የወደቀው መልአክ በናይጄሪያ? | ተወርዋሪ ኮከብ በመናፍቃን ቸርቾች ላይ ወደቀ
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 31, 2020
የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ/ሉሲፈር ኩሬ በ አኩሬ?
ባለፈው ቅዳሜ በደቡብ ምዕራብ ናይጀሪያ አኩሬ ከተማ ከሰማይ ወረደ የተባለ ተወርዋሪ ኮከብ ወይም ሚትዮራይትስ /ሜትዮሮይድስ ቸርቾችንና መቶ የሚሆኑ ቤቶችን ማፈራረሱ ታውቋል። በቦታው ከፍተኛ የፍንዳታ ድምጽ ተሰምቶና ጥልቅ የሆነ አዲስ ኩሬ ተገኝቶም ነበር። ምንም እንኳን አንዳንዶች፡ የአገረ–ገዢውን ጨምሮ፡ ይህን ኃይለኛ ፍንዳታ የፈጠረው በጭነት መኪና የተወሰደ ቦምብ ነው ቢሉም ቅሉ በይፋ ግን፡ ባለሙያዎች አሁን እንዳረጋገጡትም፡ የ 43 ዲግሪዎች አንግል የሚሸፍን ስፍራ ላይ ኩሬ የሠራ ሜትዮሮይድስ / ሚትዮራይትስ ወይም ተወርዋሪ ኮከብ ነው።
በሰማይ ላይ የሚመላለሱ ልዩ ልዩ የሰማይ ሠራዊት ከዋክብት ተወርዋሪ ኮከብ ወይንም ሚትዮራይትስ/ ሜትዮሮይድስ የሚባሉት የሚባሉት ድንጋያማ አለቶች የኮሜትና አስትሮይዶች ቅሪቶች ናቸው። ኮሜትም አስትሮይድም ግዙፍ አለቶች ናቸው። እነዚህ አካላት ወደ መሬት ወይም ወደ ሌላ አካል ቀረብ ሲሉ እየተሰባበሩ፣ እየተሰባበሩ ይመጡና፤ መሬት በፀሐይ ዙሪያ ስትሽከረከር እነርሱን ስለምትስብ፣ ወደመሬት እየመጡ ብዙዎቹ ተቃጥለው ያልቃሉ።
የሚገርም ነው፤ ባለፈው ዓመት ላይ በዚህችው አኩሬ ከተማ የአንድ ዓመት ህፃን ልጅ በማምለኪያው ቦታ ተቀብሯል በሚል ያልተጣራ ወሬ ሰልፈኞች ሌላ የመናፍቃን ቸርች አቃጥለው ነበር ። ህፃኑ በቸርች ውስጥ ከእናቱ ጋር የታየው ከወር በፊት ሲሆን፤ ከቸርቹ ሳይወጣም በዚያው የውሃ ሽታ ሆኖ ቀርቶ ነበር።
Leave a Reply