Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • April 2020
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    27282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for April 10th, 2020

የፍጻሜው ዘመን ምልክቶች | የክትባት ባላባት ቢል ጌትስ ከተማ በቁራዎች ጨለመች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 10, 2020

ይህ ትልቅ ምልክት ነው! ! ልጆቻችሁን ክትባት አታስከትቡ! እየተባልን ነው።

መካና መዲና የርኵሳንና የተጠሉ ወፎች መጠጊያ ሆኑ፣ የብሪታኒያን ከተሞች ፍዬሎችና አጋዘኖች ወረሯቸው፤ አሁን ደግሞ በዩ.ኤስ አሜሪካዋ ዋሽንግተን ግዛት በሲዓትል /Seattle ከተማ አስፈሪ ቍራዎች ሰማዩን ሸፈኑት።

ይህች Seattle (አምስቱ ፌደላት (atete /አቴቴ ይሠራሉ)የተባለች በሰሜንምዕራብ አሜሪካ የምትገኝ ከተማ የእነዚህ አንጋፋ ተቋማት መቀመጫ ናት፦

👉 የቢል ጌትስ ማይክሮሶፍት Microsoft(ኮምፒውተር)

👉 የዓለም ኃብታሙ ሰው ጄፍ ቤሶስ “አማዞን” Amazon(ኢንተርኔት)

👉 የሰንሰለት ቡና ቤቶች ንግሥቷ “ስታርባክስ” Starbucks(ቡና)

👉 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሞግዚት “ቦይንግ” Boeing(ፋብሪካው)

👉 በአሜሪካ የተላላፊ በሽታዎች ምርምር ተቋም

👉 ቲ ኢሜጅስ Getty Images(ፎቶግራፍ አንሺ)

እነዚህ ሁሉ ተቋማት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ኢትዮጵያን ተኮር ሥራዎችን ይሠራሉ

የራሱን “ዊንዶውስ” ከቫይረስ ነፃ ማድረግ የተሳነውና፣ ምንም ዓይነት የህክምና ዕውቀት የሌለው የማይክሮሶፍት መስራችና ባለቤት ቢል ጌትስ የበሽታዎችን መንስኤና መፍትሒአቸውን አውቃለሁ በሚል እየቀባጠረ ዋንኛው የአውሬው የክትባት ሥርዓት ደጋፊና ልዑክ ለመሆን በቅቷል። በተለይ አፍሪቃውያን ሕፃናትን አንዴ ለእያንዳንዱ ህጻን ጨረርአፍላቂ ላፕቶፖችን “በነፃ” ይሰጣል መለስ ብሎ ደግሞ “ያለክትባት በርሃብ ያልቃሉ” ይላል። ምን አገባው?

/ር ቴዎድሮስ አድሃኖምን የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር እንዲሆኑ ሲመኙ ከነበሩት ግለሰቦች መካከል ቢል ጌትስ አንዱ ነው። ሰሞኑን እየተካሄደ ካለው የፀረቴዎድሮስ ዘመቻ ጀርባ የተለመደው ድራማ ነው የሚታየው። ኢአማንያኑ አሜሪካና ቻይና አብረው ነው የሚሠሩት፤ የኮሮና ቫይረስን ያመረቱት ሁለቱም በህብረት ነው፤ አሁን ወረርሽኙ ያስከተለውን ከፍተኛ ዕልቂትና የማህበረሰባዊምጣኔ ኃብታዊ ቀውስ ከራሳቸው ዘወር ለማድረግ በ ዶ/ር ቴዎድሮስ ላይ የሌባ ጣታቸውን ይጠቁማሉ። ጉዳዩ ከግለሰብ ቴዎድሮስ ጋር ሳይሆን ከኢትዮጵያ ጋር ነው። ጅራፍ እራሱ ገርፉ እራሱ ይጮኽና ውሻውን መጥፎ ስም ሰጥቶ ይደፋዋል። “በጣም ጥሩው መከላከያ ጥሩ አጥቂነት ነው” የሚለውን ስልት ይጠቀሙ የለ። የጫሩት እሳት እራሳቸውን ይፍጃቸው!

ተመሳሳይ ነገር በኢትዮጵያ የጦጣዎች ምክር ቤት ውስጥ አይተን ነበር። የዲያቆን ዳንኤል ድራማም በደንብ የተቀነባበረ ነበር፤ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እንታገላታላን፤ ጊዜው የእኛ ነው” ብለው ለማሳየት አቅደወት የነበረ ብሔራዊ ቲአትር ነበር እንጅ ተላላኪያቸው ከሆነው ከለዘብተኛው ዳንኤል ክብረት ችግር ኖሯቸው አይደለም፤ ሌላ ከሱ የጠነከረ የተዋሕዶ ሰው እንዳይመጣና እርሱ እንዲቆይ ከመሻት የተነሳ ነው። በመጨረሻም መርጠውታል እኮ!

በነገራችን ላይ በመምህር ምሕረተ አብ ጠሪነት ሲደወል የነበረው የማንቂያው ደወል ጸጥ ያለው ዲ/ን ዳንኤል ክብረት በጎፋ ቅዱስ ገብርኤል የማንቂያ ደወል ላይ ከተገኘበት ዕለት ጀምሮ ነበር። ከዚህ በኋላ የመምህር ምህረተ አብ ወደ ሰዶምና ገሞራ ላስ ቬጋስ (Sin City) ማምራት በወቅቱ ከንክኖኝ ነበር። “ተዋሕዷውያን ልክ መነቃቃት በጀመሩበት ሰሞን ስለምን ሃገሩን ትቶ ወደዚያ ሄደ? ዳንኤል ክብረት አሳስቶት ይሆን?” በሚል። ከሰዶም ውጡ ሊላቸው ከሆነ ጥሩ ፤ ሆኖም የማንቂያ ደወሉ መቀጠል ነበረበት ፤ የፈለገው ቢሆን ዛሬም መካሄድ አለበት ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ወደ ሲዖል የሚልክ ፀረኢትዮፕያ መንግስት የመከልከል ወይም ትዕዛዝ የመስጠት ሞራላዊ ልዕልና የለውም።

ለማንኛውም እግዚአብሔር ይጠብቀን! ከክትባት እንራቅ!

_____________________________________

Posted in Conspiracies, Curiosity, Ethiopia, Faith, Health | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: