Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • April 2020
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    27282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for April 5th, 2020

ኮሮና ኤይር | አየር መንገዳችን የኮሮናን ጅራት ተክትሎ መብረሩን ቀጥሏል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 5, 2020

ከመደበኛ ወደ ኮንትራት በረራ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኒው ኦርሊንስ መደበኛ በረራ የለውም። ዛሬ ግን አራት አውሮፕላኖች የከተማዋን አየር ማረፊያ ሞልተውት ታይተዋል። አየር መንገዱ ከመደበኛ በረራ ወደ ቻርተር/ኮንትራት በረራ ተሸጋግሯል ማለት ነው።

በደቡቡ ዩ.ኤስ.አሜሪካ ሉዊዚያና ግዛት የምትገኘዋ ኒው ኦርሊንስ በፈረንሳዮች የተቆረቆረች ሲሆን በአፍሪቃውያን የባርነት ንግድ ዘመን ከፍተኛ ሚና የተጫወተች ከተማ ናት። ከተማዋ መጀመሪያ የምትታወቀው በጃዝ ሙዚቃ ነበር፤ ቀስበቀስ ግን የስካር፣ የሽርሙጥና፣ የዕጽ ተገዢዎችና የግብረሰዶማውያን መናኸሪያ ለመሆን በቅታለች። ለዚህም ይመስላል እ..አ በ2005 .ም ከኢትዮጵያ ተራሮች የተነሳው ምስጢራዊ ነፋስ ካትሪናየተባለውን ኃይለኛ አውሎ ንፋስ ሠርቶ ኒው ኦርሊንስ ክፉኛ የመታት። 1400 ሰዎች ህይወታቸውን ሲያጡ በ90ቢሊየን ዶላር የሚገመት ንብረትም ወድሞ ነበር። ካትሪና – ኮሮና

በዛሬው ዕለት እንደታወቀው ኒው ኦርሊንስ በኮሮና ወረርሽ ከኒው ዮርክ ቀጥላ እየተጠቃች ያለች ከተማ ለመሆን በቅታለች።

ሆን ተብሎ ይመስላል፤ አየር መንገዳችንም ኮሮናን ተክትሎ መብረሩን ቀጥሏል። ይህ ለገንዘብ ብቻ ተብሎ የሚደረግ ነገር አይደለም፤ ከበስተጀርባው እጅግ በጣም ከፍተኛ ተንኮል አለ።

____________________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Health | Tagged: , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

መድኃኔ ዓለም | ተዋሕዷውያን ለተዋሕዶ ልጆች በተለየ መልክ መልካም ማድረግ ይገባቸዋል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 5, 2020

[፩ኛ ወደ ጢሞቴዎስ ምዕራፍ ፭፥፰]

ነገር ግን ለእርሱ ስለ ሆኑት ይልቁንም ስለ ቤተ ሰዎቹ የማያስብ ማንም ቢሆን፥ ሃይማኖትን የካደ ከማያምንም ሰው ይልቅ የሚከፋ ነው።”

ብዙዎች በሃይማኖት ከሚመሳሰሏቸው ጋር በማበርና አንድ ከመሆን ይልቅ ለጠላቶቻቸው ሲቆሙና ድጋፍ ሲሰጡ ይታያሉ። ይህ ትልቅ ስህተት ነው! የተዋሕዶ ልጅ ከሌሎች ማስቀደም ያለበት እንደርሱ ተዋሕዶ የሆኑትን ወገኖቹን ብሎም በተለየ መልክ መልካም አያያዝ ሊያደርግ የሚገባው ለመድኃኔ ዓለም ልጆች መሆን አለበት ፤ በተለይ በዚህ ከማይመስሉን ሁሉ መራቅ በሚገባን ዘመን። ማንነታቸውን ባለማወቅ ወይም እራሳቸውን በመጥላት፣ ወይም በምዕራቡ ለብ ለብ ለዘብተኝነት ስልተወሰዱና መሃልስፋሪያዊ ማንነት በመያዛቸው “ሁሉን አቃፊ” ለመሆን ሲወራጩ ይታያሉ። “ገለልተኝነት”፣ “ሚዛናዊነት” እና “ሁሉን አቃፊነት” ከላይ ቆንጆ የሚመስሉ ነገር ግን ውስጣቸው ከንቱ የሆኑና በዓላማየለሽኝነት ላይ የተመረኮዙና በስንፍና ቅመም የተከለሱ የለዘብተኛነት መገለጫ ከኮሮና የከፉ በሽታዎች ናቸው። አንድ ዜጋ ወይ ኢትዮጵያዊ ነው ወይም አይደለም ፥ ወይ ከተዋሕዶ ነው ወይም አይደለም ፥ ወይ ጥሩ ወይም መጥፎ ፥ ወይ በስትግራ ፣ ወይም በስተቀኝ ፥ ወይ በራድ ወይም ትኩስ ፣ ወይ ከእውነት ጋር ወይም ከሐስት ጋር ፥ ወይ ከበጉ ጋር ወይም ከፍየሎች ጋር ፥ ወይ ከመድኃኔ ዓለም ጋር ወይም ከዋቄዮአላህ/አዱኛ ፈይሳ ጋር።

አህዛብ የዋቄዮአላህ ልጆች ምንም እንኳን ፍቅረቢሶችና ብቻቸውንም ሲቀሩ እርስበርስ የሚነካከሱ ግብዞች ቢሆኑም ቅሉ ለጋራ ግባቸው ሲሉ ግን እርስበርስ ሲተባበሩ ይታያሉ፤ ነገራቸው ሁሉ በጥላቻ ላይ የተመረኮዘ ቢሆንም ግን ለዓላማቸው ሲሉ በአንድነት ይቆማሉ። ዓላማቸው ኢትዮጵያን፣ ተዋሕዶ ባሕሏን፣ ቁንቋዋን እና ሃይማኖቷን ለማጥፋት ስለሆነ ኢትዮጵያና አምላኳ እስካሉ ድረስ ከዚህ ዓላማቸው ፎቀቅ አይሉም። ልክ እንደ ነቀርሳ፤ የሚመገበው ጤናማ ሕዋሳት እስካሉ ድረስ እነርሱን እይተመገበ ይስፋፋል፤ ጤናማው ህዋሳት ሲያልቅ ነቀርሳው እራሱን በልቶ ይጠፋል።

የዘመናችን ተዋሕዷውያን ተገቢ በሆነ መልክ እርስበርስ እንዳይተባበሩና የራሳቸው የሆነውን ነገር ሁሉ እንዳያስቀድሙ እንቅፋት የሆኑባቸው ነገሮች፦ ማንነታቸውን በሚገባ አለመገንዘባቸው፣ መድኃኔ ዓለም የሰጣቸውን ፀጋና በረከት ዋጋ ባለማወቃቸው፣ ሃገራቸውና ሃይማኖታቸው ያሰቀመጧቸውን ተልዕኮዎችና ዓላማዎች ባለመከተላቸው እንዲሁም የአምላካቸውንና የራሳቸውን ጠላት በብልጠት እንዲያውቁ ባለመፍቀዳቸው ብሎም ለመዋጋት ቁርጠኝነት ባለማሳየታቸው ነው።

እስኪ እናስበው፤ የዋቄዮአላህ ልጆች ፍቅርአልባ በሆነ የጥላቻ መንፈስ ተነሳስተው ዲያብሎሳዊ አላማዎቻቸውን ሁሉ ለጊዜውም ቢሆን አንድ ባንድ በማሳካት ላይ ናቸው ፥ በሌላ በኩል፡ በፍቅር የተሞሉት የመድኃኔ ዓለም ልጆች ኃያሉን አምላካቸውን አጥብቀው በመያዝና ቅዱሳን ሠራዊቱንም ከጎናቸው በማሰለፍ እርስበርስ እየተሳሰቡና እየተደጋገፉ በአንድ ዓላማ ቢኖሩ ምን ያህል መሬት አንቀጥቅጥ ውጤት ሊያመጡ እንደሚችሉ። እስኪ እናስበው! አዎ! የመድኃኔ ዓለም ጠላት የሆኑት የዋቄዮአላህ ልጆች 150 ዓመት አይደለም አንድ ቀን እንኳን አይቆዩም ነበር።

___________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: