አውሮፓውያን በኢትዮጵያ የሠሩትን ችቦ ለማቃጠል ሲዘጋጁ፤ እራሳቸው እግዚአብሔር በፈጠራት ፀሐይ ተቃጠሉ
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 25, 2019
ፓሪስ፣ ለንደን፣ በርሊን፣ ማድሪድ፣ ወዘተ ታይቶ በማይታወቅ ሙቀት እየተቃጠሉ ነው…ከሦስት ቀናት በፊት በማርክሮን ፈረንሳይ እንዲህ ሃይሎ የማያውቅ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር (5.1)…
የዛሬዋ ኢትዮጵያ “አርኤል”ን (የጽዮን ተራራን) ታስታውሰናለች፦
[ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ ፳፱፥]
፩ ዳዊት ለሰፈረባት ከተማ ለአርኤል ወዮላት! ዓመት በዓመት ላይ ጨምሩ፥ በዓላትም ይመለሱ።
፪ አርኤልንም አስጨንቃለሁ፥ ልቅሶና ዋይታም ይሆንባታል፤ እንደ አርኤልም ትሆንልኛለች።
፫ በዙሪያሽም እሰፍራለሁ፥ በቅጥርም ከብቤ አስጨንቅሻለሁ፥ አምባም በላይሽ አቆማለሁ።
፬ ትዋረጂማለሽ፥ በመሬትም ላይ ሆነሽ ትናገሪያለሽ፥ ቃልሽም ዝቅ ብሎ ከአፈር ይወጣል፤ ድምፅሽም ከመሬት እንደሚወጣ እንደ መናፍስት ጠሪ ድምፅ ይሆናል፥ ቃልሽም ከአፈር ወጥቶ ይጮኻል።
፭ ነገር ግን የጠላቶችሽ ብዛት እንደ ደቀቀ ትቢያ፥ የጨካኞችም ብዛት እንደሚያልፍ ገለባ ይሆናል።
፮ ድንገትም ፈጥኖ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር በነጐድጓድ፥ በምድርም መናወጥ፥ በታላቅም ድምፅ፥ በዐውሎ ነፋስም፥ በወጨፎም፥ በምትበላም በእሳት ነበልባል ይጐበኛታል።
፯ በአርኤልም ላይ የሚዋጉ፥ እርስዋንና ምሽግዋንም የሚወጉ የሚያስጨንቋትም፥ የአሕዛብ ሁሉ ብዛት እንደ ሕልምና እንደ ሌሊት ራእይ ይሆናል።
Leave a Reply