Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • February 2020
    M T W T F S S
     12
    3456789
    10111213141516
    17181920212223
    242526272829  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for February 24th, 2020

በደምቢደሎ የጠፉት ሳይገኙ ሌሎች ሴት ተማሪዎች ታግተው በመደፈር ላይ ናቸው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 24, 2020

ገና ያልተወራልትና ያልተሰማ ብዙ ጉድ እንደሚኖር አንጠራጠረ። ሰዉ በአገሩ እዴት ይህን ያህል ይሰቃያል? እስክ መቼ ነው ኢትዮጵያ የዲያብሎስ መፈንጫ የምትሆነው? ይሄን እርኩስ መንፈስንና መጥፎ ዕድልን ይዞ የመጣውን የወሮበሎች ስብስብ መንግስት በእሳት ሊጠርግ የሚችል አንድ ቆፍጣና አርበኛ እንኳ ይጥፋ? ቤተክሕነትስ ባለፈው ሳምትን መግለጫዋ ላይ ወጣት ሴት ምዕመናኗ እንዲህ እልም ብለው ሲጠፉ ጉዳዩን አስመልክቶ አንድም ቃል ትንፍሽ ያላሉበት ምክኒያት ምንድን ነው? የኢትዮጵያን ስም ለማጠለሸትና ኢትዮጵያውያን በጭካኔ ከአረቦች እንደማይተናነሱ ለማሳየት ሲባል በተዘጋጀው በዚህ ዲያብሎሳዊ አጀንዳ ላይ እንዴት ሁሉም አካል ተባባሪ ሊሆን ቻለ? እንደው ይህ ለቲዲ አፍሮ ኮንሰርት የሚወጣበት ወቅት ነውን? በሃገራችን እየተካሄደ ያለው ነገር ሁሉ እጅግ በጣም አሳዛኝና ደም የሚያፈላ ነው! ይህች እግዚአብሔር የሚያውቃት፣ እኛም የምናውቃት ኢትዮጵያ አይደለችምና እርስታችን ኢትዮጵያን በፍጥነት ከአውሬው መንጋጋ አውጥተን ልናስመልሳት ግድ ነው። እግዚአብሔር ይርዳን!

____________________________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ውቡ መካነ ሕይወት የአቃቂ ቃሊቲ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 24, 2020

፲፱፻፶፰ /1958 .ም ተመሠረተ። የቤተ ክርስቲያኑ አሠሪ/አስተካይ ወ/ሮ አቦነሽ አንበርብር ነበሩ

_____________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

በፈረንጆቹ FEB 24 — በ124ኛ ዓመት የአድዋ ድል መታሰቢያ ኮሮና ቫይረስ ጣልያን ገባ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 24, 2020

አውሮፓዊ ወይም ካውኬዢያ ዝርያ የሌለውን የዓለማችንን ነዋሪ ሕዝብ ቁጥር ለመቀነስ ያዘጋጁት ቫይረስ በእራሳቸው ላይ እየመጣባቸው ይሆን?

ለማንም ክፉን አንመኝም፤ ነገር ግን መሆን ያለበት ይፈጸም ዘንድ ግድ ነው።

ከስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አንስቶ በተለይ በአውሮፓ እና አረቢያ በብዙ መቶ ሚሊየን ሰዎችን ሕይወት ሲቀጥፉ የነበሩት የወረርሽኝ መቅሰፍቶች የመጡት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከኢትዮጵያ (አባይ ወንዝ) ተነስተው እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁሙናል።

ለምሳሌ፦

1. የጁስቲያን ወረርሽኝ ( 527 እስከ 565 .)

የጁስቲያን ወረርሽኝ በመባል የሚታወቅ ሲሆን ከ ዓመታት ድረስ ለ 60 ዓመታት ያህል ቆይቷል።

ግብፅ እና የምሥራቅ የሮማ ግዛት (ባይዛንታይን) እንዲሁ ከከባድ በሽታ አላመለጡም ፡፡ ወረርሽኙ ከፍ ብሎ ፣ ወረርሽኙ በሰፊው ህዝብ ላይ በቆመበት ጊዜ 5000 ሰዎች በየቀኑ በከተማ ውስጥ ይሞቱ ነበር ፣ ጊዜ የሟቾች ቁጥር ወደ 10 ሺህ ሰዎች ደርሶ ነበር። ወረርሽኙ በምሥራቅ ሃገራት100 ሚሊዮን ሰዎች እና በአውሮፓ 25 ሚሊዮን ሰዎች ሕይወትን ቀጥፎ ነበር፡፡

2. ጥቁር ሞት

በጣም ዝነኛ ከሆኑት ቸነፈር ወረርሽኞች መካከል ጥቁር ሞት ተብሎ የሚጠራው አንዱ ነው። ይህ ወረርሽኝ የአየር ንብረት ቅዝቀዛ ውጤት ነበር ፡፡ ጉንፋን እና ረሃብ የመቅሰፍቱ መገለጫዎች ነበሩ፡፡ በ 1320 .ም የበሽታው የመጀመሪያ ጉዳዮች ተመዝግበዋል ፡፡ በመጀመሪያ ፣ ወረርሽኙ ቻይናንና ህንድን ካራቆተ በኋላ ፣ እ..አበ 1341 በታላቁ የሐር መንገድን ተከትሎ ወደ ዶን እና የታችኛው ቮልጋ ወንዞች ጫፍ ላይ ደረሰ ፡፡ በሽታው ወደ ካውካሰስ ተራሮች እና ወደ ክራይሚያ አካባቢ ሄዶ ከዚያም በመርከቦች መጀመሪያ በጣሊያኗ ጄኖዋ ወደብ ከዚያም ወደ መላው አውሮፓ፤ በቆስጥንጥንያ ፣ በባልካን ሃገራት፣ በቆጵሮስ እና በመካከለኛው ምስራቅ ተሰራጨ፡፡

በጥቁር ሞት ወረርሽኝ ሳቢያ የሟቾች ቁጥር 60 ሚሊዮን ህዝብ እንደሚገመት ይታወቃል፡፡

3. የስፔን ጉንፋን የሚል ስያሜ የተሰጠው ወረረሽኝ በፈረንጆቹ ከ በ 1918 እስከ1919 .ም በመላው ዓለም ወደ 50 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ገድሎ ነበር።

የብዙዎቹ የእነዚህ ቸነፈር ወረርሽኞች መነሻዎች ኢትዮጵያ (አባይ ወንዝ) እንደሆነች ተመራማሪዎች ይጠቁማሉ።

እግዚአብሔር የጥንታውያኑን እስራኤላውያን ልምድ በመጨረሻ ዘመን ላይ የሚኖሩ ሕዝቦቹ እንደ ምሳሌ አድርገው እንዲጠቀሙበት ሰጥቷቸዋል፡፡ ግብፃውያኑ በባርነት ይዘዋቸው የነበሩትን እስራኤላውያን ለመልቀቅ አሻፈረኝ ባሉ ጊዜ መቅሰፍት ወረደባቸው፡፡ መቅሰፍቱ በምድረ ግብፅ ቢወርድም እስራኤላውያኑን ግን አልነካቸውም ነበር ፡፡ እናም ሳይወዱ በግድ ለቀቋቸው፡፡ በመጨረሻው ዘመን የምትገኘው ቤተ ክርስቲያን ከሚወርደው ቁጣና መቅሰፍት የተጠበቀች ናት፡፡

መቅሰፍቶቹ ወርደው ከማብቃታቸው በፊት ወደ ሰማያዊው መቅደስ የሚገባ ሰው አይኖርም።[ራዕ ፲፭፥፰]

ከእግዚአብሔርም ክብርና ከኃይሉ ጢስ በመቅደሱ ሞላበት፥ የሰባቱ መላእክት ሰባቱ መቅሰፍት እስኪፈጸሙ ድረስ አንድ እንኳ ወደ መቅደሱ ይገባ ዘንድ አልቻለም። [2፪ ተሰ ፪፥፩፡፪]

ምዕራባውያኑ የልደት በዓል በመጣ ቁጥር „Do They Know it’s Christmas?“ / “የገና በዓል እንደሆነ ያውቃሉን?“ ብለው በመዝፈን የኢትዮጵያን ክብር ዝቅ ለማድረግ ሲሞክሩ 36 አመት ሞላቸው። ታዲያ አሁን እኛም “የካቲት ፳፫ ቀን ፲፰፻፹፰ ዓ. እና ‎አድዋን ያውቃሉን?” እያልን ብንዘምር አይገባንምን?

ጣልያኖችና አውሮፓውያን በጣም ተደናግጠዋል? እስክ አሁን በጣልያን ብቻ አምስት ሰዎች መሞታቸው ታውቋል። ታሪካዊዎቹ የጣልያን ከተሞች የሙት ከተሞች መስለዋል፤ 11 ከተሞች ተዘግተዋል።

የሁዳዴ ጾም ከመግባቱ በፊት ለዘመናት ሲካሄድ የነበረው ዝነኛው የቬኒስ ከተማ ካርነቫል በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲሠረዝ ተደርጓል፤ ባዶ መንገዶች፣ ባዶ ሱቆች ባዶ ባቡር ጣቢያዎች

______________________________

Posted in Ethiopia, Faith, Health | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የታገቱትንና የተገደሉትን በማስታወስ “አቤቱ የሆነብንን አስብ!” ብለን በመጮህ ወደ ኪዳነ ምሕረት እንቅረብ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 24, 2020

እህቶቻችን ከጠፉ ልክ ዛሬ ፹ (ሰማንያ) ቀናት ሆነዋቸዋል።

ባለፈው ቅዳሜ በመስቀል አደባባይ ወደ ተካሄድው የቴዲ አፍሮ የሙዚቃ ኮንሰርት የአዲስ አበባ ወጣቶች ምን ፈልገው፣ ምን አቅደው እንደሄዱና ለሃገራቸውም ምን በጎ ነገር እንዳመጡም የማውቀው ነገር የለም። ነገር ግን እህቶቻችን ከደንቢደሎ ዩኒቨርሲቲ እልም ብለው በጠፉበት ማግስት፤ ተዋሕዶ የአዲስ አበባ ልጆች በቤተ ክርስቲያናቸው ውስጥ በግፍ በተረሸኑበት ማግስት፤ ጌታችን በተሰቀለበት መስቀል ስም በተሰየመበት ቦታ ላይ ለዳንኪራ እና ጭፈራ በመውጣት የመምህር ምሕረተአብን የማንቂያ ደወል ለማቆምና የገዳይ አብይን አጀንዳ ለማስፈጸም ወጥተው ከሆነ እጅግ በጣም ነው የማዝነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰጠን የመስቀል ስር ስጦታ የሆነችው ውዷ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም እንደ እናትነቷ አብዝታ ታዝንባቸዋለች።

ይህ ዕለት እናታችን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ከልጇ ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ቀን ነው። የእመቤታችን ቃል ኪዳን ለየት ያለ ነው። ለየት የሚለውም በሁለት ዐበይት ምክንያቶች ነው። የመጀመሪያው እርሷ ምልዕተ ፀጋ በመሆኗና ፍጽምት ርህርህተ ሕሊና ከመሆንዋ የተነሣ ስለ ሰው ልጆች አብዝታ የማለደች እናት እና ክርስቲያኖች ሁሉ ይድኑ ዘንድ ከሌሎቹ በተለየ የለመነች በመሆንዋ ነው።እንኳን እግዚአብሔር ጨካኙ ዳኛ እንኳን አብዝታ ለለመነችው መበለት ያደረገውን እናውቃለንና።(ሉቃ. ፲፰፡፩)

ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ወላዲተ አምላክ ለመባል የበቃች ከእርስዋ በቀር ሌላ የሌለ፤ በዚህም መልዕልተ ፍጡራን ትሆን ዘንድ አምላክ ያከበራት በመሆንዋ ልዩ ቃል ኪዳን ይገባላት ዘንድ የተገባት ናት። ለአምላክ እናትነት(ልዩ) ሆና መመረጧን ለሚያምን ሁሉ ልዩ ቃል ኪዳን መቀበሏ ጥያቄ አይሆንበትም። ስለዚህም ልዩ ቃል ኪዳን ተገብቶላታል። ነቢዪ ኢሳይያስ ወይወጽእ እምጽዮን መድኅን ወየዐትት ኃጢአተ እም ያዕቆብ ወዛቲ ይእቲ ኪዳኖሙ እንተ እምኀቤየ ይቤ እግዚአብሔር፦ መድኅን (ክርስቶስ) ከጽዮን ይወጣል (ከእመቤታችን ይወለዳል)፣ ኃጢአትንም ከያዕቆብ (ከእስራኤል ዘነፍስ) ያርቃል፤ ለእስራኤል የማልሁላቸው መሐላ የገባሁላቸው ቃልኪዳንም ይህቺ ናት፤ ሲል እንደተናገረ እግዚአብሔር ልዩ ውልና ስምምነት ከእስራኤል ዘነፍስ ጋር አለው።(ኢሳ.፶፱፡፳፳፩) ከዚህ ውስጥ አንዱና ዋናው ከእመቤታችን ጋር ያደረገው ነው።

ይህ ኪዳን ልዩ ከሆነበት ነገሩ አንዱ የራሱ መታሰቢያ ዕለት ያለው መሆኑ ነው። ዕለቱም ጌታችን በጌቴሰማኒ ተገልጾ ኪዳኑን የገባበት ዕለት ነው፤ ይኸውም የካቲት ፲፮ ቀን ነው። እመቤታችን ከላይ እንደተገለጸው ወደ ጎልጎታ ወደ ጌታ መቃብር እየሄደች አብዝታ ትለምን ነበር። በዚህም ምክንያት መላእክት ወደ ሰማያት አሳርገው ገነትንና ሲዖልን አስጎብኝተዋታል። እርስዋም በሲዖል ያሉ ነፍሳትን አይታ በእጅጉ አዝናላቸዋለች፤ ከዚህም በኋላ ስለ ኃጥአን አብዝታ ስትለምን ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚች ዕለት ተገልጾ ልዩ የምሕረት ቃልኪዳን ስለገባላት ኪዳነ ምሕረት እየተባለች ትከበራለች።

እኛም ከዚህ እጅግ ሊያስተውሉት ከሚገባ ታላቅ መልእክት የምናገኘው ትልቅና ታላቅ ቁም ነገር እግዚአብሔር ከመረጣቸውና ካከበራቸው ጋር እንዴት ቃል ኪዳን እንደሚያደርግ ሲሆን አብዝተው ለጠየቁትና ለተማጸኑት የቅርብ አምላክ እንጂ የሩቅ አምላክ አለመሆኑን ማሳየቱና ጸሎታቸውንና ልመናቸውን ሰምቶ ምላሽ መስጠቱን ነው። ስለሆነም አምላካችን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ኪዳን ከገባላት የመስቀል ስጦታ እናታችን በረከትን ለማግኘት ዘወትር በተሰበረ ልብና በተዋረደ መንፈስ መቅረብ ያስፈልጋል። ነቢዩ ኤርምያስ “አቤቱ የሆነብንን አስብ” ብሎ እንደጮኸው ጩኸት እያንዳንዳችን የምሕረት ቃል ኪዳንን ወደተቀበለች ወደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንቅረብ። ልዑል እግዚአብሔር ንጉሥ ሰሎሞንን ስለ አባትህ ስለ ዳዊት ስል በትረ ንግሥናህን ከአንተ አልወስድም ብሎ ቃል እንደገባለት እኛም የዘላለም ቃል ኪዳን ስለገባላት ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ሲል እንዲምረን ፍጹም ትህትናን ገንዘብ አድርገን እግዚአብሔር ያከበራቸውን አክብረን መገኘት ይኖርብናል። በዚህ ታላቅ ፆምም በረከትን ለማግኘት ፆማችንን ከግብር ጋር አገናኝተነው ደካሞች የሚረዱበትን፣ ታማሚዎች የሚጠየቁበትን፣ እስረኞች የሚጎበኙበትን፣ የታረዙ የሚለብሱበትን፣ የተራቡ የሚጠግቡበትን፣ የተጠሙ የሚጠጡበትን መንገድ ለማመቻቸት የተዘጋጀን መሆን ይኖርብናል። ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው ብሎ ሐዋርያው ያዕቆብ እንደተናገረ እኛም ፆምንና ምፅዋትን አስማምተን ለበጎ ሥራ የተዘጋጀን እንድንሆን አምላካችን በቸርነቱ ይርዳን፤ እመቤታችን በተገባላት ቃል ኪዳን ትጠብቀን።

ወ ስ ብ ሐ ት ለ እ ግ ዚ አ ብ ሔ ር

___________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: