆች የሚጠሉ ጽዮን ማርያም እናታችንንና ኢትዮጵያንም ይጠላሉ ማለት ነው። ይህም ዛሬ ፺/90% የሚሆኑትን “ኢትዮጵያውያን ነን፣ ክርስቲያን ነን” የሚሉትን ግን ኢትዮጵያውያንም ክርስቲያንም ያልሆኑትን የወደቁትን ኢትዮጵያ ዘ-ስጋ ይመለከታል።

አባታቻን አባ ዘ-ወንጌል ካስጠነቀቁን ነገሮች መካከል፤

ኢትዮጵያን በዚህ ወቅት እያስተዳደሯት ያሉት ጠላቶቿ መሆናቸውን፤ ስለዚህ እነ አረመኔው ግራኝ የነገሱባት ‘ኢትዮጵያ’ ‘ጽዮናዊቷ ኢትዮጵያ’ ሳትሆን የዋቄዮ-አላህ ‘ኦሮሚያ’ መሆኗን

በዚህ የፈተና ወቅት ፀረትግራዋይ/ፀረጽዮናውያን የሆነ አቋም እንዳይኖረን

/10% የሚሆኑት ተዋሕዷውያን ብቻ የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማየት እንደሚተርፉ

የሚሉት ይገኙበታል። ለሁላችንም በጣም ቁልፍ የሆነ ነጥብ ስለሆነ በደንብ እናስተውል!

💭 ቅዱሱ ነብይ አባታችን ንጉሥ ዳዊትም ይህን ኃይለኛ መልዕክት ነበር ከሦስት ሺህ ዓመታት በፊት ያስተላለፈልን፤ ድንቅ ነው!

✞✞✞[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፻፳፰]✞✞✞

፩ እስራኤል። ከትንሽነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ ተሰለፉብኝ ይበል፤

፪ ከትንሽነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ ተሰለፉብኝ፤ ነገር ግን አላሸነፉኝም።

፫ ኃጢአተኞች በጀርባዬ ላይ መቱኝ፥ ኃጢአታቸውንም አስረዘሙአት።

፬ እግዚአብሔር ጻድቅ ነው፤ የኃጢአተኞችን አንገታቸውን ቈረጠ።

፭ ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ ይፈሩ፥ ወደ ኋላቸውም ይመለሱ።

፮ በሰገነት ላይ እንደ በቀለ ሣር፥ ሳይነቀል እንደሚደርቅ፥

፯ ለሚያጭደው እጁን፥ ነዶዎቹን ለሚሰበስብ እቅፉን እንደማይሞላ ይሁኑ።

፰ በመንገዱም የሚያልፉ። የእግዚአብሔር በረከት በእናንተ ላይ ይሁን፤ በእግዚአብሔር ስም እንመርቃችኋለን አይሉም።

💭 ጉብኝት ወደ ፤ ❖❖❖ታላቁ ገዳም ጉንዳ ጉንዶ ማርያም❖❖❖ ፲፬ኛው ምዕተ ዓመት ተመሠረተ

✞✞✞[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፻፳፮]✞✞✞

፩ እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፥ ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤ እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፥ ጠባቂ በከንቱ ይተጋል።

፪ በማለዳ መገሥገሣችሁም ከንቱ ነው። ለወዳጆቹ እንቅልፍን በሰጠ ጊዜ፥ እናንተ የመከራን እንጀራ የምትበሉ፥ ከተቀመጣችሁበት ተነሡ።

፫ እነሆ፥ ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው፥ የሆድም ፍሬ የእርሱ ዋጋ ነው።

፬ በኃያል እጅ እንዳሉ ፍላጾች፥ የጐልማስነት ልጆች እንዲሁ ናቸው።

፭ ከእነርሱ ዘንድ ምኞቱን የሚፈጽም ብፁዕ ሰው ነው፤ ጠላቶቻቸውን በአደባባይ በተናገሩ ጊዜ እርሱ አያፍርም።

✞✞✞[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፻፳፯]✞✞✞

፩ እግዚአብሔርን የሚፈሩት ሁሉ፥ በመንገዶቹም የሚሄዱ ምስጉኖች ናቸው።

፪ የድካምህንም ፍሬ ትመገባለህ፤ ምስጉን ነህ መልካምም ይሆንልሃል።

፫ ሚስትህ በቤትህ እልፍኝ ውስጥ እንደሚያፈራ ወይን ናት፤ ልጆችህ በማዕድህ ዙሪያ እንደ ወይራ ቡቃያ ናቸው።

፬ እነሆ፥ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው እንዲህ ይባረካል።

፭ እግዚአብሔር ከጽዮን ይባርክህ፤ በሕይወትህ ዘመን ሁሉ፥ የኢየሩሳሌምን መልካምነትዋን ታያለህ።

፮ የልጆችህንም ልጆች ታያለህ። በእስራኤል ላይ ሰላም ይሁን።

_________________________________

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: