Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • July 2019
    M T W T F S S
    1234567
    891011121314
    15161718192021
    22232425262728
    293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for July 3rd, 2019

የእስራኤል ፖሊስ አንድ ኢትዮጵያዊ እስራኤላዊ በመግደሉ እስራኤል ከፍተኛ ቀውስ ላይ ናት | በሰለሞን ምክኒያት

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 3, 2019

የእስራኤል ፖሊስ አባል አንድ ኢትዮጵያዊ እስራኤላዊ ወጣትን መግደሉ የኢትዮእስራኤሎችን ቁጣ ቀስቅሷል። የጠበቃ ድርጅት ኃላፊ እንዳሉት ሰለሞን ተካ የተገደለዉ ባለፈዉ ዕሁድ ሐይፋ ከተማ ላይ ነዉ።

ኢትዮጵያውያን ወደ እስራኤል ቢሄዱ አያልፍላቸው፣ ወደ አረብ ሃገራት ቢሄዱ አያልፍላቸው፣ ወደ አውሮፓ፣ አሜሪካና አውስትራሊያም ቢሄዱ ተገቢውን እርካታየተሞላበትን ኑሮ መኖር አይቻላቸው። አንድ ሃገር ያላቸው ኢትዮጵያ ናት፡ ነገር ግን እርሷንም ለማጥፋት ደፋ ቀና በማለት ላይ ናቸው። ወዴት ለመሄድ?

ሌላ የታዘብኩት፦

1. በእስራኤል ከኢትዮእስራኤሎች ጎን ሌሎች እስራኤላውያን በተፈጠረው ጽንፈኛ ድርጊት ላይ ተቃውሟቸውን ሲያሳዩና ሲያሰሙ፣ ይታያሉ፤ ሜዲያው ሲነጋገርበት፣ መሪዎች ይቅርታ ሲጠይቁ ይሰማሉ፥ በአረብ ሃገራት በእህቶቻችን ላይ በሚደረሰው ግፍ ላይ ለምንድን ነው አረቦቹ ከኢትዮጵያውያን ጎን ለፍትህ የማይቆሙት?

2. ላለፉት ወራት በሃገረ ኢትዮጵያ ብዙ ኢትዮጵያውያን ተፈናቅለዋል፣ ታስረዋል፣ ተገድለዋል፤ የራሳችን ፖሊሶች እናቶችንና ልጆቻቸውን፣ ጋዜጠኞችን እና ተቃዋሚዎችን በማንገላታት ላይ ናቸው። በእስራኤል አንድ ኢትዮጵያዊ ሲገደል የእስራኤል ከተሞች በእሳት ጋዩ፤ በኢትዮጵያ ግን ይህ ሁሉ ግፍ እየተፈጸመ ዜጎች መንገድ ላይ ወጥተው ተቃውሞዋቸውን ለማሰማት ያልደፈሩበት ምክኒያት ምን ይሆን? የእነ መሀንዲስ ስመኘው፣ የእነ ጄነራል ሰዓረ እና አሳምነው ግድያ ለምን የኢትዮእስራኤሎችን ዓይነት ቁጣ አለቀሰቀሰባቸውም? ምን የሚያስተኛቸው ወይም የሚያስራቸው ኃይል ቢኖር ነው?

__________________

Posted in Ethiopia, Infos | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: