Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • April 2020
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    27282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

የክትባት ባለ እናት መሊንዳ ጌትስ | አፍሪቃን ቶሎ ካልከተብናት ሬሳዎች መንገድ ላይ ተጥለው ይታያሉ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 14, 2020

የቢል ጌትስ ባለቤት መሊንዳ ጌትስ፤ ስለ በሽታና ሞት እያወራች ትስቃለች፤ እንዲህም ትላለች፦

ክትባት፣ ክትባት፣ ክትባት ሌላ መፍትሔ የለም!!!“አፍሪቃውያንን” እኛ መርፌ ካልወጋናቸው ተስፋ የላቸውም። ልክ እንደ ኤኩዋዶር በቅርቡ በአፍሪካም ሬሳዎች በመንገድ ላይ እንደ ቆሻሻ ይወረወራሉ። የአፍሪቃ ወላጆች ጭንቀት እንቅልፍ ይነሳኛል።

ማማ አፍሪቃ” መሆኗ ነው። ባሏ ቢል ከማይክሮሶፍት ኃላፊነቱ የተሰናበተው ያለ ምክኒያት አልነበረም። ተመልከቱ፤ በአፍሪቃ 54 አገራት አሉ፤ እነዚህ አገራት በመልክ ዓምድር፣ በአየር ጸባይ፣ በታሪክ፣ በባሕል፣ በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በምጣኔ ሃብት እጅግ በጣም የተለያዩ አገራት ናቸው፤ ነገር ግን ሁሉም እንደ አንድ ሃገር “አፍሪቃ” እያሉ መጥራቱን ይመርጣሉ፤ እንደነርሱ፤ አፍሪቃ አህጉር ሳትሆን አንድ አገር ናት።

የሚገርመው ግን አፍሪቃ በኮሮና እምብዛም ያልተጠቃችው ብቸኛዋ አህጉር መሆኗ ነው። ይህ ደግሞ በጣም ያንገፈግፋቸዋል። ሁሉም የሚጠይቁት “ኮሮና በአፍሪቃ የኛን ያህል ለምን አልተስፋፋም?” የሚለውን ቅናትና ጥላቻ የተሞላበትን ጥያቄ ነው። እግዚአብሔር የአፍሪቃ ሃገራትን ይጠብቃቸው እንጂ ከዚህ በፊትም እንዳወሳሁት በአፍሪቃ ኮሮናን የመሰለ ወረርሽኝ ከተቀሰቀስ(ማድረጋቸውም አይቀርም) እነዚህ አረመኔዎች ለጉብኝትና አደን የሚቋምጡላቸውን የዱር አራዊቱን አስቀርተው መላውን አህጉር ከመጨፍጨፍ እንደማያመነቱ እርግጠኛ መሆን ይቻላል። ሰሞኑን በዶ/ር ቴዎድሮስ ላይ የተቀሰቀሰው የጥቃት ዘመቻ ይህንን ነው የሚጠቁመን።

__________________________

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: