Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2020
    M T W T F S S
     123
    45678910
    11121314151617
    18192021222324
    25262728293031
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for May 1st, 2020

የዘመነ ኮሮናን አጋጣሚ ባለመጠቀማችን የቤተ ክርስቲያንን ክብሯን ለባዕድ አሳልፈን ሰጠን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 1, 2020

አባቶቻችን “ቁጭ ብለው የሰቀሉትን ቍሞ ማውረድ ይከብዳል!” ያሉት ተረት ደረሰብን።

እጅህን ካልታጠብክ ትጠፋለህ የሚል ህግ ፈሪሳዊ ህግ ነው!

አሁንም ገና በትንሣኤ በመዘጋት ነገሩ የሚያበቃ እንዳይመስላችሁ። ምክኒያቱም በየአጋጣሚው ቤተ ክርስቲያንን ከማንደድ፣ ምዕመናንን ከመጉዳት እማይቆጠቡ አህዛብና መናፍቃን በየስልጣኑ ወንበር ላይ ባሉበት ዘመን ላይ በገዛ ቦታችን ደብዳቢ ጽፈን፡ “ቤተ ክርስቲያን ትዘጋ! ሰው በቤቱ ይዘጋ” ብለን” ይሄ እኮ የቤተ ክርስቲያን ሥራ አይደለም፤ እሷ ባትኖር መንግስት ማለቱ አይቀርም እኮ ፥ እውነቱ ግን መፍትሔው ያለው በእግዚአብሔር ዘንድ ብቻ ነው ፤ ንጉሥ የወደደውን ዘመን የወለደውን አትከተሉ!

በቃ! ቤተ ክርስቲያንን ክፈቱ! ዛሬውኑ ክፈቱ!

___________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ኃያሉ ጊዮርጊስ የተዋጋላትና ተዋሕዷውያን ደማቸውን ያፈሰሱባት ኢትዮጵያ የቤተ ክርስቲያን እርስት ናት

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 1, 2020

አዎ! ተራራዎቿ እና ሜዳዎቿ ፣ አፈሮቿ እና ውሃዎቿ ፣ ደኖቿ እና አታክልቶቿ ሁሉም የተዋሕዶ ኢትዮጵያውያን ደም የፈሰሰባቸው ውድ የቤተ ክርስቲያን ንብርቶች ናቸው። ስለዚህ ለማረስ፣ ሕንፃ፣ መንገድና አደባባይ ለመሥራት ዓለማዊው መንግስት ነው የቤተ ክርስቲያን ፈቃድ ማግኘት ያለበት። እስኪ በአዲስ አበባ ብቻ ተመልከቱት፤ የት ነው አንድ ዜጋ ንጹሕ አየር፣ ንጹህ ውሃ፣ ንጹህ ፍቅርና ደስታን የሚያገኘው? ልክ እንደዚህች በሚያምር ደን እንደተከበበችው እንደ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ባሉት የተቀደሱ ሥፍራዎች አየደለምን? ግን አደራ! የሠፈሮቹንም ስም “ፈረንሳይ”፣ “ጀርመን” ፣ “ፒኮክ” ፣ “ቼችኒያ” ወዘተ በማለት ጠላትን ለወረራ አንጋብዝ!

ተአምር ሠሪው ሰማዕት ሆይ ፤ ፈዋሴ ዱያን እንደመሆንህ ከወፍ በሽታ ፈውሰህ የምታድን ነህና ልምናችንን ጸሎታችንን ዘወትር ቸል ሳትል ስማን ከሱ በኢ የሚቆጠሩ ልዩ ልዩ ነገሮች ይተላለፋሉና።

ኃያሉ ጊዮርጊስ ሆይ፤ ድካም የማይሰማህ ትጉህ ገበሬ ነህና ዳግመኛ እንዳያጣሉንና እንዳይተናኮሉን ጠላቶቻችን እንደ ጢስ አጥነህ፤ እንደ ጉም አብነህ ፈጥነህ አጥፋቸው። በአንተ ዘንድ ባለሟልነትን በመናፍቃንና በአላውያን ዘንድ የመፈራትን ግርማ እንዳጎናጸፍከው ከእኛ የተዋሕዶ ልጆችም በግዙፍ አካልና በረቂቅ መንፈስ ሊተናኰሉን በሚመጡ ጠላቶቻችን ላይ ድል የመንሣትን አክሊል አቀዳጀን። አሜን።

የፈረሰኛው ሰማእት የቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤትና ምልጃ አይለየን!

_________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: