Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • July 2019
    M T W T F S S
    1234567
    891011121314
    15161718192021
    22232425262728
    293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for July 7th, 2019

ታላቅ ጉዳይ | በኢትዮጵያ ሕፃናት ላይ ያነጣጠረው ሉላዊ የሉሲፈራውያን ሕፃናት-ዸፋሪ አውታር መሪ ታሠረ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 7, 2019

መታሠርና ለፍርድ መቅርብ ያለባቸው እንደ እነዚህ ዓይነት ያሉ ሰዎች ናቸው

ቢልየነሩ ባለኃብት ጄፍሪ ኤፕሽታይን የዓለም አቀፉ ዲያብሎሳዊ የሕፃናት ደፋሪዎች አውታር መሪ እንደሆነ ባለፉት ዓመታት ሲወሳ ቆይቷል። ይህ ጽንፈኛ አውታር የቀድሞዎቹን የአሜሪካ ፕሬዚደንቶች ክሊንተንን፣ ኦባማን፣ ቡሽን፣ የብሪታኒያ ልዑሎችን እና ሌሎችንም ብዙ ታዋቂ ባለጌ ሰዎችን ያካተተ ዲያብሎሳዊ አውታር ስለሆነ፡ በዚህ መልክ አሁን ከተጋለጠ ለዓለማችን ትልቅ ድል ነው የሚሆነው።

ጄፍሪ ኤፕሽታይን ባለፈው ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ተልካ የነበረችውን ሶፊያየተባለች ሮቦትን ለመሥራትና በመላው ዓለም ለመላክ የገንዘብ ድጎማ ሲያደርግ የነበረ ቆሻሻ ሰው ነው። የዚህች ሮቦት ተልዕኮ ግብረሰዶማዊነትን እና ሕፃናትዸፋሪነትን በአገራችን ከማስፋፋት ጋር የተያያዘ ነው።

የሳውዲ ዜግነት የተሰጣት ሮቦት ሶፊያ፡ በዘመነ ግራኝ አህመድ በመካ መዲና በኩል አድርጋ ወደ ኢትዮጵያ ማምራቱ ያለምክኒያት አይደለም። እዚህ ይመልከቱ፦ What Is the Connection Between Pedophilia and A.I. (Artificial Intelligence)?

የሚከተለው ከዓመት በፊት ልክ በዚህ ዕለት ያቀረብኩት ጽሑፍ ነው

ግብዞች በእግዚአብሔር አፈጣጠር እና ፍጥረታት ላይ እያመጹ ነው፤ እራሳቸውን አምላክ ለማድረግ ይሻሉ። በትንቢተ ዳንኤል እና በ ዮሐንስ ራዕይ መጻሕፍት ላይ ሁሉም ነገር ተብራርቶ ይነበባል። አሁን ብዙ እየትወራለት ያለው የሰው ሠራሽ አዕምሯዊ ጥናት ዘመቻ የፀረክርስቶሱና የአውሬው መንፈስ የቀሰቀሰው ዘመቻ እንደሆነ ምንም አያጠራጥርም።

ተራቅቀናል የሚሉት አመጸኞቹ ሰዎች አሁን ሮቦቶችን እየሠሩ ቀስ በቀስ እንደ እግዚአብሔር እንዲመለኩ ማድረግ ይጀምራሉ።

ባለፈው ዓመት፡ “ሶፍያ” የተሰኘች “ሴት” ሮቦት በሳውዲ አረቢያ ተወዳጅነት ማትረፏና ከሁሉ አገሮች ቀድማ የሳውዲ አረቢያን ዜግነት ለመጀመሪያ ጊዜ ማግኘቷ፡ የፀረክርስቶሱ ኃይል በምዕራባውያኑ ኤዶማውያን ቴክኖሎጂና በእስማኤላውያኑ ዶላር ድጋፍ በመላው ዓለም እንደሚሠራጭ ይጠቁመናል። ሆንግ ኮንግ የተሠራችው “ሶፊያ” በሳውዲ አረቢያ በ666ቱ መንፈስ ከተጠመቀች በኋላ፡ ወደ ተመረጡ አገሮች ተጓዘች።

ሶፊያ” ከመሠራቷ ከአምስት ዓመታት በፊት ቅሌታሙ ባለ ኃብት አሜሪካዊ፡ ሕፃናት ደፋሪው፡ ጀፍሪ ኤፕሽታይንየሚደግፈው የሰው ሠራሽ አዕምሯዊ ጥናቶችን ማካሄጃ ተቋም በኢትዮጵያ ተምሠረተ፤

(በአዲስ አበባ ሉሲአጠገብ)፤ እዚያም አበበየተባለ እግር ኳስ ተጫዋች ሮቦት ተሠራ፤ ከዚያ በኋላ ሮቦት “ሶፊያ” ተሠራች፤ ከሳምንት በፊት ሮቦት “ሶፊያ”ን ወደ ኢትዮጵያ እንድትመጣ የጋበዛት ይህ ተቋም ነው። (አዳም እና ሔዋን መሆናቸው ነው)

የዚህ ተቋም ኃላፊ የሆነው ሊቅ ጌትነት አሰፋ የሚከተለውን ከንቱ ዓረፍተ ነገር ተናግሯል፦

በመጪዎቹ አሥር ወይም ሃያ አመታት ውስጥ የሰው ልጅ የሚባል አይኖርም፤ በማሽን ይተካል”

I don’t think Homo sapiens-type people will exist in 10 or 20 years’ time.”

ይህን ዲያብሎሳዊ ህልምና ዕቅድ በሥራ ላይ ለማዋል፡ ሰኔ ፪ሺ፲ ዓ.ም፡ “ሶፊያ ወደ ኢትዮጵያ እንድትጓዝ ታዘዘች፣ የባህል ልብሳችንን አለበሷት፣ ቋንቋችንን ተናገረች፣ ሰንደቅ ዓላማችን ላይ ካረፈው የሉሲፈር አምስት መዓዘናዊ ኮከበ እና ከዶ/ር አብይ ጋር አብራ እንድትታይ ተደረገች። ጎልቶ የሚታየው ኮከቡ ነው!

[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፫፥፲፭]

የአውሬው ምስል ሊናገር እንኳ ለአውሬውም ምስል የማይሰግዱለትን ሁሉ ሊያስገድላቸው፥ ለአውሬው ምስል ትንፋሽ እንዲሰጠው ተሰጠው።

__________________

Posted in Conspiracies, Curiosity, Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የኢሳያስ እና ዶ/ር አህመድ ሤራ | የታላቁ ደብረ ቢዘን ገዳም አምስት አባቶች ታሠሩ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 7, 2019

[የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፲፰፥፲፰]

እውነት እላችኋለሁ፥ በምድር የምታሥሩት ሁሉ በሰማይ የታሠረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል።

በኤርትራ ክፍለ ሃገር(አዎ! ካሁን በኋላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ግዛቶች ክፍለ ሃገራት ነው የምላቸው) ከተመሠረተ ስድስት መቶ ሃምሳ ዓመታትን ያስቆጠረው ታላቁ የደብረ ቢዘን ገዳም ጣሊያን ኤርትራን እያስተዳደራት እያለም ቢሆን በኢትዮጵያ አስተዳደርና ንብረት ሥር ነበር (በውጫሌ ስምምነት ውስጥ ተጠቅሷል)

ላለፉት አሥራ ሦስት ዓመታት በፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ወኅኒ የሚንገላቱት(ውሸት ነው አልተፈቱም)የቀድሞው የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ የዘጠና ሁለት ዓመቱ አዛውንት አቡነ አንጦኒዮስ እንዲፈቱላቸውና የኢሳያስ መንግስት በቤተክርስቲያን ጉዳይ የሚያደርገውን ጣልቃገብነት በመቃወም ድምጻቸውን ሲያሰሙ የነበሩት የታሪካዊው ደብረ ቢዘን ገዳም መነኮሳት(ባለፈው ዓመት የተቀረጸው ቪዲዮው ላይ ይታያሉ)የሚከተሉት ናቸው፦

፩ኛ. አባ ክብረአብ ተክሌ

፪ኛ. አባ ማርቆስ ገብረ ኪዳን

፫ኛ. አባ ገብረ ትንሣኤ ተወልደ መድሕን

፬ኛ. አባ ኪዳነ ማርያም ተከስተ

፭ኛ. አባ ገብረ ትንሣኤ ዘሚካኤል

ነገሮችን ሰፋ አድርገን ከተመለከትን ይህ በዶ/ር አብዮት አህመድ እና በፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ የተቀነባበረው ፀረክርስትና ዘመቻ መሆኑን እንረዳለን።

ለአንድ የሰሜን ኢትዮጵያውያን ትውልድ መጥፋት ተጠያቂ የሆነውን ኢሳያስ አፈወርቂን ወድቆበት ከነበረው የማዕቀብና መገለል ጉድጓድ ያወጡት ዶ/ር አብዮት አህመድ እና ሉሲፈራውያኑ ደጋፊዎቹ ናቸው። ኢሳያስ ኦነጎችን እና ብርሃኑ ነጋዎችን እየቀለበ ሲያሳድግለት ስለነበር እንዲሁም ወጣት የተዋሕዶ ልጆች እየተሰደዱ እንዲያልቁ ትልቅ አስተዋጽዖ ስላበረከተ የ ዶ/ር አብይም የሉሲፈራውያኑ ደጋፊዎችም ባለውለታቸው ነበርና ነው። አሁን ሁለቱ የተዋሕዶ ጠላቶች በተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ጥቃት በመፈጸም ላይ ይገኛሉ።

በጅጅጋ የተዋሕዶ ልጆች ላይ የተካሄደው ጭፍጨፋ እንደ ማንቂያ ደወል ሊሆነን በተገባ ነበር። ዛሬ እየታዘብን ያለነው፤ ወንጀለኞች እየነገሡ፥ እውነተኞች እየኮሰሱ፤ ዘራፊዎች እየፋፉ፥ ከልብ አገልጋዮች እየተገፉ፥ መንፈ ሳውያኑ ሊቃውንት ሜዳ ላይ እየተጣሉ የመጡበትን ዘመን ነው። እስኪ በአሁኑ ሰዓት እየተሰደደ፣ እየታሠረና እየተገደለ ያለው ማን እንደሆነ እንመልከት። ሃፍረተቢሱ ገዳይ አልአብይ ገና ሃዘኗን ያልጨረሰችውን የጄነራል አሳምነውን ባለቤትና የልጆቹ እናትን ለማሠር ደፍሯል፤ ይህ እንዴት ይሆናል? በኢትዮጵያ ታሪክ ይህን መሰሉን ጽንፈኛ ተግባር የምናውቀው መንግስቱ ኃይለ ማሪያም የኃይለ ሥላሴንና ሚንስትሮቹን ቤተሰቦች አንድ ባንድ እየለቃቀመ ሲገድል በነበረበት ዘመን ብቻ ነው። ወያኔ እንኳን የ ብርሃኑ ነጋንና መሰሎቹን ቤተሰቦች ያንገላታበት ግዜ አልነበረም። ገዳይ አልአብይ እንደ ሞኞቹ ወያኔዎች በማሠር ብቻ አልተወሰነም፤ ተቃዋሚ የሚላቸውን እየመነጠረ ወዲያው ይገድላል።

ሰሞኑን ከታሠሩት ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን መካከል አንድም ጴንጤ ወይም ሙስሊም አለመኖሩ ብዙ ሊጠቁመን የሚችል ነገር አለ። አዎ! በተዋሕዶ ልጆች የግራኝ አህመድ እና የመንግስቱ ኃይለማርያም ቀይ ሽብር ዘመን ተመልሶ መጥቷል።

ቤተክርስቲያናችን ከታሠሩት ጋር የታሠረች፥ ከተገረፉት ጋር የተገረፈች፥ ከተገደሉትም ጋር አብራ የሞተች ናት፤ ደግሞም የካህን ሐዘንና ዕንባ ከባድ ነው፥ ውዳሴ ማርያምና ዳዊት ስለሚደግም ስር ይነቅላልና ለጉዳዩ ቤተክህነትም ምዕመናንም ተገቢውን አትኩሮት እንስጠው

እግዚአብሔር ሁሉንም ከእሥራታቸው ይፈታቸው ዘንድ ስለ ታሠሩ ሰዎች እንማልዳለን!

__________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: