Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • September 2019
    M T W T F S S
     1
    2345678
    9101112131415
    16171819202122
    23242526272829
    30  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

አባታችን ንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ ኢየሱስ ከሠላሣ ዓመታት በፊት ያስተላለፉልን ዛሬም ወቅታዊ የሆነ ድንቅ መልዕክት

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 22, 2019

መላው ዘመናቸውን ኢትዮጲያዊነታቸውን ተንከባክበውና ጠብቀው፣ ያለ ሱፍና ከረባት አለባበሳቸውን አሳምረው፣ የእንግሊዝኛው ቋንቋ በአማርኛው መሃል እየገባ ሳያሰናክላቸው ጥርት ባለ ኢትዮጵያኛ ለኢትዮጵያ ቆመውና ኢትዮጵያውያንን በእውቀት መግበው ወደ ሚቀጥለው ሕይወት አልፈዋል።

አዎ! ያለተዘመረላቸው ድንቁ አባታችን ለምሳሌ የሚከተለውን ተናግረው ነበር፦

ኢትዮጵያ እንኳን ዜጎቿን “ኢትዮጵያዉያን ነን” የሚሉትን ቀርቶ የዓለምን ሕዝብ ትመራለች ብንላችሁ “ኡ!!“ልትል ስለምትችሉ የንስሐ እድሜ ካገኛችሁ ተፈጽሞ እንደምታዩ እንነግራችኋለን። በዓመጻችሁ ጸንታችሁ ከተጠረጋችሁ ደግሞ ቅኖችና የዋሃን ትዉልዶች እንደሚያዩት በእግዚአብሔር ስም እናረጋግጥላችኋለን። እንደ እናንት የእግዚአብሔርን ኃይል የምንጠራጠር አይምሰላችሁ። እግዚአብሔር፤ ንጉሡ ሰናክሬም የተመካባቸዉንና የተማመነባቸውን 185000 (አንድመቶ ሰማኒያ አምስት ሺህ” ሠራዊት በዐይን ቅጽበት ዉስጥ እንዳልነበሩ አድርጎ እንዳረገፋቸዉ ከመጽሐፍ ቅዱስ አላነበባችሁምን? ሲወራስ አላዳመጣችሁምን?

እግዚአብሔር አሁን በኛ ዘመን ኃጢአት እጅግ በነገሠበት ወቅት ደግሞ 185000 አይደለም 1850000000 (አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ ሃምሳ ሚሊዮን)ሠራዊት በዐይን ቅጽበት ዉስጥ ማርገፍ የሚያቅተው ይመስላችኋልን? እናንተ ሆናችሁ በዓለም ዉስጥ ያለው ትዉልድ ማንም ይህን ማን በዓመፃዉ ከጸናና እጁን ለእግዚአብሔር አልሰጥ ካለ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ አመጸኛ ትዉልድ ረግፎ እንደ ኖኅና ቤተሰቡ ቅንነት፥ የዋህነት፥ እዉነተኛነት የተላበሱትን ሰዎች ብቻ የማያስቀር ይመስላችኋልን?

ስለዚህ “ሠራዊቱ፣ ድኅንነቴ፣ ጠባቂዬ፣ ዘሬ፣ ጎጤ ኃያላን መንግሥታት፤ የአውሮፓ ህብረት፣ የአፍሪካ ህብረትወዘተ” የሚባሉት እንኳን እናንተን ራሳቸውንም ማዳን እንደማይችሉ በዚሁ ልንገልጽላችሁ እንወዳለን። ከእግዚአብሔር ቁጣ ሊድኑ የሚችሉት በእዉነተኛ ንስሐ ለእግዚአብሔር እጃቸዉን ሲሰጡና በኢትዮጵያ በቅርቡ እግዚአብሔር ለሚዘረጋው መንግሥቱ ለሥጋዊዉም ለመንፈሳዊዉም ሥርዓት ተገዥ ሲሆኑ ብቻ ነዉ። በተቀረ ግን የዓመጻ፣ የክህደት፣ የርኩሰት ጽዋቸዉን እያንዳንዱ መንገሥት፣ ቡድን ፣ ድርጅት፣ ግለሰብ እየጠጣ ነጻነቱ ተገድቦ ወደሚኖርባትና እንደ ዓመጻው ደረጃ ፍዳዉን ወደሚቀበልበት ቦታ መሄድ ነዉ የሚቀረዉ። ይህን ሁሉ የተናገርነዉ መቺስ እጃችሁን ለእግዚአብሔር ትሰጣላችሁ ብለን በማሰብ ሳይሆን የእናንተ ልበ ደንዳናነት ቢታወቅም ባለማወቅ በቅንነትና በየዋህነት አብሮዋችሁ የተሰለፉ ሰዎች ካሉ ከዛሬ ጀምሮ ከእናንተ ጋር አንድነትና ኅብረት እንዲፈጥሩ፣ እንዲሁም በእዉነተኛ ንስሐ እንዲመለሱ ለማሳሰበ ነኡ።” በማለት ተገልጿል።

ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር የተመሰረተችና በቅዱሳን ቃል ኪዳን የተጠበቀች፤ ከሁል በላይ ደግሞ የእመቤታችን አስራት አገር ስለሆነች እንኳን በአገር ዉስጥ ለጥፋቷ የተሰለፉ አይደለም፤ እርሷን ለማጥፋት የተሰለፉ የዉጭ መንግሥታት በሙሉ በእግዚአብሔር ቁጣ ይጠፋሉ፤ ከምድር ይጠረጋሉ። እርሷ ግን በእግዚአብሔር መንግሥትነቷ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ትቆያለች። ታዲያ አሁን ቢሆን “የአዲሲቷ ኢትዮጵያ መሪዎች ነን” እያሉ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊነት ላይ የሚያላግጡ ሆኑ እርሷን ለማጥፋት የተሰለፉ የተለያዩ ቡድኖችና ድርጅቶች እንዲሁም መንግሥታትና ግለሰቦች ዛሬ ነገ ሳይሉ በእዉነተኛ ንስሐ ለእግዚአብሔር እጃቸዉን ቢሰጡና ወደማንነታቸዉ ወይንም ወደ ኢትዮጵያዊነታቸዉ ቢመለሱ የሚበጃቸዉ እንደሆነ በዚሁ አጋጣሚ መልእክቱን አቀርባለሁ።”

ንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ ኢየሱስ

______________________

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: