Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • March 2020
    M T W T F S S
     1
    2345678
    9101112131415
    16171819202122
    23242526272829
    3031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for March 6th, 2020

እግዚአብሔር መልስ አለው | አሳቤ ታግታ አሊስ እና አይሻ በሰላም ትምህርታቸውን ሊቀጥሉ?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 6, 2020

ከደምቢዶሎ ከጠፉት ህፃናት ተማሪዎች መካከል አንዷ “አሳቤ አየለ አለም “ ናት። አዎ! በአሁኑ ሰዓት በዚህ አለም አሳባችን ሊያይል የሚገባው በእነዚህ ምስኪን ልጆች ጉዳይ ላይ መሆን ነበረበት፤ ሆኖም የኛዎቹ ወንጀለኞች የመጠረጊያ ሰዓታቸው እስኪደርስ ድረስ ዝምታውን መርጠዋል፣ አለምም ጆሮ ዳባ ብላለች። እግዚአብሔር ግን ዝም አይልም!

በኮሮና ቫይረስ ምክኒያት በመላው ዓለም ከአምስት መቶ ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ወደ ትህምርት ቤት መሄድ አልቻሉም። አሜሪካ፣ ብሪታኒያ እና አረቢያ ትምህርት ቤቶችን በመዝጋት ላይ ናቸው።

ለመሆኑ በደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ከተሰወሩት እህቶቻችን ጋር አብረው ሲማሩ የነበሩት ኦሮሞ ተማሪዎች ትምህርታቸውን በሰላም ቀጥለዋልን? ጉዳዩን በማስመልከት ወደ ዩኒቨርሲቲው ሄዶ ሊመረምር፣ ሊያጣራና ሊጠይቅ የሚችል አንድም ተቆርቆሬ ሜዲያ ወይም ግለሰብ የለም? !

____________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

አብዮት አህመድ አንድ ትውልድ የቀጠፈውን ኦሮሞውን መንግስቱን ለመመለስ “ካራማራን” አነሳ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 6, 2020

ያውም በአድዋ መታሰቢያ በዓል ማግስት። እያየን ነው? እባቡ አብዮት የመስቀል ደመራን በዓል በኢሬቻ፣ የአድዋን ደግሞ በካራማራ ለመተካት ሰውን ቀስ በቀስ በማለማመድ ላይ ይገኛል።

ሞኙ ኢትዮጲያዊ ባለፈው ታሪክ ሂደት ላይ እንዲጠመድና ለፉት ነገሥታት ስለሠሩት እንዲጨቃጨቅ ይደረጋል፤ እነዚህ የኢትዮጵያ ጠላቶች ግን በጀት ፍጥነት ሃገራችንን በመሸጥ እና በመቋረስ ላይ ይገኛሉ። እነዚህ ታሪክ የሌላቸው ወሮበሎች ታሪክህን በመስረቅ ታሪክ ለመስራት ቆርጠው ተነስተዋል። ወጣቱ ያለቸው አንዲት ሃገ ር ኢትዮጵያ ብቻ ናት፤ ነገር ግን አባቶቹ ያቆዩለትን ይህችን ሃገር ከጥፋት ከማዳንና እራሱንም ከመከላከል ይልቅ እንደተመቸው ድብ የሦስት ወር እንቅልፍን መርጧል፤ ይህን ወጣት ምን እንዳደረጉት፣ በምን በክለው እንዳስተኙት ለማወቅ ከባድ ነው። ዲያስፐራ ባለው ሃገርወዳድ ከበስተጀርባ አንድ ኢትዮጵያዊ የጥላ መንግስት (Shadow Government) በይፋ ተመሥርቶ ህዝቡና ኢትዮጵያዊ የሆነው የሠራዊቱ አባል ለአመፅ እስካልተቀሰቀሰ ድረስ እንደምናየው የኢትዮጵያ ልጆች የወሮበሎቹ የጠላት ቅጥረኞች መጫወቻ መሆኑን ይቀጥላሉ።

እስኪ ተመልከቱ ወገኖቼ 20 ልጃገረድ ተማሪዎች ለ80 ቀናት ያህል ታግተዋል፤ የነርሱን ጉዳይ በማስመልከት ተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ የማይገባቸውና ብቃት የሌላቸው፤ ወይንም ህን ተብለው የተመረጡ የግራኝ አህመድ ደጋፊዎች አንድ የዝግጅት ኮሜቴ እንዲያቋቁሙ ተደረጉ፤ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ የተቃውሞ ሰልፉ እንዳይካሄድ ተወሰነ፤ ልክ እንደ መስከረም ፬ቱ። በሌላ በኩል ግን ወጣቱ ልክ ሆዱ እንደሞላና እንቅልፍ እንደጠገበ ሰው በአደባባይ ወጥቶ እንዲጨፍርና በዓላትን ጸጥ ብሎ እንዲያከብር ፈቅደውለታል፤ በዚህም አንገብጋቢ የሆኑት ጉዳዮች እንዲረሱና ሁሉም ነገር ኖርማል እንደሆነ ተደርጎ እንዲቆጠር ለማድረግ እየተሞከረ ነው። በአደዋ መታሰቢያ ሆነ በካራማራው በዓላት ላይ የታገቱትን ምናልባትም የተገደሉትን እህቶቻችንን የሚያስታውስ

አንድ መፈክር እንኳን ይዞ የወጣ ሰው የለም። በየጎዳናው እየዞሩ የበዓሉን ተሳታፊዎች ሲጠይቁ የነበሩት “ገለልተኛ” የሚባሉት ሜዲያዎች እንኳን በዓላትን ለማክበር እድሉን ያላገኙትን የታገቱት እህቶቻችን ጉዳይ አስመልክቶ ጥያቄዎችን ሲጠይቁ አልተሰሙም? ይህ ምን ዓይነት ደካማ ትውልድ ቢሆን ነው?

_______________________________

Posted in Ethiopia, Infos, Life | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የግራኝ አህመድ መንግስታዊ ሽብር በ እስክንድር ነጋ ላይ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 6, 2020

29ኛ ጊዜ እንዲሰለጥኑ ከተደረጉት የኦሮሚያ ልዩ ሃይል ውርንጭላዎች አንዱ ዛሬ በአዲስ አበባ እስንድርን በድጋሚ ተተናኮለው። ለመጭው “ምርጫ” እየተለማመዱ ነው … ጦርነት ውስጥ እንገባለን ብሏል ገዳይ አብይ…

____________________________

Posted in Ethiopia, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: