Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 6, 2020
“አሁን ሠራዊቱ በፕሬዚደንት ትራምፕ ሳይሆን በድብቅ ኃይሎች ነው የሚታዘዘው፤ ኮሙኒስቶች መፈንቅለ መንግስት አድርገዋል፤ አሜሪካ አብቅቷላታል” ይለናል ክርስቲያኑ ዘጋቢ ሪክ ዋይልስ።
እንግዲህ በአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ይጀምራል ማለት ነው፤ ይህ ደግሞ ለመላው ዓለም ጣጣ ነው። “ሂዱ ንገሯቸው! አትንኳን በሏቸው! ኢትዮጵያን እንዲመሩ ያስቀመጣችኋቸውን ስጋዊ የኦሮሞ ፋሺስቶችን አስወግዷቸው!” ብለን ነበር። ለማንኛውም፤ እጅግ በጣም አስገራሚ የሆነ ዘመን ላይ እንገኛለን፤ ወገን!
________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Infos | Tagged: ሉሲፈራውያን, መንግስት, ባርነት, ባቢሎን, አሜሪካ, አረቦች, ኢትዮጵያ, ዘረኞች, የሤራ ፖለቲካ, የኦሮሞ እንቅስቃሴ, ድብቅ መንግስት, ፀረ-ኢትዮጵያ ሤራ, ፍርድ | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 6, 2020
በአክሱም ኃውልት አምሳያ ተሠርቶ በዋሽንግተን ከተማ የቆመው ታሪካዊ ሐውልት ትናንትና አስደናቂ መብረቅ ጎበኘው።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ባለፈው ጥቅምት ወር ላይ ይህን ቪዲዮ በተዘጋው ቻነሌ በኩል አቅርቤ ነበር። ቀጥሎ በድጋሚ አቀርበዋለሁ። በጥሞና እንከታተለው!
ረሳነው? | የአክሱም ሐውልት በመብረቅ የተመታበት ምስጢር
ከ82 ዓመታት በፊት የተሰረቀው የአክሱም ሐውልት፡ ሐሙስ፡ ጥቅምት18 ቀን1930 ዓ.ም እ.አ.አ ጥቅምት 28 ቀን 1937 ፡ በፋሺስቱ የኢጣሊያ መሪ በቤኒቶ ሙሶሊኒ ተመርቆ ሮም ከተማ ላይ በይፋ ተተከለ። ሐውልቱ የቀድሞው የአፍሪቃ ሚንስቴር ዋና ሕንፃ፡ በኋላም ላይ የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) ዋና መሥሪያ ቤት ከሆነው ህንፃ ፊት ለፊት እንዲቆም ተደረገ፤ (ልብ እንበል፤ ድርቅና ረሃብ ከኢትዮጵያ ጋር በተያያዘ እንዲታወቁ ፀረ–ኢትዮጵያ ሤራውን ጠነሰሱ)
ቍ.11 ያረፈበትን ሸሚዝ ለብሶ የነበረው ጀግናው ኢትዮጵያዊ አበበ ቢቂላ ልክ የአክሱም ሐውልት ጋር ሲደርስ ጫማውን አውልቆ ጣለ፤ የኦሎምፒክ ማራቶንን አሸነፈ፤ ፋሺስቶችን አዋረዳቸው። ኢትዮጵያን የያዘ አሸናፊ ነው!
ሰማይ ጠቀስ ፎቆች ሁሉ በአክሱም የአወቃቀር ንድፍ ነው የሚሠሩት። በኒው ዮርክ ከተማ ተሠርተው የነበሩት መንትያዎቹ የአለም ንግድ ማዕከል ሕንፃዎች በመሀመዳውያኑ የሽብር ጥቃት ፈራረሱ። አክሱም በሳባውያን የግማሽ ጨረቃ አምላክ “አልማቃህ” ላይ + ነጎድጓድ / መብረቅ…በሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ።
ኢጣልያ በዲያብሎሳዊ ቅጥፈትና በፈርኦናዊ ትዕቢት ሐውልቱ ይበላሻል፣ በመንገድ ላይ ሊፈራርስ ስለሚችል አልመልስም አለች።
የአክሱምን ሐውልት ለማስመለስ ኢትዮጵያ ጩኸቷን አሰማች፤ በኋላም ላይ በሮማው የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና እርሻ ድርጅት(FAO) ዋና መሥሪያ ቤት በሆነው ህንፃ ረሃብን የተመለከተ ስብሰባ ላይ ተግኘትው የነበሩት ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ኢጣሊያ ሐውልቱን ለኢትዮጵያ በፍጥነት እንድትመልስ ጥሪ አቀረቡ።
የአክሱም ሐውልት በመብረቅ ተመታ።
የኢጣልያ መንግስት የአክሱምን ሐውልት ለመመለስ ተስማማ፤ “ኡ!ኡ! ሌላ ጣጣ ሳይመጣብን ኧረ ቶሎ ውሰዱልን!” አለ፡ በድንጋጤ፡ የወቅቱ የኢጣልያ ጠቅላይ ሚንስትር ሲልቪዮ ቤርሉስኮኒ።
የአክሱም ሐውልት ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ።
በነገራችን ላይ፡ “ጉግል” ገብታችሁ በአማርኛው “የአክሱም ሐውልት(በሁሉም ‘ሐ‘ዎች)ጻፉ፤ 16ሺህ ፣ “አክሱም” በሚለው ደግሞ 294ሺህ የፍለጋ ውጤቶች ብቻ ይገኛሉ፤ አዎ! ስለ አክሱም እና ስለ አክሱም ሐውልት…ዋው! በላቲኑ ግን “The Obelisk of Axum” 107ሺህ ወይንም በ ”Axum“ 3ሚሊየን የፍለጋ ውጤቶች ይወጣሉ… አስገራሚ ነገር ነው!
_____________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: 9/11, መብረቅ, ሮም, ሽብር, ኒው ዮርክ, አሜሪካ, አክሱም, ኢትዮጵያ, ኢጣሊያ, ዋሽንግተን, የአክሱም ሐውልት, የኢትዮጵያ ጠላቶች, የእግዚአብሔር ቁጣ, ፋሺዝም, God's Judgment, Italy, Lightning, Rome, The Axum Obelisk | Leave a Comment »