Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2020
    M T W T F S S
     123
    45678910
    11121314151617
    18192021222324
    25262728293031
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

የ EBS “ማሕተብ-አውልቍ” ቅሌት ብዙ የሚጠቁመን ነገር አለ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 27, 2020

ይህ EBS/.. ኤስ የሠራው ቪዲዮ ነው። ካሜራው ወደ አቃቂ አድቬንቲስት አዳሪ ተማሪ ቤት አምርቶ ነበር። እዚያም የተዋሕዶ ተማሪዎች ወደዚህ ተማሪ ቤት ለመግባት ማህተባቸውን መበጠስ አለባቸው ፥ ሙስሊሞቹ ግን ከእነ ሂጃባቸው መግባት ተፈቅዶላቸዋል።

ግን እያየን ነው፤ የአህዛብን፣ የመናፍቃንን እና የዘረኞችን በተዋሕዶ ላይ ያነጣጠረውን ሕብረት?! ተመሳሳይ ላባ ያላቸው ወፎች አንድ ላይ ይበራሉ ፥ ተኩላውም ቀስ በቀስ ለምዱን እየገፈፈ ነው።

ከጥቂት ዓመታት በፊት፤ በጥምቀት ከተራ ፪ሺ፱ ዓ.ም፡ እ..አ በ1943 .ም በተቋቋመው የአቃቂ የአድቬንቲስት አዳሪ ተማሪ ቤት “ተማሪዎች” የሆኑት የተዋሕዶ ልጆች ከግቢው መውጣት ስላልተፈቀደላቸው፤ ወደ በሩ ተጠግተው፤ “የኛ!” እያሉ በመዘመር ለጥምቀት በዓል ከመንበራቸው በክብር የወጡትን ታቦታት ይቀበሏቸው ነበር። በወቅቱ ጠይቄ እንደተረዳሁት ከሆነ፡ የተዋሕዶ አዳሪ ተማሪዎች ውደ ትምህርት ቤቱ ሲመዘገቡ፡ ማሕተባቸውን እንዲያወልቁ ተደርገው ነው፤ አልያ መግባት አይችሉም።

የኢቢ ኤስ ቪዲዮ እራሱ እንደሚያሳየው መሀመዳውያኑ ግን ከነሂጃባቸው እንዲገቡ ተፈቅዶላቸዋል፤ ጉድ የሚያሰኝ አሳዛኝ ጉዳይ ነው። 21ኛው ክፍለ ዘመን ልክ እንደ ቅኝ ተገዢዎች ኢትዮጵያውያን በሃገራቸው መብትና ምጫ የላቸውም ፤ የተዋሕዶ በሆነቸው በሃገረ ኢትዮጵያ! ያው እንግዲህ የደቡባውያኑ የእነ አፄ ኃይለ ሥላሴ ፈረንጅ አፍቃሪነትና ሁሉን አቃፊነት እምቧይና እሾህ አፍርቶ ይታያል

_________________________

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: