Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • December 2019
    M T W T F S S
     1
    2345678
    9101112131415
    16171819202122
    23242526272829
    3031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for December 11th, 2019

ማሕተቡን አሥራ የተወለደችው ሕፃን እናት ሚስጥሩን ይፋ አደረገች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 11, 2019

ለኢትዮጵያውያን ክብራቸው፣ ኩራታቸውና ደስታቸው ማሕተባቸው እንጂ በደም የተቀባው የኖቤል ሜዳሊያና የአይ.ኤም.ኤፍ ዶላር አይደለም። ከእነ ማሕተቡ መወለድ የበለጠ ፀጋ አለን?

ነፍሳቸውን የሸጡት ሜዲያዎችና እንደ እስስት ተለዋዋጪዎቹ የማሕበራዊ ድህረገጽ ተዋንያዮች ስለ እነ ገዳይ አብይ የቱርክ ድራማ ሌት ተቀን ከመለፈፍ ይልቅ ለራሳቸው ሲሉ ስለ ልጃችን የማሕተብ ተዓምር በማውሳት የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ ያለማቋረጥ ማወደስ ቢችሉ ይመረጥ ነበር። ግን አለመታደል ሆኖ አብዛኛዎቹ ሜዲያዎች በአውሬው እጅ ውስጥ ገብተዋል። ስለዚህ፡ ምስክራችን ከላይ ብቻ ነው!!!

የዚህች መልአክ የመሰለች ሕፃን የማሕተብ ተዓምር ዜና የበሰረበት ወቅት ልክ ገዳይ አብይ የኖቤል ሰላም ሽልማቱን ከሚቀበልበት ወቅት ጋር መገናኘቱ ያለምክኒያት አይደለም፤ ሰውየው ከክርስቶስ ተቃዋሚዎቹ አንዱ እንደሆነ 100% እርግጠኛ ነኝ፤ ስለዚህ፡ በተፈጥሯዊው ማሕተብ በኩል እግዚአብሔር እጅግ በጣም ትልቅ የሆነ መልዕክት እያስተላልፍልን ነው። ጆሮ ያለው ይስማ ፣ ዓይን ያለው ይመልከት፣ ላልደረሰው ያድርስ፡ ለ አስራ ሁለት ሩብ ጉዳይ ሆኗል!

+ ማተብሽን ፍች በጥሽው ቢሉኝ+

እኔስ ከነ አንገቴ ውሰዱት አልኩኝ

ፊተኛ ነንና አንዳንሆን ኋላኛ

ህዝቤ ተነቃቃ ተነስ አትተኛ

ጅብ ከሄደ ውሻ እንዳይሆን ጩኽት

የተዋህዶ ልጆች አሁነ ነው ሰዓቱ

አይተን እንዳላየን ስንቱን አሳልፈናል

የእርሱ ፈቃድ ይሁን ብለን ዝም ብለናል

አሁን ግን ይበቃል ዝምታው ይሰበር

+ይገለጥ ይታወጅ የተዋህዶ ሚስጢር+

ክርስቲያን ማለት ኢትዮጵያ ማለት ነው!

+____________________________+

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የአባታችን የአባ ዘ-ወንጌል ስንብት | ይህን ምስኪን ህዝብ በጥላቻ የሚያይ ክርስቲያን አለ?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 11, 2019

 

፪ሺ፲፪ ዓ.ም – ዘመነ ዮሐንስ

[፩ኛ የዮሐንስ መልእክት ምዕራፍ ፬፥፳]

ማንም። እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል?

+_________________________________+

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

አውሬው መንግስት በቤተ ክርስቲያን ላይ እያካሄደ ያለው ጦርነት ተፋፍሞ ቀጥሏል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 11, 2019

ሰሞኑን አባ ዘወንጌልን በተመለከተ አንዳንድ ሕልሞች ይታዮኝ ነበር። ሕልሞቹን ለማስታወስ እየታገልኩ ነው። አባታችን የጠቆሙን ነገሮች ሁሉ አንድ በአንድ በመፈጸም ላይ ናቸው።

አባታችን አባ ዘወንጌል በአንድ ወቅት እንዲህ ብለውን ነበር፦

ኢትዮጵያን በዚህ ወቅት እያስተዳደሯት ያሉት ጠላቶቿ ናቸው!”

አዎ! አውሬው ጦርነቱን አስቀድሞ በማካሄድ ላይ ያለው የቤተ ክርስቲያን በር በሆኑት በሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ላይ ነው፦

. ምሥጢረ ጥምቀት
. ምሥጢረ ሜሮን
. ምሥጢረ ቁርባን
. ምሥጢረ ክህነት
. ምሥጢረ ተክሊል
. ምሥጢረ ንስሐ
. ምሥጢረ ቀንዲል

መጀመሪያ በቁርባን(ሕብስትና ወይን / ስጋውና ደሙ) ፣ ቀጥሎም በጥምቀት ላይ ነው የዘመቱት። በኢትዮጵያ የእንጀራና ዳቦ መጋገር ባሕል ባልተለመደ መልክ የአሕዛብ ዳቦ ቤቶች በብዛት እየተከፍቱና በየትምህርት ቤቱ ለሕፃናቱ ዳቦና ማርማላታ እያጎረሷቸው መሆናቸውን እንዲሁም ዓብያተ ክርስቲያናት ባሕረ ጥምቀትን በመነጠቅ ላይ መሆናቸውን በግልጽ እያየነው ነው።  የሰው ልጅ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ እንደማይችል ምቀኛው ጠላታችን ዲያብሎስ አጠንቅቆ ያውቃልና።

________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: