Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 6, 2019
ዋው! ጽሙድ እንደበሬ ትጉህ እንደ ገበሬ እንዲሉ በጾም በጸሎት የተጠምዱት የአቡነ ሀብተማርያም ልጆች በበርሊን ጎዳናዎች… ያውም በፐርጋሞን ኃውልት ዙሪያ…ብዙ አንጮኽም፡ ግን ለሚመለከተው ክፍል ይህ ታላቅ የማስጠንቀቂያ ምልክት ነው።
ይህ ትልቅ እርምጃ ነው… ይህን ሰልፍ በበርሊን ማካሄዳቸው በጣም አስፈላጊ ነው… ምክኒያቱም በኢትዮጵያ ውስጥ በመካሄድ ላይ ያለው የዘርና የሃይማኖት ጭፍጨፋ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መልክ ከፕሬቴስታንት ጀርመን ጋር የተያያዘ ነው። በቁስጥንጥንያ ለኦርቶዶክስ ክርስትና መውደቅና ቱርክ የምትባል የክርስቶስ ተቃዋሚ ሃገር እንድትመሠረት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረከተችው የማርቲን ሉተር ጀርመን ናት፣ በሃገራችንም ኢትዮጵያን በማመስ ላይ ያለውን አመጸኛ የኦሮሞ እንቅስቃሴ የጀመሩት እንደ ዮኻን ክራፕፍ ያሉት ፕሮቲስታንት ጀርመናውያን ነበሩ።
እ.አ.አ ከ 1837 እስከ 1843 ዓ.ም ባለው ጊዜ ፕሮቴስታንቱ ጀርመናዊ ዮኻን ክራፕፍ ኦሮሚያ የተባለውን ግዛት ለመመሥረት የተነሳሳው ክርስትናን ለማስፋፋት ሳይሆን፡ እንደ አንድ ፕሮቴስታንት የኢትዮጵያ ቀጥተኛ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ለመዋጋት ነው። ለዚህም በወራሪነት ባሕርይ ከጀርመኖች ጋር ይስማማሉ በሚል ሃሳብ “ጋላ” ተብለው ሲጠሩ የነበሩትን ጎሳዎች ለማደራጀት የተነሳሳው። ተልዕኮው የክርስቶስ ተቃዋሚ ተልዕኮ ነው።
በርሊን የክርስቶስ ተቃዋሚው መቀመጫ ከሆኑት ዋና ከተሞች መካከል አንዷ ናት።
- + የፖለቲካ መናኸሪያ በርሊን፣
- + የኤኮኖሚ ለንድን እና ኒው ዮርክ፣
- + የመንፈሳዊ ቫቲካን እና መካ ናቸው።
የራዕይ ዮሐንስ ላይ ከተጠቀሱት ሰባት ዓብያተ ክርስቲያናት(ሁሉም ያሁኗ ቱርክ ውስጥ ነው የሚገኙት) መካከል አንዷ፤ ፐርጋሞን ናት፤ ይህችም የሰይጣን ዙፋን የሚገኝባት ቦታ እንደሆነች ቅዱስ ዮሐንስ ጠቁሞናል።
ታዲያ ከ ፐርጋሞን የተወሰደው የሰይጣን ኃውልት አሁን የሚገኘው በበርሊን ከተማ ነው። እነ ሂትለር፣ ቡሽ፣ ኦባማና ሂላሪ ክሊንተን ሁሉም ይህን ኃውልት ለመሳለም ወደ በርሊን ጎራ ብለው ነበር። ሚሊየን ሙስሊም ወራሪዎችን ወደ ጀርመን አገር ያስገባችው ወይዘሮ አንጌላ ሜርከልም ከዚሁ ኃውልት ፊት ለፊት ነው የምትኖረው፤ ለዚህም ይመስላል ሰላማዊ እና ንጹህ በሆነቸው ጀርመን ላለፉት ጥቂት አመታት ታይቶ የማይታወቅ ቅሌታማ ተግባር ተከላካይ በሌላቸው ጀርመናውያን ህፃናትና ሴቶች ላይ እየተፈጸመ ያለው።
በየዕለቱ አሰቃቂ ድርጊቶች ይከሰታሉ፣ ሁሉም ውረጅ፡ አንፈልግሽም ይላታል፡ ሆኖም ሴትየዋ ያው 15 ዓመት ሞላት ሥልጣን ላይ ከወጣች፤ ከሥልጣን ለመውረድ ፈቃደኛ አይደለችም፤ በኢትዮጵያ ላይ ተንኮል በመሥራት ላይ ያለቸውን ጀርመን ታጠፋ ዘንድ የተቀመጠች የዘመኑ ኤሊዛቤል ነችና።
እ.አ.አ. በ 1871 ዓ.ም የተዋሀደችው የጽንፈኛው ማርቲን ሉተሯ ጀርመን (ሁሉም ጀርመን አንድ አይደለም) የፐርጋሞንን የሰይጣን ኃውልት ወደ አገሯ በማስገባት ኢትዮጵያን መተናኮል ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በየጊዜው ስትቀጣ ቆይታለች። ጀርመን ቅኝ ግዛቶቿን አጣች፣ የአንደኛውንና ሁለተኛውን የዓለም ጦርነቶች በመቀስቀስ ዜጎቿ ብዙ ተሰቃዩ፣ ለመሰደድ ተገደዱ፤ የመሰማማት ህልም ነበራት ግን የራሷ ግዛቶች ተቆራረሰው በጎረቤት ሃገራት ተወሰዱ። አሁን ከምስራቁ የጀርመን ክፍል ጋር ከተዋህደችበት ጊዜ አንስቶ እንደገና የወራሪነትና የመስፋፋት መንፈሷ ተቀስቅሷል፤ በዚህም ምናልባት ለሦስተኛው የዓለም ጦርነት እንደገና መንስኤ ልትሆን ትችላለች። እኔ እንኳን በአቅሜ፡ “ከቀውስ መዳን የምትሹ ከሆነ ከኢትዮጵያ ላይ እጃችሁን አንሱ፣ ፐርጋሞንን ወደ ቱርክ መልሱ” የሚሉ ቃላትን የያዘ ደብዳቤ ለአንጌላ ሜርከል ሳይቀር ጽፌ ነበር።
________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: ሙስሊሞች, ሽብር, በርሊን, ተቃውሞ ሰልፍ, ተዋሕዶ, ኢትዮጵያ, እስላም, ኦሮሚያ, ኦሮሞ, ወራሪዎች, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እመነት, ዮኻን ክራፕፍ, ጀርመን, ጋላ, ጥቃት, ፀረ-ኢትዮጵያ ሤራ, ፀረ-ክርስቶስ, ፐርጋሞን, ፕሮቴስታንቶች | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 6, 2019
ያን ምስኪን በሬ እናስታውሰዋለን?
በዚያን ወቅት እነዚህን ጥያቄዎች ጠይቄ ነበር፦
ለመሆኑ
-
በሬው የማን ነው?
-
በሬውን ማን አመጣው?
-
በሬው እንዴት ጥብቅ ፍተሻ ሲደረግበት ወደ ነበረው ወደ መስቀል አደባባይ ሊገባ ቻለ?
-
በሬው ወደ ቅ/እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ለምን ተወሰደ?
-
በሬው ፌደራል ፖሊሶችን ለምን አሳሰባቸው? በጠዋትስ ለምን በእስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ተገኙ?
ከደመራ አንድ ሳምንት በፊት በመስቀል አደባባይ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን እና ግዮን(አባይ) ሆቴል አቅራቢያ የሚፈሰውን ወንዝ የዋቄዮ–አላህ ልጆች ከለሉት፣ ከዚያም የሩጫ ውድድር አካሄዱ፣ የደመራ ችቦ በበራ በሳምንቱ ሰይጣናዊውን የኢሬቻን በዓል በመስቀል አደባባይ በማክበር አጋንንታቸውን በአካባቢው አራገፉ።
አዎ! ይህ በመስቀል አደባባይ እና ቅዱስ እስጢፋኖስ አካባቢ ያለው ቦታ ከፍተኛ የመንፈሳዊ ውጊያ የሚካሄድበት ቦታ ነው። ነገሮችን ለማባባስ በቤተክርስቲያን እና ቤተክህነቷ ውስጥ ሰርገው የገቡ እንደ ኢሬቻ በላይ የመሳሰሉ የዲያብሎስ የግብር ልጆች ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ ናቸው።
„ “….ሰዎች ጥቅም ወዳድ ናቸውና በጥቅም ሂድባቸው…የሚፈልጉትን እያሳየህ ወደምትፈልገው ስፍራ ውሰድ እና ጣላቸው… ከዚያም በሬ ሆይ! ሳሩን አየህና ገደሉን ሳታይ… ብለህ ተርትባቸው” ብሎናል አይደል ግራኝ አብዮት አህመድ።
አዎ! እኔ ሰይጣን ብሆን ኖሮ የማደርገው ልክ አሁን በቤተክርስቲያን ላይ እይተሠራ ያለውን ነገር ነው። ቤተክርስቲያንን በሞቃታማ ጦርነት ብቻ ተዋግቶ ማሸነፍ እንደማይቻል አውቀውታል፣ ስለዚህ በአንድ በኩል ያዘጋጇቸውን አሕዛብንና መንፋፍቃን ለጥፋት ማሰማራት፣ በሌላ በኩል የኤሬቻ ባሪያዎችን ሰርገው እንዲገቡ ማድረግ፤ ከሁሉ በላይ ደግሞ የቤተክርስቲያንን አመራር በጥቅም መያዝ አስፈላጊ ነው። እንግዳችንን በቁንጣን ለማሰቃየት ብዙ ጉርሻ ማጉረስ እንዳለብን ሁሉ ቤተክርስቲያንን ለማፈንና ከተቀዳሚ የመንፈሳዊ መንገዷ ለማሰናከል ለዓብያተ ክርስቲያናቱ ሰፋፊ መሬት መስጠት፣ ከዚያም “ልማት” በተባለ ዘመቻ አብያተክርስቲያናቱ በንግድ ቤቶች፣ በምግብና መጠጥ ቤቶች፣ በጋራጆች ወዘተ እንዲከበቡ ማድረግ፣ “ከዚያም በሬ ሆይ! ሳሩን አየህና ገደሉን ሳታይ…” ተብሎ ይተረትባታል።
ባለፈው መስከረም ላይ አርብ ዕለት ወደምወዳት የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን አመራሁ፤ ፀሎት ካደረስኩ በኋላ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ምሳ ለመብላት ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ ወደ ሚገኙት ምግብ ቤቶች አመራሁ። አሳላፊዋ እንደመጣች፣ “የጾም ምግብ መብላት እፈልግ ነበር፤ ግን ምግቦቻችሁን በጭቃው ዘይት (የዘምባባ ዘይት) የምትሠሩ ከሆነ ይቅርብኝ” አልኳት፡ እርሷም “አይ ሁሉም በጭቃው ዘይት ነው የሚሠራው፣ ሁሉም ሰው ተስማምቶ ይበላዋል” አለችኝ። ብዙ ሰው ነበር፤ ወጣቶች። በጣም በማዘን፤ “ምነው! ምነው! እሺ አምቦ ውሃ አምጭልኝ” አልኳት፣ “እሱም የለም ሚሪንዳና ስፕራይት ወይም ሃይላን ውሃ ብቻ ነው ያለን” አለችኝ። ለስላሳ መጠጥ ስለማልጠጣ ውሃ አዝዤ ቁጭ አልኩ። በዚህ ወቅት ባለቤቱ መሰለኝ በእጁ የያዘውን ገንዘብ እየቆጠረ ወደ እኔ መጣና “ውሃው ተስማማህ?… ኑሮ ውድ ስለሆነብን እኮ ነው የጭቃውን ዘይት የምንጠቀመው ፥ ሁሉ ነገር ተወደደ” አለኝ። እኔም፡ “ቤተክርስቲያን ግቢ ይህን መርዛማ ዘይት ለምዕመናኑ በመቀለባችሁ መቅሰፍት እንደሚመጣባችሁ እውቀቱ፣ ጤናማ የሆነውን ዘይት ተጠቅማችሁ ምግቡን ትንሽ ማስወደደ አይሻለም?” አልኩትና ሂሳቡን ሰጠሁት፡ ከዚያም አንገቱን ደፍቶ ሄደ።
ብዙም አልቆየም አንድ አረጋዊ ካህን አባት ምግብ ቤቱ በር ላይ ቆመው ምግብ ሲያዙ አየኋቸው።
የታሸገ ነገር ተሸክመው መራመድ እንደጀመሩ ተከትያቸው ሄድኩና “እንድምን ዋሉ አባ? አንዴ ላናግርዎት?” አልኳቸው። “ከዚህ ምግብ ቤት ምን ዓይነት ምግብ ገዝተው ይሆን? በመርዛማው ጭቃ ዘይት የተሠራውን ምግብ ገዝተው ይሆን?” ስል ፥ እሳቸውም፡ “አይ ልጄ እንጀራ ነው የገዛሁት፣ ምን ዛሬ እንጀራው ውስጥስ ምን እንደሚያስገቡበት ይታወቃል፣ ሰጋቱራ ምናምን ይባላል” አሉኝ፤ በዚህ ጊዜ ሰዎች ከበቡን፡ እኔም፤ “እንዴ አባ ይህ ቦታ የቤተክርስቲያን ንብረት አይደለምን? ማን ምን እንደሚሸጥ ቁጥጥር መካሄድ የለበትምን?” እንዳልኩ በዚህ ጊዜ የከበበን ሰው ቁጥር ጨመረ። ዘበኛ ነገሩም እንደተለመደው “ምንድን ነው? ምንድን ነው?….. ይህን ጉዳይ ሌላ ቦታ ሄደህ አሳውቅ…ቅብርጥሴ” እያለ መጣ። እኔም “አያገባህም…መንፈስ ቅዱስ ነው የላከኝ፣ በርገር ሁሉ ትሸጣላችሁ…” በማለት ድምጼን “እንደ እብድ” በይበልጥ ከፍ ማድረግ ጀመርኩ። ካህኑም “ተወው ይናገር” በማለት ዘበኛውን ከእኔ አራቁት። አንድ ሌላ ቄስ ወደ እኔ መጥቶ “ኑሮ ውድ ነው፣ በተገኘው ነገር ምግብ ቢሠራ ምን ክፋት አለው? በርገርስ ምግብ አይደለምን?” እንዳሉኝ በይበልጥ ቱግ ብዬ በመጮኽ “ምን ዓይነት መርገም ነው? ቤተክርስቲያን ግቢ እንዴት መርዝ ይሸጣል? በርገር የአሳማ፣ የአህያ ወይም የውሻ ስጋ ሊደባለቅበት እንደሚችል አታውቁምን? ለመሆኑ በጣም ብዙ ምዕመናን ያለው ይህ ድንቅ ቤተክርስቲያን ለምንስ የንግድ ቦታዎች አስፈለጉት? ቤተክርስቲያናችን ሁለት ሺህ ዓመታቱን ሁሉ የዘለቀችው በገንዘብ ነውን? ምግብ ቤቶች መከፈት ካለባቸው እንኳን ባለቤቶቹ ጥንቃቄ የሚያደርጉ የተዋሕዶ ክርስቲያኖች ብቻ መሆን አለባቸው፣ አሊያ ሁሉም መዘጋት ይኖርበታል። ከአህዛብ ሃገር ከማሌዢያ በመጣ በመርዘኛ ዘይት ምግብ ተሠርቶ እየተሸጠ በምን ዓይነት ተዓምር ነው ምዕመናን ከቤተክርስቲያን ተባርከው ሊወጡ የሚችሉት? ቅዳሴው፣ ፀሎቱና ጸበሉ ሁሉ እኮ ኃይላቸውን እየተነጠቁ ነው፣ ቅዱስ እስጢፋኖስን ለሁለተኛ ጊዜ በድንጋይ እይወገራችሁት ነው!” በማለት ስናገር ሁሉም በሃፍረት አንገታቸውን ደፍተው ይታዩ ነበር። (የጉልበቶቻቸውንና ክንዶቻቸውን መገጣጠሚያዎች ስለታመሙ አባቶች መስቀል እንዲያሳርፉባቸው የሚጠይቁ ብዙ ወጣቶች አይቻለሁ፤ ጭቃው ዘይት)።
በአንድ በኩል ጉዳዩ በጣም የሚያሳዝንና መፍትሄም ቶሎ የሚሻ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ግን በተለይ የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ምዕመናን እሮሮ አሁን በዚህ መልክ መሰማት መጀመሩ ለበጎ ነገር ስለሆነ በከፊል አስደስቶኛል። አካባቢው ከፍተኛ መንፈሳዊ ውጊያ የሚካሄድበት ነውና፣ ዲያብሎስ ከሁሉም አቅጣጫ ነው እየተዋጋን ያለው።
የሚቀጥለው ቪዲዮ ስለ አቡነ ሀብተማርያም ገዳም የቅኔ ተማሪዎች እሮሮ ይሆናል
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም እግዚአብሔር ለቅድስና ሥራ ስለመረጣቸው በእናተቸው ጀርባ ታዝለው ወደ ቤተክርስቲያን ሄደው በሕጻን አንደበታቸው ከቀዳሹ ካህን ጋር “እግዚኦ ማሐረነ ክርስቶስ” በማለት ይጸልዩ ነበር፡፡ ባደጉም ጊዜ ይህን ጸሎት ደጋግመው ይጸልዩ ነበር፡
ሰላም ለዝክረ ስምክ፡– በዃለኛው ዘመን የዚህን ዓለም ረሃብና ጥም የሚያስረሳና ከወይን ዘለላ ይልቅ ለሚወደድ ስም አጠራርህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ህጻን የሆነ የማርያም ልጅ ወዳጅ ጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ሆይ በቦታው ታርፍለት ዘንድ ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት አጥብቆ እንደ ለመነ እኛንም ልጆችህን ከሀዘን ሁሉ ታድነንና በቤታችንም ታርፍ ዘንድ እንለምነሃለን፡፡ እግዚኦ ማሐረነ ክርስቶስ!
የአባታችን የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ረድኤት፣ በረከት፣ ምልጃና ቃል ኪዳናቸው አይለየን፡
__________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: መስቀል, መስከረም ፳፻፲፪, ምግብ ቤት, ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን, በሬ, ንግድ ቦታ, አዲስ አበባ, ኢሬቻ, ኢትዮጵያ, ኢየሱስ ክርስቶስ, ዘምባባ ዘይት, የምዕመናን እሮሮ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት, ደመራ, ጭቃ ዘይት, ፖሊሶች, Demera, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith, Meskal, Ox | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 6, 2019
አብዮት አህመድ የኖቤል የሰላም ሽልማትን ለመቀበል በሚቀጥለው ሳምንት ኦስሎ ከተማ በሚገኝበት ወቅት የዜና ማሰራጫዎችን ለማነጋገር ፈቃደኛ አይደለም። ይህም ነፃ እና ገለልተኛ ፕሬስ በጣም አስፈላጊ ነው ከሚለው የሽልማት ኮሚቴው መርሆ ጋር ስለሚጻረር ትችት እየተሰነዘረበት ነው።
የኖቤል የሰላም ሽልማት በተለምዶ ዲሴምበር 10 ቀን ከመካሄዱ አንድ ቀን በፊት የኖቤል የሰላም ሽልማት የዜና ስብሰባ ያካሂዳል ፡፡
አብይ አህመድ ከኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤርና ሶልበርግ ጋር ከተገናኘ በኋላ ከጋዜጠኞች ለሚቀርብለት ጥያቄዎች ለመጠየቅ ፈቃደኛ እንዳልሆነ ከመግለጹ ሌላ በየዓመቱ በኖብል የሰላም ማእከል በሙዚየሙ ውስጥ በሚከበረው የልደት በዓል ላይና ከህፃናት ጋር በሚደረገው ዝግጅት ላይም አይሳተፍም፡፡
አብይ አህመድ የኖርዌይ ፖለቲከኞች እና ምሁራን ከሚሳተፉበት ሚስጥራዊ ሽልማት ኮሚቴው በኩል ያልተለመደ ትችትና ወቀሳ አግኝቷል ፡፡ “ሀሳብን የመግለጽ ነፃነት እና ነጻ ፕሬስ የሰላም ወሳኝ አካላት ናቸው ብለን እናምናለን። አብይ አህመድ የዜና ጉባኤ አለመያዙ ችግር እንዳለበትና በኦስሎ በሚቆይበት ጊዜ ከሜዲያ ጋር እንዲነጋገር በጣም ፈልገን ነበር።” ብለዋል ፡፡
ከዚህ በፊት ከሚዴያ ጋር ለመነጋገር ተመሳሳይ ፍራቻን አሳይቶ የነበረው ምንም ሳይሰራ በ2009 ዓ.ም ይህን ሽልማት የተረከበው የአብይ ሞግዚት ባራክ ሁሴን ኦባማ ነበር።፡ ተመሳሳይ ላባ ያላቸው ወፎች አንድ ላይ ይበራሉ!
አሁንስ ምን ዓይነት ድራማ አዘጋጅተውልን ይሆን? ምንስ አስደንግጧቸው ይሆን? የኖበል ኮሜቴው ለገዳይ አብይ ሽልማቱን በመስጠቱ ተጸጽቶ ይሆን? ወይንስ ዲዜምበር 10 አብዮትን ሊጠብቀው የሚችለው ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ አስደነገጠው። ብዙ የሚደብቀው ጉዳይ ስላለ በነፃ ከጋዜጠኞች ጋር ነፃ ቃለ መጠይቅ ማድረግ አይችልም፤ በደንብ የተዘጋጀበትና እራሱ ካዘጋጃቸው ጋዜጠኞች ውጭ በገለልተኛ ወይም ተቃዋሚ በግልጽ ሲጠየቅ ታይቶ አይታውቅም። ለምን? ብላችሁ እራሳችሁ ጠይቁ! ለማንኛውም ኖርዌይ ለዚህ ገዳይ ይህን ሽልማት በመስጠቷ ጽንፈኛ ኦሮሞዎች እየፈጸሙት ላሉት የዘር ማጥፋት ድርጊት ከተጠያቄዎቹ መካከል አንዷ ናት።
________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Infos | Tagged: ሜዲያ, ሰላም, ቃለ መጠይቅ, ተሳትፎ, ኖርዌይ, አብይ አህመድ, አብዮት አህመድ, ኢትዮጵያ, ኦስሎ, የሰላም ሽልማት, ግራኝ አህመድ, ፍራቻ, Genocide | Leave a Comment »