ቪዲዮው መጀመሪያ ክፍል ላይ የሚታየው ባለፈው ሳምንት ላይ የተቃጠለው የአቡነ ተክለ ሐይማኖት ቤተክርስቲያን ነውን? የተሻለ መረጃ ያላችሁ፣ ጉዳዩን የምታውቁና ማረጋገጥ የምትችሉ ወንድሞች እና እህቶች ባካችሁ ጠቁሙን፤ መረጃው በጣም አስፈላጊ ነው።
ቪዲዮው የተሠራው “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ደኖችን ማዳን” „Saving Ethiopian Orthodox Church Forests“ የሚለውን ዘመቻ ለዓመታት በምታካሂደው አሜሪካዊት፡ በ ዶ/ር ማርጋሬት ሎውማን ነው (ከምስጋና ጋር)።
ነገሮች ሁሉ ተገጣጠሙብኝ፦ እንደ ዋልድባ ገዳማት በመሳሰሉት ጫካማ አካባቢ ፋብሪካዎች እንዲሠሩ ካዘዟቸው በኋላ የኢትዮጵያ ቤተከርስቲያን ደኖችን መጠበቅ አለብን የሚሉ ዘመቻዎችን ብዙ የውጭ ሰዎች በማካሄድ ላይ ናቸው። የዶ/ር ማርጋሬትን ሥራ ዝቅ ማድረጌ አይደለም፤ አስተዋፅኦ ታደርግ ይሆናል፣ ለበጎ ሊሆን ይችላል። ሆኖም ለሁለት ሺህ ዓመታት ያህል ደኖቿን ጠብቃ ያቆየችልን ቤተክርስቲያን እስከሆነች ድረስ ለምን ሙሉውን ኃላፊነት ለቤተክርስቲያኗ አይተውላትም?
በተለይ የ ግራኝ አብዮት አህመድ የ”ችግኝ ተከላ” ዘመቻ ተንኮል ያለበት መሆኑን ብዙዎች አሁን እየተረዱት ነው። ደን የምትንከባከበው ቤተክርስቲያን ሆና የምትቃጠለውም ቤተክርስቲያን ናት። እንደ አብዮት አህመድ ከሆነ፦
“ለዋቄዮ–አላህ መስዋዕት ከማድረጌ በፊት ለዛፉ ችግኝ መትከል አለበኝ፤ ለዚህም በብዙ ሚሊየን የሚቆጠሩትን ኢትዮጵያውያን ማንቀሳቀስ እችላለሁ፤ ንጉስ ነኝ፣ ጁፒተር ነኝ ፥ ልጆቿ የተገደሉባትና የዕምነት ቦታዎቿ የተቃጠሉባት ቤተክርስቲያን ግን በጎቿን ማዘዝ እንኳን አትችልም፤ ዛፎቹና ደኖቹ የኛ/ኬኛ ናቸው”።
አዎ! ለዋቄዮ-አላህ ብዙ መስዋዕት በማቅረብ ላይ ስላሉ አምላካቸው ጊዜያዊ ድፍረቱን ሰጥቷቸዋል፤ ለዚህም ነው በቤተክርስቲያን ላይ ዕብደት የተሞላባቸውን ድርጊቶች በመፈጸም ላይ ያሉት።
„ኦሮሞ ነን” የምትሉ የተዋሕዶ ልጆች ከክርስቶስ ተቃዋሚው ፍዬል ጋር መደመር ካልፈለጋችሁ፡ ፈጥናችሁ “ኦሮሞነታችሁን” ካዱ!