Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for May 1st, 2021

ቀዳም ሥዑር | የቅዱስ እሳት ተአምር በኢየሩሳሌም | The Miracle of the Holy Fire in Jerusalem

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 1, 2021

✞✞✞ቅዳሜ፤ ቀዳም ሥዑር (ሹር ቅዳሜ)፤ ለምለሚቱ ቅዳሜ፥ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፥ ሰንበት ዐባይ፥ ቅዱስ ቅዳሜ።✞✞✞

የማያቃጥለው እና የክርስቲያኖችን ነፍስ የሚያስደስተው ይህ ድንቅ ሥነ-ስርዓት በኢየሩሳሌም በሚገኘው የትንሳኤ ቤተክርስቲያን ውስጥ በቅዱስ ቅዳሜ ይካሄዳል።

ፋሲካ የሚውልበት ቀን በየዓመቱ እንደ አዲስ ይወሰናል፡፡ የቀን እና የሌሊት ርዝመት እኩል በሚሆንበት የፀደይ እኩልነት እና ከአይሁድ ፋሲካ በኋላ የመጀመሪያ እሁድ መሆን አለበት። ስለዚህ ብዙ ጊዜ የተለያዩ መስፈርቶችን በመጠቀም ከሚወስነው የካቶሊክና ፕሮቴስታንት ፋሲካ ቀን ይለያል።፡ የቅዱስ እሳት በዓለም ምስራቅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በጣም የታወቀ ተዓምር ነው፡፡ ለዘመናት በየአመቱ በተመሳሳይ ቦታ፣ በተመሳሳይ ጊዜና በተመሳሳይ ሁኔታ ይካሄዳል። ከጊዜ ወደ ጊዜ እንደዚህ በመደበኛነት እና ያለማቋረጥ የሚከሰት ሌላ ተዓምር አይታወቅም። የሚከናወነው በኢየሩሳሌም በሚገኘው የትንሳኤ/ የቅዱስ ጎለጎታ ቤተ ክርስቲያንን ውስጥ ነው ፣ በምድር በጣም በተቀደሰው ስፍራ ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በታሰረበት፣ በተሰቀለበት እና በመጨረሻም ከሞት በተነሳበት፡፡

The ceremony, which awes the souls of Christians, takes place in the Church of the Resurrection in Jerusalem. The date for Pascha is determined anew for every year. It must be a first Sunday after the spring equinox and Jewish Passover. Therefore, most of the time it differs from the date of Papal Protestant and Protestant Easter, which is determined using different criteria. The Holy Fire is the most renowned miracle in the world of Eastern Orthodoxy. It has taken place at the same time, in the same manner, every single year for centuries. No other miracle is known to occur so regularly and so steadily over time. No other miracle is known to occur so regularly and so steadily over time. It happens in the Church of the Holy Sepulchre in Jerusalem, the holiest place on earth, where Christ was crucified, entombed, and where He finally rose from the dead.

Breaking News from #Jerusalem the Resurrection Church :blood is leaking from the stone Jesus body was laid before his burial . You can hear the Israeli police closed the area.

___________________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

በጌታችን የስቅለት ዕለት በሚሮን እስራኤል ፵፬/44 አይሁዶች ሞቱ | ያሳዝናል፤ ግን በአጋጣሚ?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 1, 2021

R.I.P ነፍሳቸውን ይማርላቸው!

ሰሜን እስራኤል ውስጥ ትናንትና ጠዋት አይሁዶች በዓል በሚያከብሩበት ሥፍራ በደረሰ መገፋፋትና መረጋገጥ ፵፬/44 ሰዎች መሞታቸው ታወቀ። ሚሮን በተባለችው ከተማ ውስጥ ላግ ባኦመር የተባለው የአይሁዶች በዓል በመከበር ላይ ሳለ በደረሰው በዚሁ አደጋ ከ፻፶/150 በላይ ሰዎችም መቁሰላቸውን የጤና ባለሥልጣናት ተናግረዋል። ግፍያና መረጋገጡ የደረሰው በስፍራው በርካታ ሰዎች በአንድ ጠባብ መሿለኪያ ውስጥ ለማለፍ ሲሞክሩ በተፈጠረ መጨናነቅ ነበር። ስፍራው ማስተናገድ የሚችለዉ ሰዎች ቁጥር ፲/10ሺህ መሆኑን ባለሥልጣናት ቢናገሩም ከተባለው ዐሥር እጥፍ በላይ ሰዎች በቦታው እንደነበሩ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል። አንድ ምእመን እንደተናገረው በአካባቢው ፶/50 ሰዎች ሊይዝ በሚችል ቦታ ላይ ቁጥራቸው ፭፻/ 500 የሚሆን ሰዎች ነበሩ። የዐይን ምስክሮች ሰዉ ወደ ተጣጣበበው ስፍራ እንዲገባ የፈቀዱትንና መውጫዎችንም በፍጥነት አልከፈቱም ያሏቸውን ፖሊሶች ወቅሰዋል። በሀገሪቱ ብሔራዊ የሐዘን ቀን ያወጁት የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ፦ በአደጋው ሥፍራ በሔሊኮፕተር ፈጥነው በመገኘት ንግግር አሰምተዋል። «በሜሮን ተራራ ላይ የተከሰተው አደጋ በእሥራኤል ሐገረ መንግሥት ታሪክ ከከፉት ክስተቶች አንደኛው ነው። በአደጋው ለሞቱት ሐዘናችን እንገልጣለን። ለሟቾች ቤተሰቦች መጽናናትን፣ ለቁስለኞች ደግሞ ፈጽሞ እንዲሻላቸው እንመኛለን።»ወደ ራቢ ሺሞን ባር ዮቻይ የመቃብር ሥፍራ መጓዝን የሚያካትተው በዓል አይሁዶች በሮማውያን ወራሪዎች ላይ ያካሄዱት አመጽ መታሰቢያ ነው። ሜሮን ተራራ ላይ የሚገኘው በአመጹ ተሳታፊ የነበሩት የራቢ ሺሞን ባር ዮቻይ የመቃብር ስፍራ በየዓመቱ በሺህዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን የሚጎበኙት ስፍራ ነው። ዛሬ በቦታው የተገኙትን ሰዎች ብዛት መገናኛ ብዙኃን ፲/10 ሺህ እንደሚጠጋ ገምተዋል።

ሕልም ይሆን?” በማለት እራሴን ተገርሜ በመጠየቅ ላይ ነኝ። በሚሮን ከተማ ይህ አሳዛኝ ዕልቂት ሲፈጸም፤ “ሕማማተ መስቀልን” እያነበብኩ ነበር።

የሙሴ አገልጋይ የነዌ ልጅ ኢያሱ በመሰሪዎቹ ከነዓናውያን ነገሥታት ላይ ድል የነሣበት ቦታ ‘ሚሮን’ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጠቅሷል።

[መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ ምዕራፍ ፲፪፥፳]

የአሶር ንጉሥ፥ የሺምሮን ሚሮን ንጉሥ፥

በአክሱም ጽዮን ላይ ጦርነት ከፍተው የእግዚአብሔርን ልጆች በመጨፍጨፍ ላይ ያሉት እነ ግራኝ አብዮት አህመድ የተረገሙት ከነዓውያን የዋቄዮ-አላህ ልጆች ናቸው። እነዚህ የእግዚአብሔር ጠላቶች (ነገሥታት)በመጭዎቹ ቀናት ጽላተ ሙሴን በያዙትና በቅዱስ ጊዮርጊስ በሚመሩት በአክሱም ጽዮን ልጆች ድል ይነሳሉ ማለት ነው!

የሚገርም ነው፤ በጸሎተ ሐሙስ ዕለት ይህን አውስቼ ነበር፤

👉 በ ፲፱፻፵/1940ዓ.ም የታዩ ቁልፍ ታሪካዊ ክስተቶች፦

☆ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከግብጽ ነፃ ወጥታ የራሷን ፓትርያርክ ትመርጥ ዘንድ ሂደቱ ተጀመረ፤ በ፲፱፻፶፩/1951 ዓ.ም የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት እና የመጀመሪያው ፓትርያርክ አቡነ ባስልዮስ (ገብረ ጊዮርጊስ)ቀዳማዊ ሆኑ።

☆ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር እንደገና ትቀላቀል ዘንድ ሂደቱ ተጀመረ

☆ አይሁዶች በ ፪ሺ፱፻/2900 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የተባበረ እና ሉዓላዊ ሀገር በመሆን ለእስራኤል ነፃነት አወጁ – እስራኤል አገር ሆነች

👉 እነዚህ ታሪካዊ ክስተቶች ምንን እየጠቆሙን ይሆን?

❖ በኦሮማራው ንጉሥ አፄ ምኒልክ የተለያዩት የትግራይ እና ኤርትራ ትግርኛ ተናጋሪ ሰሜን ኢትዮጵያውያን መዋሐድና አንድ መሆን?

❖ የሰሜን ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምስረታ?

👉 ሌላው አስገራሚ ነገር፤

በዚህ የጌታችን የትንሣኤ እሁድ ዕለት የፎርሙላ አንድ ሞተር ስፖርት እስቅድምድም ወደ ፖርትጋሏ ፖርቲማኦ ተመልሷል። ዋው! ከዚህ ጋር በተያያዘና 👉 ፵፬/44 ቁጥርን አስመልክቶ የሚከተሉትን ጽሑፍና ቪዲዮ ልክ ከአምስት ወራት በፊት በዲሴምበር መግቢያ ላይ አቅርቢያቸው ነበር።

👉 “የዓለም ቻምፒየኑ የመርሰድስ ሾፌር የ666ቱን ድብቅዋሻ አሳየኝ”

ይህን ባለፉት ቀናት እንደማቀርብ ቃል የገባሁትን ቪዲዮ ሳዘጋጅ አንድ “ክው!” ያደረገኝን ሰበር ዜና ሰማሁ፤ እሱም፤ “ሉዊስ ሃሚልተን በኮሮና ተያዘ”የሚለው ነበር። ትናንትና ባቀረብኩት ቪዲዮ ላይ የተካሄደው የባሕሬኑን ውድድር ሉዊስ ሃሚልተን ነበር ያሸነፈው። “የፈረንሳይ ሁከት፣ ብጥብጥና እሳት ከአክሱም ጽዮን ጋር ምን ያገናኛቸዋል? https://youtu.be/ZtLqhNtQ09s

ላለፉት ሳምንታት ሾፌር ሉዊስ ሃሚልተን ያሳየኝ የ666ቱ ድብቅ ዋሻ ይህን ይመስላል ፥ ቁጥሮቹ ላይ እናተኩር፦

ውቦቹን የግዕዝ ቍጥሮቻችንን ባለመጠቀሜ ይቅርታ

👉 25 ኦክቶበር 2020 .ም ፖርቲማኦ ፖርቱጋል ፎርሙላ 1/F1 ሉዊስ ሃሚልተን የ6 ጊዜ የዓለም ቻምፒየን፤ ከ1ኛ ቦታ ጀመረ፤ 66 ዙሮች መነዳት አለባቸው፤ በዚህ ቦታ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ

ነው የፎርሙላ 1 ውድድር ሲካሄድ፤ አሸናፊው ቍ. 44 ሉዊስ ሃሚልተን ሆነ። በፎርሙላ 1 ታሪክ ለ 92ኛ ጊዜ ውድድሩን በማሸነፍ ሉዊስ ሃሚልተን የታላቁን ጀርመናዊ ሚካኤል ሹማከር ሬከርድ ሰበረ። የሚገርም ነው፤ ይህ በደቡብ ፖርቱጋል የሚገኘው ቦታ፤ ፖርቲማኦ በኮሮና ምክኒያት የአሜሪካን ከተሞች ተክቶ ነው በድንገት እንዲያዘጋጅ የተደረገው። ከአስራ አምስት ዓመታት በፊት ወደ እዚህ አካባቢ ለጥቂት ወራት ለስራ ሄጄ ነበር፤ በጣም ድንቅ ቦታ ነው፤ በተለይ “ላጎሽ” የተባለችው ትንሽ ከተማ በዓለም ካየኋቸው ውብ ከተሞች መካከል የምትመደብ ናት።

በዚሁ ዕለት ጎረቤቴ “ላሊበላ” ወደተባለው የሃበሻ ምግብ ቤት “እንሂድ፤ እንጀራ፣ እንጀራ”(ነጭ ናት፤ ምግባችንን ይወዱታል) ብላኝ ሄድን፤ አጠገባችን የነበሩ እንግዶች ለምግባቸው 66 ዩሮ ከፍለው እንደወጡ፤ መሸት ሲል የቴሌቪዥኑ ዜና አንድ ታዋቂ ጀርመናዊ ፖለቲከኛ በ66 ዓመታቸው ማረፋቸውን ተናገረ። “አሃ!” አልኩ “ዛሬ 66 ዙር በፖርቲማኦ፤ ምግብ ቤት 66 ዩሮ አሁን ደግሞ ይህ ታዋቂ ፖለቲከኛ በ66 ዓመቱ አረፈ” በማለት ተገረምኩ። ነጠብጣቦቹ እስኪገጣጠሙልኝ ድረስ ለጎረቤቴ አልነገርኳትም።

👉 15 ኖቬምበር 2020 .ም ፥ ኢስታንቡል ቱርክ ፎርሙላ 1/F1፤ ቱርክም በኮሮና ምክኒያት ነው እንድታዘጋጅ የተደረገችው እንጂ ፕሮግራም ውስጥ አልተካተተችም ነበር። በኢስታንቡል ፓርክ ሉዊስ ሃሚልተን የ6 ጊዜ የዓለም ቻምፒየን፤ ያለተለምዶው ከ6ኛ ቦታ ይጀምራል፤ ሁልጊዜ 1ኛ ወይም 2ኛ የሚጀምር ቻምፒየን ነበር፤ ዛሬ ግን 6ኛ።

እንደሚታወቀው ቱርክ የክርስቶስ ተቃዋሚ 666 ሃገር ናት፤ በዮሐንስ ራዕይ ላይ የተጠቀሱት 7ቱ የእስያ

አብያተ ክርስቲያናት ታስረው የሚገኙትም እዚሁ ቱርክ ነው። ከሳምንታት በፊት የተከሰተውን ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ እናስታውሳለን?

በቱርክ ኢስታምቡልና ኢዝሚር ዛሬም በአስከፊ ማዕበል ተመቱ”

ለማስታወስ ያህል እ..አ ከ2007 ጀምሮ የሚሾፍረው የእንግሊዛዊው ክልስ ሉዊስ ሃሚልተን መለያ ቍ. 44 ነው።

ዝናባማ በነበረው የኢስታንቡል ፓርክ ሉዊስ ሃሚልተን ውድድሩን ክ6ኛ ቦታ ጀመረ፤ ወደ 3ኛ ዘለለ፤

እንደገና ወደ 6ኛ ተመለሰ፣ በመጨረሻም 1ኛ ሆነ፤ በዚህም በፎርሙላ 1/F1 ታሪክ ለ 7ኛ ጊዜ ቻምፒየን በመሆን ከታላቁ ጀርመናዊ ሚካኤል ሹማከር ሬከርድ ጋር እኩል ሆነ።

በዚህም ቍ 44 ሉዊስ ሃሚልተን በ666ቱ ቱርክ ሃገር አውሬውን በ7 ሰበረው! ስለ 7ቱ ዓብያተ ክርስቲያናት ነበር ወዲያው ያሰብኩት።

👉 12 ዓመታት በፊት ይህን በጦማሬ ጽፌ ነበር

. 44 ሉዊስ ሃሚልተን የመጀመሪያው ጥቁር F1 ቻምፒየን፣ ባራክ ኦባማ 44ኛውና የመጀመሪያው

ጥቁር የአሜሪካ ፕሬዚደንት። ባራክ ኦባማ በጦማሬ መልስ ሰጥቶ አይቼ ነበር። https://wp.me/piMJL-6o

👉 ይህን ቪዲዮ ሳዘጋጅ “ሉዊስ ሃሚልተን በኮሮና ተያዘ!” የሚለው ሰበር ዜና ደረሰኝ፤ ይገርማል ከአራት ወራት በፊት ሉዊስ ፀረክትባት እና ፀረቢል ጌትስ የሆነ አቋም እንዳለው ጭምጭምታ አሰምቶ ነበር! ቢል ጌትስ?

👉 አሁን ነጠብጣቦቹን እናገናኛቸው፦

666 = ቱርክ

666 = ባራክ ኦባማ

666 = ባለ 44 እድሜው አብዮት አህመድ አሊ

666 = የክትባት አባት ቢል ጌትስ

በዓለም በጣም ኃብታም ከሆኑት ስፖርተኞች መካከል አንዱ የሆነው ሉዊስ ሃሚልተን አጥባቂ ክርስቲያን ነው፤ እርዳታ ሰጭና ፀረዘረኝነት ትግልን የሚያደርግ ትሁት ሰው ነው። አግዚአብሔር አምላክ ፈውሱን መድኃኒቱን ይላክለት!

ሌላ፦ ልክ “66% uploaded 6 minutes left” ላይ ሲደርስ ኢንተርኔቴ ያለወትሮው ተቋረጠ። እንደገና ስጀምረው፤ “Woman says why she believes Monster Energy drinks are from Satan” / ሴትዮዋ የሞንስተር ኢነርጂ ወይንም የኃይል መጠጦች ከሰይጣን ናቸውብላ እንደምታምን ትናገራለች” የሚለውን ቪዲዮ አየሁ። ዋው!

___________________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Infos, Life | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: