ቅዱስ ዑራኤል በደመና? | የትግራይ ጀነሳይድ እንዲቀጥል አህዛብ በአዲስ አበባ ሰልፍ በወጡበት ዕለት
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 30, 2021
👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 👉 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 👉 ዮሴፍ 👉መድኃኔ ዓለም
👉 ከደቂቃዎች በፊት ደመናው ልክ ወደ ኢትዮጵያ አቅጣጫ ባለው የደቡብ ምስራቅ ሰማይ ላይ
❖❖❖[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፺፮፥፩፡፫]❖❖❖
“እግዚአብሔር ነገሠ፤ ምድር ሐሤትን ታድርግ፥ ብዙ ደሴቶችም ደስ ይበላቸው። ደመና ጭጋግም በዙሪያው ናቸው፤ ጽድቅና ፍርድ የዙፋኑ መሠረት ናቸው። እሳት በፊቱ ይሄዳል፥ ጠላቶቹንም በዙሪያው ያቃጥላል።“
❖❖❖[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፺፰፥፮፡፰]❖❖❖
“ሙሴና አሮን በካህናቱ ዘንድ፥ ሳሙኤልም ስሙን በሚጠሩት ዘንድ ናቸው። እግዚአብሔርን ጠሩት፥ እርሱም መለሰላቸው። በደመና ዓምድም ተናገራቸው፤ ምስክሩንና የሰጣቸውን ትእዛዝ ጠበቁ። አቤቱ አምላክችን ሆይ፥ አንተ ሰማሃቸው፤አቤቱ፥ አንተ ማርሃቸው፥ ሥራቸውን ሁሉ ግን ተበቀልሃቸው።“
የአሕዛብ አምልኮታቸው ከወርቅና ከብር፣ ከነሐስና ከመዳብ፣ ክድንጋይና ከእንጨት፣ ከኒኬልና ከሸክላ በሰው እጅ የተሠሩ ናቸው። አፍ እያላቸው አይናገሩም ዓይን እያላቸው አያዩም፣ ጆሮ እያላቸው አይሰሙም፣ አፍንጫ እያላቸው አያሸቱም፣ እጅ እያላቸው አይዳስሱም፣ እግር እያላቸው አይራመዱም/አይሄዱም፣ በጉሮሮአቸው አይናገሩም፣ በአፋቸውም ውስጥ ትንፋሽ የላቸውም። እንግዲህ ሠሪዎቻቸውና የሚያምኑባቸው ሁሉ እንደሱው ይሁኑ በዕውነት ለዘላለሙ አሜን።
✝✝✝አቤቱ የመላእክት ሁሉ አለቃ የሚሆን የቅዱስ ዑራኤል አምላክ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በክርስቶስ ክርስቶሳውያን የተሰኘን የጥምቀት ልጆች ከመከራ ሥጋ ፤ከመከራ ነፍስ ጠብቀን ለዘለዓለሙ አሜን።✝✝✝
___________________________________
Leave a Reply