በተለይ የአውሬው መንግስት አሸባሪ ባለሥልጣናት ከውጭ አገራት ሲመለሱ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራውን አላቆምም ማለቱ ሁሉም ነገር ሉሲፈራውያኑ እንዳቀዱት እየተካሄደ መሆኑን ይነግረናል። የኢትዮጵያ አየር መንገድን ለዚህ የወረረሽኝ ዘመን አዘጋጅተውታል።
“ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን” ከሚለው መልዕክት የተወሰደ፦
የአዳም ዘር! እስካሁን የምታውቀው የቅጣት ማእበል ሁሉ ከብዶ ቢመጣም በታሪክም በማየትም በመስማትም ታውቀዋለህ የማታውቀው ፍጥረቱን ምን እንደሆነ የማትለየው የአውሬ አይነት ምድሪቱን ይከድናል፡፡ ከፊል ሰው፤ ከፊል አውሬ፤ አውሬ መሰል አጋንንት፤ የተለየዩ አውሬዎችን መልክ የቀላቀለ አውሬ ሌትም ቀንም ምልክት አልባውን ለመብላት ይዘምታል፡፡ የሰው ልጅ የያደራጀው ማንኛውም መሳሪያ እያጠፋቸውም ለቅጣቱ የላካቸው የሰራዊት ጌታ እስካላነሳቸው ድረስ! ይህ የሚሆነው ደግሞ የታዘዙትን አጠናቀው ሲጨርሱና የልዑል ህዝቦች ሁሉን ተረክበው ሲደላደሉ ብቻ ይሆናል፡፡
የልዑል ሕዝቦች በተወሰነላቸው በየመኖሪያቸው ላይ ምልክትና ጥበቃ ስለሚኖር መግባት አይቻልም፡፡ ፈቅደው ከሚያስጠልሉተ በስተቀር፡፡ የሰው ዘር ሰምቶትም አይቶትም ወይም ይሆናል ብሎ ገምቶት የማያውቀው ብዙ ሚሊዮኖችን የሚየጠፋ የበሽታ ዓይነት ይከሰታል፡፡ ያለከልካይም ይጠርጋል፡፡
የአገራችን ኢትዮጵያ ገዢዎችና ምንዝሮቻቸው በ2ኛው የእሳት ወንፊት ውስጥ /የነሱ ድጋፍ ሰጪ አዛዥ መካሪዎችም/ እጣቸው፡፡ የሃጢያተኞችም ወገናቸው እንደ ገለባ ክምር ነው፡፡ ፍጻሚያቸውም ለገሃነም ይሆናል፡፡ የሃጢያተኞች ስራቸው ክፉ ነው ፍጻሜዋም ገሃነም ነው፡፡ [መጽኃፈ ሲራክ ም፤ ፳፩፥፱፧፡፲]