Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • April 2021
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

ጸሎተ ሐሙስ / የነጻነት ሐሙስ ፪ሺ፲፫ ዛሬ በኢየሩሳሌም፤ እስራኤል | ግብጾች የኢትዮጵያን ገዳም አወኩት!

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 29, 2021

👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 👉 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 👉 ዮሴፍ 👉መድኃኔ ዓለም

👉 ማክሰኞ 👉 ሐሙስ 👉 ዓርብ 👉 ቅዳሜ 👉 እሑድ

በኢየሩሳሌም የሚገኘውን የኢትዮጵያ ገዳም ግብጾች “መውረስ አለብን” እያሉ አሁን ኢትዮጵያውያን ምዕመናንን በመበጥበበጥ ላይ እንደሆኑ ከደቂቃዎች በፊት የደረሰኝ መልዕክት ይጠቁማል። ዋው! በእርግጥም አጋንንቱ ተለቅቀዋል!

ሕማማተ እግዚእ ዕለተ ሰሉስ/ማክሰኞ በገብርኤል፣ ጸሎተ ሐሙስ በማርያም፣ ዓርብ ስቅለት በኡራኤል፣ ቅዳሜ፤ ቀዳም ሥዑር (ሹር ቅዳሜ) በጊዮርጊስ እንዲሁም እሑድ ትንሣኤ በተክለ ሐይማኖት ዕለታት ሲውሉ ከ፸፫/73 ዓመታት በኋላ (፲፱፻፵/1940ዓ.ም)ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ነው። ዘንድሮ በትግራይ ሕዝብና በአክሱም ጽዮን ላይ ጦርነት የታወጀው በእነዚህ ቀናት ነበር፤ በቅዱስ ጊዮርጊስና በአባታችን በአቡነ ተክለ ሐይማኖት ዕለታት።

👉 በ ፲፱፻፵/1940ዓ.ም የታዩ ቁልፍ ታሪካዊ ክስተቶች፦

☆ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከግብጽ ነፃ ወጥታ የራሷን ፓትርያርክ ትመርጥ ዘንድ ሂደቱ ተጀመረ፤ በ፲፱፻፶፩/1951 ዓ.ም የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት እና የመጀመሪያው ፓትርያርክ አቡነ ባስልዮስ (ገብረ ጊዮርጊስ)ቀዳማዊ ሆኑ።

☆ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር እንደገና ትቀላቀል ዘንድ ሂደቱ ተጀመረ

☆ አይሁዶች በ ፪ሺ፱፻/2900 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የተባበረ እና ሉዓላዊ ሀገር በመሆን ለእስራኤል ነፃነት አወጁ – እስራኤል አገር ሆነች

👉 እነዚህ ታሪካዊ ክስተቶች ምንን እየጠቆሙን ይሆን?

❖ በኦሮማራው ንጉሥ አፄ ምኒልክ የተለያያኡት የትግራይ እና ኤርትራ ትግርኛ ተናጋሪ ሰሜን ኢትዮጵያውያን መዋሐድና አንድ መሆን?

❖ የሰሜን ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምስረታ?

_______________________________________

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: