Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • December 2019
    M T W T F S S
     1
    2345678
    9101112131415
    16171819202122
    23242526272829
    3031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for December 7th, 2019

ለመራዡ ኡማ የ፲ሚሊየን ብር ሽልማት | ፫መቶ ታዳጊ የቅኔ ተማሪዎች ግን እየተራቡ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 7, 2019

ይሄ እንዴት ሊሆን ቻለ? የቄሳርን ለቄሣር?

ይህ በጣም ከሚያሳዝኑኝና ከሚያንገበግቡኝ ጉዳዮች መካከል አንዱ ነው። የአዲስ አበባን ሕፃናት በመመረዝ ላይ ላለው ለታከለ ኡማ መመረዣ ዳቦውን እና ማርመላታውን ይገዛበት ዘንድ ቤተክህነት አስር ሚሊየን ብር መለገሷን ሰምተናል፤ በቤተክርስቲያን ሥር የሚገኙ ሕፃናት ግን በመራብ ላይ ናቸው። እንዴት?

በርካታ ቀዳሚ የኢትዮጵያ ምሁራን መነሻቸው ከአብነት ትምህርት ቤት ነው። የአብነት ትምህርት ከዘመናዊ ትምህርት መስፋፋት ጋር ተያይዞ የወትሮ ሚናውን ማጣቱ ቢስተዋልም፤ አሁንም ጥቂት ለማይባሉ ወጣቶች ምርጫ መሆኑ አልቀረም።

የዕውቀት በርን የሚከፍትላቸውን የቅኔ ትምህርትን በንባብ ቤት፣ ዜማ ቤት፣ አቋቋም ቤት፣ ቅኔ ቤት፣ ቅዳሴ ቤት እና መፃሕፍት ቤት ለመከታተል ሦስት መቶ የቅኔ ተማሪዎች በድንቁ የአቡነ ሀብተ ማርያም ገዳም ይገኛሉ። ይሁንና የትምህርት ቤቶቹ ህልውና ከሚያስተዳድሯቸው ገዳማትና አብያተ ክርስትያናት መድከምና መጠንከር ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ለፈተና ሲዳረጉ ይስተዋላሉ። ተተኪ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች በቂ የመተዳደሪያ የገቢ ምንጭ ስለሌላቸውና ከቤተክህነትም እንኳን ምፅዋት ስለማያገኙ አሁን በመቸገር እና በመራብ ላይ ናቸው። አዎ! በአዲስ አበባ፣ ያውም በጣም ሰላማዊና ገነታማ ከሆኑት የከተማዋ ክፍሎች መካከል በአንዱ።

_____________________________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | 1 Comment »

 
%d bloggers like this: