Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • April 2020
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    27282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

ጌታችሁ በምን ሰዓት እንዲመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 14, 2020

በእኛ ላይም የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ላከ፤ የቅድስት ቢተ ክርስቲያንህንም ደጆች በምሕረትና በሃይማኖት እንዲከፈቱ አድርግልን። እስከ መጨረሻዪቱ ሕቅታም ድረስ ልዩ ሦስትነትህን ማመንን ፈጽምልን።

የቤተክርስቲያን ሸምጋይ እና አስታራቂ ሆኖ የመጣው ልወደድባይ የአውሬው መንግስት ኮሮናን ተገን አድርጎ ሕዝበ ክርስቲያኑን ከቤተ ክርስቲያን ለማራቅ ከፍተኛ ሥራ እየሠራ እንደሆነ እያየነው ነው። የክርስቶስ ተቃዋሚው የቤተ ክርስቲያንን ቦታ ለመውረስ ተወዳጅነት እያጡ የመጡትን ቴሌቪዥን እና ኢንተርኔት ጣቢያዎች (ኢቢሲ፣ ፋና)የሰሙነ ሕማማት ሥርዓተ ጸሎት በቀጥታ በማስተላለፍ ላይ ይገኛል። የቤተ ክርስቲያንን እና ሜዲያዎቿን ኃላፊነት በመንጠቅ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፎች ይመታል ማለት ነው።

ሲጀመር ዲያብሎስ አስታራቂ ሆኖ እንዲገባብን መደረግ አልነበረበትም፤ ካሜራዎቹንም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንዲያስገባ መፈቀድ አልነበረበትም። መንግስትና ሜዲያዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየሠሩት ያሉት ወንጀል ለይቅርታ፣ ለዕርቅና ለንስሐ የሚያበቃ አይደለምና።

በደመራ ዕለት መስቀል አደባባይ አጥር ላይ የተላተመችውን የኢቢሲ ድሮን ካሜራ እናስታውሳለን? በሬውንስ? እነዚህ ነገሮች ያለምክኒያት አልተከሰቱም! ዛሬ ግራኝ አህመድ በክቡር መስቀሉ የተሰየመውን አደባባይ እና የጃን ሜዳን ጥምቀተ ባሕር ለመውረስና ያለመውንም አንጋፋ መስጊድ በቅርቡ ለመሥራት በመንቀሳቀስ ላይ ነው። በኮሮና ድራማ ተጠምደን ጸጥ ብለናል፤ አይደል! አዎ! የበሬውን አንጀት ለሞኙ ኢትዮጵያዊ ሰጥቶ አፉን ይዘጋና ሰንጋውን ለራሱ በማግበስበስ ላይ ነው። ትንሽ ከፊት ሲሆን ሀገር ያሳንሳል!

“….ሰዎች ጥቅም ወዳድ ናቸውና በጥቅም ሂድባቸውየሚፈልጉትን እያሳየህ ወደምትፈልገው ስፍራ ውሰድ እና ጣላቸውከዚያም በሬ ሆይ! ሳሩን አየህና ገደሉን ሳታይብለህ ተርትባቸውብሎን የለ ተሳላቂው አብዮት። በመስቀል አደባባይ ደመራ ዕለት በሬው የተላከውም በቤተ ክርስቲያን እና ክቡር መስቀሉ ላይ ለመሳለቅ ታስቦ ነበር። አንርሳው!

ወገኖቼ መታለሉ ይብቃ! ይብቃ! ይብቃ! ንቁ! እንንቃ! ነፍሱ እንዳይታወክበት የሚሻ የተዋሕዶ ልጅ ይህን የቀጥታ ስርጭት በዚህ ሰሙነ ሕማማት ከመከታተል መቆጠብ ይኖርበታል።

__________________________________________

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: