Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • March 2020
    M T W T F S S
     1
    2345678
    9101112131415
    16171819202122
    23242526272829
    3031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for March 1st, 2020

ኢትዮጵያ ማለት ድል ማለት ነው | ቀነኒሳ ሬከርዱን ሰበረ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 1, 2020

ኢትዮጵያን ለታሪካዊ ጠላቶቿ እንዳሻው አሳልፎ በመስጠት ላይ ባለው አብዮት አህመድ መንግስት እጅ የታገቱትን፡ ምናልባትም የተገደሉትን እህቶቻችንን እያስታወሰን!

በዛሬው ዕለት በለንደን በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ሩጫ የቀድሞውን አጭበርባሪ የብርታኒያ ሶማሌ ሬከርድ (61:14)ነበር 60 ድቂቃ ከ22 ሰከንድ በማስቆጠር የሰበረው። ባለፈው ሳምንት አባቤል የሻነህ ለታገቱት እህቶቿ ሮጣ የግማሽ ማራቶን ዓለም ሬከረድን መስበሯን እናስታውሳለን።

ይህ የኢትዮጵያ የድል ወር ነው፤ የኢትዮጵያ ጠላቶች ድል መመታት የጀምሩበት ወር ነው፤ ከኢትዮጵያና እግዚአብሔር አምላኳ ጋር የሚሰለፍ ፈጠነም ዘገየም ሁሌ ድል ይቀዳጃል፤ ስለዚህ በኢትዮጵያ ላይ የተነሱት ጠላቶቿ ሁሉ አንድ ባንድ በቅርቡ መምበርከካቸው የማይቀር ነው። ወይ ከኢትዮጵያ ጋር ነን ወይም ደግሞ አጥብታ ያሳደገቻቸውን ጡቷን ከሚነክሷት ከይሲ ከሃዲዎች ጋር ነን።

_______________________________

Posted in Ethiopia, Infos | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የማንቂያ ደወል | ተዋሕዶ በጨለማው ውስጥ ታበራልችና ጧፋችሁን ከፍ አድርጉ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 1, 2020

[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፫፥፲፭]

የአውሬው ምስል ሊናገር እንኳ ለአውሬውም ምስል የማይሰግዱለትን ሁሉ ሊያስገድላቸው፥ ለአውሬው ምስል ትንፋሽ እንዲሰጠው ተሰጠው።

እግዚአብሔር ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ሁሉንም ይጠብቃቸው። የፍጻሜ ዘመን ላይ ደርሰናል፤ የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢታዊ ምስክርነት የፍጻሜ ዘመን ቃጭል እንደሆነ እያየን ነው።

የኮሮና ቫይራስ ክስተት ባስከተለው ስጋት በቻይና፣ በደቡብ ኮሪያ፣ በጣልያን ዓብያተ ክርስቲያናት በሮቻቸውን ዘግተዋል፤ የተለመደውን የሰንበት አገልግሎት ሁሉ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ይህን የማንቂያ ደወል ስነ ሥርዓት ስመለከት ብልጭ ብሎ የሚታየኝ ዲያብሎስ በዚህ ሁሉ ብርሃን እንዴት ቅጥል እንደሚል ነው። ከሳምንታ በፊት በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን የተከሰተው ይህ ነበር። “ይህች ዓለም የኔ ነች” ብሎ የሚያምነው ዲያብሎስ አይተኛም፣ መሸነፍን አይወድም፤ ዛሬም በንዴት እንዳጓራ ነው፤ ስለዚህ እንዲህ የመሳሰሉትን የፍቅር፣ የሰላምና የብርሃን መድረኮችን፣ እንዲሁም ክርስቲያናዊ አገልግሎቶችን ሁሉ ከቤተ ክርስቲያን ለማራቅ የተቻለውን ሁሉ ይሞክራል።

ቅዱስ ዮሐንስ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ፡፡” ፣ “ከእኔ በኋላ የሚመጣው በመንፈስ ቅዱስ እና በእሳት ያጠምቃችኋል”፣ “የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ እነሆ” እያለ ምሥጢራትን / ምስጢረ ጥምቀት፣ ምስጢረ ንስሐን እና ምስጢረ ቁርባንን / እንድንካፈል ያስተምረናል፡፡

ጥምቀት፣ ቁርባን፣ ንስሐ ስንት መንፈሳዊ ሀብትና ጸጋ እንደሁም ከፍ ያለ የእግዚአብሔር ልጆች ክብር ስለሚሰጡን በተለይ በአሁኑ ጊዜ ተቀዳሚዎቹ የዲያብሎስ ጥቃት ዒላማዎች ናቸው። ባሕረ ጥምቀተን በመከልከል፣ የጥምቀት በዓልን በመተናኮል፣ ፀበላቱንና የሕይወት ህብስትን በመመረዝ፣ ብሎም ለንስሐ የተዘጋጁትን የክርስቶስ ልጆች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ በመግደል በፀረቤተ ክርስቲያን ዘመቻው ዲያብሎስ ምን ያህል ርቆ ለመሄድ እንደበቃ ዓይናችን እያየው ጆሮአችንም እየሰማው ነው።

በድጋሚ እግዚአብሔር ይጠብቀን እንጂ በቀጣዩና በቅርቡ ዲያብሎስ አውሬው በሃገራችን ሊፈጽመው ያቀደው ክስተት እርሱን የማይቀበለውንና ለእርሱ የማይሰግድለትን ሕዝበ ክርስቲያኑን ከቤተ ክርስቲያን ማራቅ ለዚህም እንደ ኮሮና ቫይረስ የመሳሰሉትን ተላላፊ በሽታዎች ከማሰራጨት ጋር የተያያዘ ነው። ልክ ዛሬ በቻይና፣ ደቡብ ኮርያ እና ጣልያን እንደሆነው በሃገራችንም ዓብያተ ክርስቲያናት በሮቻቸውን የሚዘጉበት፣ የሰንበት ቅዳሴዎች የሚቋረጡበትና እነደእነዚህ የመሳሰሉት ድንቅ “የማንቂያ ደወል መርሀ ግብራት” የሚቆሙበት ጊዜ ሩቅ አይደለም። እግዚአብሔር እስከፈቀደልን ድረስ እንዲህ በትጋት እንቀጥልበታለን፤ ነገር ግን ለሁሉም ነገር አስቀድመን ብንዘጋጅ ጥሩ ነው!

የሚገርም ነው፤ “የማንቂያው ደወል መርሐ ግብር” በብዛት በዓርብ ዕለት ነው የሚካሄደው። ይህም በተጨማሪ ትልቅ “የማንቂያ መልዕክት” ይኖረዋል። በዚህ ዕለት የአዲስ ኪዳን ሥርዓት ክቡር ደሙ የፈሰሰበት የሕይወት ህብስት ቅዱስ ሥጋው የተቆረሰበት ዐረፍተ ማእከል የተናደበት እጸ መድኃኒት ቅዱስ መስቀሉ ተሰጠን። የክርስቶስ ተቃዋሚው፣ የመስቀሉ ጠላት አውሬው ግን የሚሰግዱለትን ልጆቹን (ሙስሊሞችን) በየመስጊዱ በዚሁ ዕለት ለመሰብሰብ ሆን ብሎ ይህን ዓርብ ዕለት መርጦታል። የእኛ የመንቂያ ቀን አርብ የእረፍት ቀን ሰንበት፤ የአውሬው “የዕረፍትና” ድል የተነሳበት ቀን ዓርብ ነው።

2012 – የኢትዮጵያ ግመሎች – ሳውዲ አረቢያ – ኮሮና ቫይረስ

በነገራችን ላይ፤ ኮሮና ቫይረስ አሁን ሁላችንም እንደሰማነው በቻያና መቀስቀሱን ነው። ይህም ሆን ተብሎ የተደረገ ነው። ነገር ግን ኮሮና ቫይረስ የጀመረው ከሰባት ዓመታት በፊት፡ በአውሮፓውያኑ 2012 .ም ላይ በሳውዲ አረቢያ ነው (ከኢትዮጵያ ወደ ሳውዲ የተላኩ ግመሎች ያመጡት ፤ “MERS‐CoV / መርስኮሮናቫይረስ”)። በፈረንጁም በኛም 2012 ብዙ ነገሮች ያየንበት / የምናይበት ቁልፍ ዓመት ነው።

_________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: