Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • January 2020
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for January 11th, 2020

በኦሮሚያ ሲዖል ኢትዮጵያውያን ልጃገረዶች ጫካ ውስጥ በመደፈር ላይ ናቸው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 11, 2020

እላይ ከተቀመጡት ሁለት ሦስት “ባለ ሥልጣናት” መካከል አንዱ በእሳት እስካልተጠረገ ድረስ ይህ ነገር በዚህ አስከፊ መልክ መቀጠሉ አይቀርም። ፋሺስት ኢጣሊያ እንኳን ያላሳየችውን ጭካኔ ነው እነዚህ ጥቁር ፋሺስቶች በማሳየት ላይ ያሉት።

የደምቢዶሎው የኦሮሞዎች ጂሃድ የናይጄሪያ እስላማዊ መንግስት ከቦኮ ሃራም ሽብር ፈጣሪዎች ጋር በማበር የቺቦክ ልጃገረድ ክርስቲያን ተማሪዎችን ከሚጠልፈው ሁኔታ ጋር በጣም ይመሳሰላል። ደምቢዶሎ ገና ለሙከራ ነው! የኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ልክ እንደ ልፍስፍሶቹ የናይጄሪያ ክርስቲያኖች ለሆዳቸው የሚያድሩ ከሆነና ዝምታውን ከመረጡ ጠለፋው በመንግስት ድጋፍ ይቀጥላል።

ይህ ሁሉ ጉድ ሆን ተብሎ በዲያብሎስ የግብር ልጅ በአብዮት አህመድ የተቀነባበረ መሆኑን የሚጠራጠር ሰው አለ? አሁንም ልክ ከሃገር ሊወጣ ሲል ሕዝቡን የማሞቂያ እሳቱን ከዚህም ከዚያም ሰብሰቦ ባዘጋጀው ጭድ ላይ ይለኩሰዋል። ይህ ሁሉ ጽንፈኛ ተግባር ለመጭው “ምርጫ” ይረዳው ዘንድ የፈጠረው ሌላ እርኩስ ድራማ ነው።

በተለይ ክርስቲያንና አማርኛ ተናጋሪዎች በሆኑት ኢትዮጵያውያን ላይ በተለይ ኦሮሚያ በተባለው ሲዖል እየተካሄደ ያለው በሃገራችን ታይቶና ተሰምቶ የማይታወቀው የጭካኔ ተግባር ከበስተጀርባው የተለያዩ ዲያብሎሳዊ ዓላማዎችን የተሸከመ ነው፦

👉 1. አማራና ክርስቲያን የሚሏቸውን ኢትዮጵያውያንን ለማዋረድና ሞራላቸውን ለመሥበር ፥ የአማርኛ ቋንቋን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት(እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ይሁን በማለት ላይ ናቸው)

👉 2. አማራው ከኢትዮጵያዊነቱ እንዲላቀቅና የራሱ የሆነ ማንነት እንዲኖረው ፣ ክርስቲያኑን ከአክሱም ፂዮን እንዲርቅ ለማድረግ

👉 3. ኢትዮጵያውያን ከአረቦች የባሰ ጭካኔ ይፈጽማሉ በሚል ቅስቀሳ የአረብ ሞግዚቶችን የግፍና አረመኔነት ታሪክ ለማስረሳትና ለመሸፈን

👉 4. አብዮት አህመድ “እኔ ነኝ ያስፈታኋቸው፣ ከሰቆቃ ነፃ ያወጣኋቸው በማለት ተወዳጅነት እንዲያገኝ

ለመሆኑ በክልሉ ይህ ሁሉ ግፍና ሰቆቃ ሲከሰት “ደግ ነው” የተባለው የኦሮሞ ጎሳ የት ነው ያለው? አባ ገዳ የተባሉት የእባብ አገዳዎቹስ?

_________________________________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ኦሮሚያ ሲዖል | ግራኝ አህመድ ከሃገር ወጣ ፥ ቄሮ-አልሸባብ አለምማያ ዩኒቨርሲቲን በእሳት አጋየው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 11, 2020

ከዚህ በተጨማሪ፡ መምህር ዘመድኩን በቀለ እንዳሳወቀን፡ የወልዲያ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የፈለገ ምህረት ሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪ የነበረው ወጣት ሱራፌል ሰሎሞን ፀጋዬ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጅቷል።

በሌላ በኩል

ዛሬ በኮፈሌ ከተማ በጃዋር ምክንያት በአረመኔዎች እጅ በግፍ የተገደሉት የአቶ ታምራት ፀጋዬ፣ የልጃቸው የወጣት ሄኖክ ታምራትና በአቶ ታምራት ሱቅ የሚሠራው የሚያሳድጉት ልጃቸው የ80 ቀን መታሰቢያ ዕለት ነው። በወቅቱ የግፍ አገዳደሉን እንዲህ ነበር የዘገብኩት። ነፍስ ይማር።

አስገዳዩ ጃዋር ለፍርድ ሳይቀርብ ከውጭ ዐቢይ አህመድ፣ ለማ መገርሳ፣ ከውስጥ መራራ ጉዲናና በቀለ ገርባ ጭራሽ ኢትዮጵያዊ ዜግነት ሰጥተው በኦፌኮ የፖለቲካ ፓርቲ ታቅፎ ወንጀለኛውን ለምርጫ ውድድር አቅርበውታል። ፍትህ ለኮፈሌ ሰማዕታት። ፍትህ ለ86ቱ ኢትዮጵያውያን።

በአረጋዊው አቶ ታምራትና በልጆቻቸው ላይ የተፈጸመባቸው አረመኔያዊ ግድያ።

ዐዋጅ ዐውጆ ንፁሐንንን በአሰቃቂ ሁኔታ ያስፈገደለው ጃዋር አባ ሜንጫ ለይስሙላ እንኳ ለፍርድ እስኪ ቀርብ ድረስ ጩኸቴን እቀጥላለሁ።

ይሄ መንግሥታዊ የዘር ማጥራት ነው። ኦርቶዶክስ በኢትዮጵያ እንዳይኖር ተፈርዶበታል።

በምዕራብ አሩሲ የኮፈሌ ገብርኤል ሰበካ ጉባኤ አባል ናቸው። እዚያው ተወልደው ያደጉም ናቸው። አረጋዊ አቶ ተምራት ፀጋዬ። አቶ ታምራት ፀጋዬ ዐማራና ኦርቶዶክስ ከመሆናቸው በቀር ከአንድም ሰው ጋር ጠብ የሌላቸው ለፍቶ አዳሪ ነበሩ። የእነ ዐቢይ አህመድ መንግሥት ከኦሮሚያ ኦርቶዶክሶችንና ዐማሮችን፣ ጉራጌና ወላይታዎችን፣ ለማጽዳት ጃዋርንና ሠራዊቱን ይጠቀማል። በዚሁ መሠረት የዘር ማጽዳቱ እጣ አቶ ታምራት ቤተሰብ ላይ ወደቀ። ክፉ ቀን።

ገዳዮቹ አክራሪው የኦሮሞ ወሃቢያ መንጋ በመጀመሪያ አቶ ታምራትን ከቤታቸው አውጥተው መሃል አስፋልት ላይ አረጋዊውን እንደ እባብ ቀጥቅጠው ገደሉ። የእሳቸውን መሞት ካረጋገጡ በኋላ ቀጥሎ አባትየው አስከሬን አጠገብ በቅርቡ ከአዋሳ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ የተመረቀውን ልጃቸውን አቢቲ ታምራትን እየጎተቱ አምጥተው የአባትየውን አስከሬን ካሳዩ በኋላ እሱንም በተመሳሳይ መንገድ እዚያው ቀጥቅጠው ገደሉት። አባትና ልጅን ከገደሉ በኋላ ቀጥለው እንደ ልጃቸው ያሳደጉትን የሱቃቸውን ሠራተኛ በሁለቱ አስከሬን አጠገብ አርደው ገደሉ። መኪናዎቻቸውን፣ ንብረታቸውን በእሳት አቃጠሉ።

በመጨረሻም የሟቹን አረጋዊና የልጆቻቸው አስከሬን ላይ ገመድ በአስከሬኑ አንገት ላይ አስረው ከተማው ላይ እየጎተቱ ሲጨፍሩ ዋሉ። ዐማራና ነፍጠኛን ሰባብረው ጣሉ ማለት ነው። የኦሮሞው ፕሬዘዳንት የአቶ ሽመልስ አብዲሳን ትእዛዝ ፈጸሙ ማለት ነው። ይሄ ሁሉ ሲሆን የኦሮሚያ ፖሊስና መከላከያ ቆሞ ከማየት ውጪ ምንም አያደርግም ነበር። ይሄ ድርጊት እጅግ በተጠና መንገድ በተጠና መልኩ በከተማዋ የሚገኙ የክርስቲያኖቹ ንብረትና ቤት በሙሉ በእሳት እንዲወድም ተደረገ።

ይሄ ቀደም ብለው የተዘጋጁበት የዘር ማጥፋት ድርጊት ነው። የሟቾቹ ቁጥር ከዚህም በላይ ይገመታል። ኦርቶዶክስ ኦሮሚያን ይልቀቅ ነው ፉከራቸው። ለማ መገርሳ ጴንጤ ነው። በዚህ ላይ የመከላከያ ሠራዊቱ አዛዥ ነው። የሚሞተው ዐማራ፣ ወላይታ፣ ትግሬና ጉራጌ ስለሆነ ፈጽሞ አያገባውም። ዐቢይ አህመድ ጴንጤም እስላምም ነው። በዚህ ላይ የሀገሪቱ ጦር ኃይሎች አዛዥም ነው። የሚሞተው ኦርቶዶክሱ ስለሆነ አያገባውም።

እንዲህም ሆኖ ጃዋር በሕግ አይጠየቅም። ጭራሽ በእሱ ምክንያት የሞቱ ሰዎችን ዜና እነ ቢቢሲ ሲሠሩለት እንደ ጀብዱ ሼር ያደርጋል። መንግሥቱም ፀረ ኦርቶዶክስ ነው። ኦርቶዶክስን ለማጥፋት በድብቅ በምክርቤት ያጸደቁት ሁላ ነው የሚመስለው። እጅግ የተጠና ነገር ነው እየተካሄደ ያለው። ይሄ የሚቆም አይደለም። አንድም እስላም ድርጊቱን ሲያወግዝ አታይም። ከጥቂቶች በቀር በአብዛኛው ጮቤ ሲረግጥ ነው የምታየው።

ይሄን አሳቃቂ ድርጊት የፈጸሙት ኢትዮጵያውያን ናቸው ለማለት ይቸግረኛል። ጣልያንም እንዲህ አላደረገ። የመንግሥት እጅ አለበት። የተጠና ድርጊት ነው። አዳሜ እርምህን አውጣ። ይኸው ነው። የሚያሳዝነው የትግራይ ልጆችም እየሞቱ የትግሬ አክቲቪስቶች እየተፈጠረ ባለው ነገር ደስተኛ መሆናቸው ነው። እነ ናሁሰናይ፣ እነ አሉላ ሰሎሞን ቄሮን ግፋ በለው ማለታቸውም የሚያሳየው ይሄንኑ ነው። ነገን ደግሞ እናያለን።

የሞቱትን ነፍሳቸውን ይማርልን። የሰማዕታት በረከት ያድርግላቸው። አሜን።

+___________________________+

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: