Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • December 2019
    M T W T F S S
     1
    2345678
    9101112131415
    16171819202122
    23242526272829
    3031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for December 13th, 2019

የሰይጣን ምልክት 666 ነው ፥ የክርስቶስ የሆኑት ደግሞ ባንገታቸው ላይ ያለው ማሕተብ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 13, 2019

ትክክለኛዋ እምነት በተዓምር፣ በማርያም መቀነት / በቀስተ ደመና የታጀበች እምዬ ኦርቶዶክስ ፥ አድዋ ዘምታ ጊዮርጊስ ድል ያደረገላት፣ መከላከያ ሚንስትሯ ጊዮርጊስ የሆነ፣ ጳጳሳቷ ለአገር የሞቱ፣ አንድነት የምትሰብክ፣ የድኾች መጠጊያ፣ ፀበሏ የሚፈውስ፣ እምነቷ የሚፈውስ፣ ደመራዋ የሚያምር፣ ጥምቀቷ የሚያምር፣ አፅዋማቷ የሚያምሩ፣ ሥርዓቷ፣ መጻሕፍቷ፣ ገዳማቷ፣ ውቅር ዓብያተክርስቲያናቷ፣ የካህናቱ ዝማሬው፣ ቅኔው፣ ማሕሌቱ፣ ቅዳሴው፣ አለባበሳችን ፥ ሁሉ ነገራችን እንደ ኦርቶዶክሶች የሚያምር የለም።

ቃለ ሕይወት ያሰማልን፡ ወንድማችን!

+______________________________+

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ድንቅ ማታ በበዓታ | ከጠፈር ስትታይ ምድራችን በማርያም መቀነት ተከብባለች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 13, 2019

ይህ የተነሳው ከምድራችን በሦስት መቶ ሃምሳ ኪሎሜትር ከፍታ ላይ ከሚገኘውና ዓለማችንን በመዞር ላይ ካለው ከአለም አቀፉ የጠፈር ምርምር መእከል (ISS) ነው። ይህን ቪዲዮ በአጋጣሚ ማታ ላይ ማየቴ ነበር። አስገራሚ ነውእንዴት እንደገባሁ እንኳን አላውቅም

ጥሩ ዓይን ያለው/ያላት ወገናችን “ልቡን” ስለጠቆሙኝ፡ ከምስጋና ጋር፡ ተሻሽሎ የቀረበ

በፈርንጁ ዓለም ዘንድ ሙሉዋ ጨረቃና 13 የሚያርፍበት ዕለተ አርብ  ብዙ ፈተና እና መዘዝ ያለው ነው። ያለምክኒያት በዚህ ወቅት የኢትዮጵያን ጠላት ገዳይ አብዮትን አልሸለሙትም፣ ያለምክኒያት በዚሁ ወቅት የዓለም ባንክ ገንዘቡን ሊያጎርፍለት ቃል አልገባለትም፣ ያለምክኒያት በዚሁ ወቅት በዓለ ጥምቀትን አውሬው ዩኔስኮ አልመዘገበውም።

ባለፈው ቪዲዮ ላይ፡ አውሬው ዓይኑን በጥምቀት፣ ቍርባንና በተቀሩት ምስጢራተ ቤተክርስቲያን ላይ ማነጣጠሩን አውስቼ ነበር። ያውእመቤታችንም እየጠቆመችን እኮ ነው

በዓታ ለማርያም | መልአኩ ቅዱስ ፋኑኤል ኅብስትና ሰማያዊ ጽዋዕ ይዞ ከሰማይ ወረደ

እንኳን አደረሰን

ቅድስት ድንግል ማርያም በ፶፻፬፻፹፭ ዓመተ ዓለም ከሐና እና ከኢያቄም በፈቃደ እግዚአብሔር ተወልዳ እስከ ሦስት ዓመት ድረስ የኖረችው በወላጆቿ ቤት ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ ኢያቄምና ሐና የተሳሉትን ስእለታቸውን አስታውሰው ወስደው ለቤተ እግዚአብሔር ሰጧት፤ ካህኑ ዘካርያስም ስለምግቧ በመጨነቁ ሕዝቡን ሰብስቦ ሳለ መልአኩ ፋኑኤል ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ይዞ ከሰማይ ወረደ፤ ዘካርያስ ለእርሱ የመጣ ሀብት መስሎት ታጥቆ እጅ ነስቶ ቢቆም ወደ ላይ ራቀበት፡፡ ከስምዖን ጀምሮ በዚያ የተሰበሰቡት ሰዎችም በተራ ቢሞክሩ በተመሳሳይ ወደ ላይ ራቀባቸው፡፡ ምን አልባት ለእንግዶች የመጣ ሀብት እንደሆነ ብለው ሐና እና ኢያቄም እንዲቀርቡ አደረጓቸው፤ ለእነርሱም ራቀባቸው፤ ዘካርያስም ሐናን ‹‹እግዚአብሔር የሚያደርገውን የሚያውቅ የለምና ልጅቷን ትተሸ ወደዚህ ነይ›› ባላት ጊዜ ቅድስት ማርያም ድክ ድክ እያለች እናቷን ስትከተል መልአኩ ፋኑኤል ወደ እርሷ ቀርቦ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ጋርዶ መግቧት ዐረገ፤ ሊቀ ካህናቱም ሕዝቡም የምግቧ ነገር ከተያዘልን በቤት እግዚአብሔር ትኑር ብለው አስገብተዋታል፡፡

ድንግል ማርያምም ሰማያዊ ኅብስትና መጠጥ እየተመገበች ፲፪ ዓመት በቤተ መቅደስ ኖረች፡፡ ፲፭ ዓመት ሲሞላት ግን ለአቅመ ሔዋን በመድረሷ ከቤተ መቅደስ ትውጣልን በማለት አይሁድ በጠላትነት ተነሱባት፡፡ ካህኑ ዘካርያስም ይህን ሰምቶ እመቤታችንን ጠየቃት «ኦ ወለተ እስራኤል እፎ ትፈቅዲ ትንበሪ፤ ልጄ እንደምን ሆነሽ ልትኖሪ ትወጂያለሽአላት፡፡ እርሷም «ከእግዚአብሐር በታች ያለኸኝ አባት አንተ ነህ፤ በዚያውም ላይ እናት አባቴ አደራ ያሉህ አንተን ነው፤ ወደ እግዚአብሔር አመልክትልኝ፤» አለችው፡፡ ዘካርያስም ጸለየ፤ እግዚአብሔርም ከነገደ ይሁዳ ሚስቶቻቸው የሞቱባቸውን በትራቸውን ሰብስበህ በቀዳማይ ሰዓተ ሌሊት ከቤተ መቅደስ አግብተህ ስትጸልይ አድረህ በቀዳማይ ሰዓተ መዓልት አውጣው ብሎ ምልክትም እሳይህአለው ብሎ ነገረው፡፡ እርሱም እንዳለው አድርጎ በማግሥቱ በትሮቹን አውጥተው ቢያዩ የዮሴፍ በትር አብባና አፍርታ ተገኘች፡፡ ከበትሩ ጫፍ ላይ «ኦ ዮሴፍ ወልደ ዳዊት ዕቀባ ለማርያም ፍኅርትከ፤ ዮሴፍ ሆይ እጮኛህ ማርያምን ጠብቃት፤» የሚል ጽሑፍ አገኙ፤ርግብም መጥታ በራሱ ላይ አርፋለች፤ ስለሆነም ዮሴፍ እንዲጠብቃት ተወሰነ፡፡

የኢትዮጵያ ቀለማት / የማርያም መቀነት

የማርያም መቀነት ወርደሽ ንገሪያቸው

ወራሪና ባንዶች ካለ ባህሪያቸው

አይቶ ለመረዳት የታወሩ ናቸው

የኢትዮጵያ ሰንደቅ እኔ ነኝ በያቸው

በሠማዩ ላይ ሲታይ ቀለም

የሷ ነው እንጂ ሌላ አይደለም

+__________________________+

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ታሪካዊ ውሳኔ | ፀረ-ክርስቶስ ቱርክ በአርመን ወገኖቻችን ላይ ያካሄደችው ጭፍጨፋ የዘር ማጥፋት ነው ስትል አሜሪካ ወሰነች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 13, 2019

ኢትዮጵያን በቅርቡና በጽኑ የሚመለከት ታሪካዊ ውሳኔ… ከስንት ዓመታት ውጣ ውረድ በኋላይህ ለመጥፎ ዜናዋ ቱርክ መጥፎ ዜና ነው።

በአርመናውያንና በሌሎች ክርስቲያኖች ላይ በጎርጎሮሳዊው 1915 እና 1916 ዓ.ም የተፈፀመው “የዘር ማጥፋት መታሰቢያ” በሚል ያዘጋጁት የውሳኔ ሃሳብ ለአሜሪካ ምክር ቤት/ሰኔት ቀርቦ ውሳኔ እንዲሰጥበት ሲደረግ ይህ የአራተኛው ጊዜ ነበር። አሁን ውሳኔው ጸድቋል።

በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በክርስቶስ ተቃዋሚዋ ቱርክ በተካሄደው የጅምላ ጭፍጨፋ ሁለት ሚሊየን ክርስቲያን አርመኖች ስልታዊ በሆነ መንገድ ተፈጅተዋል። ይህ በተደራጀ ዘመቻ የተካሄደው ጭፍጨፋ የዘር ማጥፋት እንደሆነ አሜሪካ አሁን በይፋ ተቀብለዋለች። ንስሐ መግባት የማትሻዋ ቱርክ ይህን እስካሁን አልተቀበለችውም፤ ሌላ ዕልቂት መፈጸም ትሻለቻና፤ ለምሳሌ በሶርያ፣ በኢራቅ፣ በቱርክአዎ! በሃገራችን ኢትዮጵያ።

ከዛሬ አንድ መቶ ዓመት በፊት የተካሄደው የጅምላ ጭፍጨፋ “የዘር ማጥፋት፡ ነው ሲሉ ከ20 በላይ ሃገራት እውቅና ሰጥተዋል። የአርሜኒያ ታሪካዊ ወዳጅ ኢትዮጵያስ? አይይአሁን ያለው አውሬ መንግስትማ በክርስቲያን ኢትዮጵያውያን ላይ ለተመሳሳይ የግፍ ጭፍጨፋ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል፤ ያውም ልክ ቱርክ የተከተለችውን ዓይነት ስልታዊ የሆነ መንገድ በመከተል፤ አርሜኒያ 2.0። ያለምክኒያት አይደለም በዚህ ሳምንት በቂ ኦክስጅን በመሳብ ላይ የሚገኘው ገዳይ አብይ የቱርኩን ፕሬዚደንት ኤርዶጋንን እንደ ምሳሌው አድርጎ የወሰደው።

የኢትዮጵያና አርሜኒያ ታሪካዊ ወንድማማችነት ይለምልም፣ የኢትዮጵያና ሕዝቧ ጠላቶች ይቃጠሉ!

ቀደም ሲል የቀረበ

+ “የጂኒው ጃዋር እህት | ቱርኮች ሚሊዮን ክርስቲያን አርመናውያንን መጨፍጨፋቸውን አላወግዝም“+

+ የክርስቲያን ወገኖቻችን እልቂት መታሰቢያ | በቱርኮች ፈንታ አርመኖችና ግሪኮች ወደ አገራችን ይግቡ+

_________________________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: