Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2020
    M T W T F S S
     123
    45678910
    11121314151617
    18192021222324
    25262728293031
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

“አማራ አክቲቪስቶች” አቶ ልደቱንና እኅተ ማርያምን ለመፍረድ ቸኮላችሁ በታገቱት እህቶች ጉዳይ ግን ጭጭ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 24, 2020

የቀድሞዋ የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ጎልዳ ማይር የሚከተለውን ተናግረው ነበር፦

ልጆቻችንን በመግደላቸው አረቦችን ይቅር ማለት እንችላለን ፡፡ ልጆቻቸውን እንድንገድል ስለሚያስገድዱን እነሱን ይቅር ማለት አንችልም፡፡ ከአረቦች ጋር ሰላምን የምናመጣው እኛን ከሚጠሉን ይልቅ ልጆቻቸውን አብልጠው ሲወዱ ብቻ ነው ፡፡

We can forgive the Arabs for killing our children. We cannot forgive them for forcing us to kill their children. We will only have peace with the Arabs when they love their children more than they hate us”

ኢትዮጵያ አሁን ለምትገኝበት አሳዛኝ ሁኔታ ተጠያቂዎቹ በቅድሚያ ሰሜን ኢትዮጵያውያን ናቸው። በተለይ የትግራይ እና የአምሃራ ልሂቃን የተባሉት ይህችን የእግዚአብሔር ሃገር ለጠላቶቿ በሰፊ ሰፌድ በማስረከብ ላይ በመሆናቸው ትውልድ ይወቅሳቸዋል፤ በእግዚአብሔር ፊትም ይጠየቃሉ።

በተለይ የአማራ አክቲቪስት ነንየሚሉት በይበልጥ አሳፋሪዎች ናቸው፤ በዋቄዮአላህ መንፈስ ሥር የወደቁ ይመስላሉ፤ ሁሌ ከማይሆን ጠላት ጋር አብሮ መሰለፍ፣ ከራሳቸውን ቤተሰብ ይልቅ የማያውቁትን ቡዳ ሲያቀርቡ፣ ሲደግፉ፣ ሲያደንቁና ሲያሞካሹ መታየታቸው የተለመደ ነገር ሆኗል።

እስኪ ከሰሞኑ እንኩን የአቶ ልደቱ አያሌውን እና የእህተ ማርያምን ጉዳይ አስመልክቶ አማራን ነንየሚሉ ግለሰቦችና ሜዲያዎች ያለማቋረጥ የሚያካሂዱትን የስድብና የጥላቻ ዘመቻ ተከታተሉት፤ በጣም አሳዛኝና አሳፋሪ ነገር እያየንና እየሰማን ነው። ልጆቻቸውን ለሚገድሉት በእነ አብይ አህመድ፣ ለማ መገርሳና ጃዋር መሀመድ ላይ ያላሳዩትን ያህል ቁጣና ወኔ ነው በአቶ ልደቱና እህተ ማርያም ላይ በማሳየት ላይ የሚገኙት።

በእኔ በኩል፤ ዘውገኛ የሆኑትን አማራ ሜዲያትግሬ ሜዲያቅብርጥሴ የተባሉትን ሜዲያዎች ገብቼ ማየት መንፈሴን ያውከዋል፤ ግን ሰሞኑን እስኪ ልታዘብ፣ ነገሮችን ሞኒተር ላድርጋቸው በሚል ወኔ ስገባ በተለይ አማራየተባሉ ሜዲያዎች ለእኅተ ማርያምን ጉዳይ በጣም ሰፊ ሽፋን ሰጥተውት ይታያሉ፤ ያውም በሚያሳዝንና በሚቀፍ መልክ። ትግሬየተባሉት ሜዲያዎች ግን አንድም ነገር ስለ እኅተ ማርያም ሲዘግብ አላየሁም፤ ያውም እህተ ማርያም በትግሬ ኢትዮጵያውያን ላይ ነበር ጠንከር ያለ፤ ጽላተሙሴን ከአክሱም ለመንጠቅ እስከ መሻት ድረስ የደረስ ነቀፋና ትችት ስትሰጥ የነበረው።

ምን እየተካሄድ እንደሆነ እያየን ነው? ታዲያ “አማራነኝ የሚለው ኢትዮጵያዊ ምን ዓይነት የሞራልና የመንፈሳዊ ውድቀት ውስጥ እንደገባ እያየን አይደልምን? ለዚህ ምክኒያቱስ ምንድን ነው?

ወገን፤ ለሃገራችን ኢትዮጵያና ልጆቿ፣ ለቤተ ክርስቲያናችን እንደነ አብይ አህመድ፣ ብርሃኑ ነጋ፣ ሽመልስ አብዲሳ፣ ለማ መገርሳና ታከለ ኡማ ክምንዜውም የከፋ ጭካኔ፣ ውድቀትና ውርደት ያመጣ መንጋ የለም። የታመቀውን ቁጭትህን በእነ ልደቱ አያሌው እና እኅተ ማርያም ላይ ማውጣቱ ግብዝነትና ጨቅላነት ነው። እነ አብዮት አህመድ ናቸው እናቶችህን ከየቤታቸው የሚያፈናቅሉት፣ ወጣት ሴት ተማሪዎችህን የሚያግቱት፣ ጡታቸውን የሚቆርጡትና የሚገድሉት። ሕፃናቶችህ እኮ ኦሮሚያ በተሰኘው ሲዖል እየተበከሉብህ፣ እየተመረዙብህና እየታረዱብህ ነው፣ መንፈሳዊ አባቶችህም እንደ እብድ ውሻ ታድነው እየተደፉብህ ነው። ሰሞኑን እንኳን መምህር ምህረተአብ የትውልድ ከተማ በመቱ የሽመልስ አብዲሳ አውሬ ፖሊሶች የተዋሕዶ ልጆችህን ማህተብ በምላጭ እየበጠሱባቸው ነው፣ ሃይማኖታቸውን እንዲቀይሩ እያስገደዷቸው ነው። መሀንዲሶችህ፣ ሐኪሞችህ፣ የጦር መሪዎችህ ዓይንህ እያየ እየተረሸኑ ነው ፥ ልጆችህ፣ ሴቶችህ፣ አየርህ፣ ውሃህ፣ ወንዞችህ፣ አፈርህ፣ እህልህ፣ ጤፍህ፣ ዘይትህ፣ ዶሮዎችህ፣ በጎችህ ፍራፍሬህ፣ አየር መንገድህ፣ ባንክህ፣ ቴሌህ ፥ ባጠቃላይ ሃገርህ ለባዕዳውያኑ የታሪክ ጠላቶችህ እየተሸጡብህ ነው፤ አይኖችህ እያዩ ጆሮዎችህ እየሰሙ።

የምድር ሲዖል ባደረጓትና በተሰረቀችው ክልላቸው በተዋሕዶ ልጆች ላይ የሚካሄደውን ጭፍጨፋና የታገቱትን ሴት ተማሪዎች ጉዳይ አስመልክቶ ግን ቁጣህንና ወኔህን ከማሳየት ተቆጥብሃል፣ ለተቃውሞ ሰልፍ መውጣት እንኳን ፈርተሃል።

ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተሠራ ያለውን ተወዳዳሪ የሌለውን ወንጀል ለሚታዘብ የበቃ ሰው ሥልጣኑን የጨበጠው የአህዛብ መንጋ ለአንዲትም ቀን እንኳን በምኒሊክ ቤተ መንግስት መቆየት እንደሌለበት ይረዳል። እንዲያውም ከአብዮት አህመድ እስከ ጃዋር መህመድ ድረስ ያሉት የኢትዮጵያ ጠላቶች አገር ለቀው ሳይውጡ ዛሬውኑ በእሳት መጠረግ አለባቸው። ለኢትዮጵያ ከዚህ ሌላ መፍትሄ ስለማይኖር ኢትዮጵያን ለማዳን ሰሜን ኢትዮጵያውያን ተባበረውና ሊበላቸው የተዘጋጀውን አዞውን መቀለቡን አቁመውና ኢትዮጵያዊ የሆነውን የሠራዊቱን አካል አስተባብሮ በአውሬው መንግስት ላይ መፈንቅለ መንግስት በፍጥነት ማካሄድ ይኖርባቸዋል። ሌላ አማራጭ የለም፤ በምርጫ ሳጥን፣ ዲሞክራሲ፣ መብት ቅብርጥሴየሚባለው ሥጋዊ አካሄድ አይሠራም! ሥጋዊ የሆኑት የዋቄዮአላህ ልጆች ወይ አንገትህ ላይ ናቸው ወይም ደግሞ በእግርህ ሥር መረገጥ አለባቸው።

_________________________________

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: