አረጋዊው አሜሪካዊ | ዋ! ለአሜሪካ መቅሰፍቱን እንዳታመጡ ግብረ-ሰዶማዊያንን ወደ ኢትዮጵያ አትላኩ
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 11, 2019
አዎ! የእነዚህ የዲያብሎስ ልጆች ተልዕኮ ስጋና ደምን ብሎም ነፍስን መስረቅ ነው።
አዎ! የእነዚህ የዲያብሎስ ልጆች ተልዕኮ ስጋና ደምን ብሎም ነፍስን መስረቅ ነው። የኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ፀረ–ግብረሰዶማዊ ድምጻቸውን ከፍ ሲያደርጉ በመላው ዓለም ተደማጭነትን አትርፈዋል። ሰሞኑን የተከሰተው ነገር የሚያስተምረን ትልቅ ትምህርት ቢኖር፡ ኢትዮጵያውያን በአንድ ልብ ሲቆጡ ዓለም እንደምትንቀጠቀጥ ነው። ከመንግስታቱ እና ደጋፊዎቻቸው በቀር በመላው ዓለም ድጋፍ ያገኘንበት ተግባር ነው። ከመንግስት አንጠብቅ፤ ጉዳዩ በሕዝቡና ቤተ–ክርስቲያኑ እጅ መግባት አለበት። ጉዳዩ የአዲስ አበባን ጴንጤ ከንቲባ አይመለከትም፤ ወገን አትታለል። ከሦስት ዓመታት በፊት ታቅዶ የነበረውን የግብረሰዶማዊነት ተቃውሞ ሰልፍን አሁን ነው ማዘጋጀት የሚኖርብን፤ አሥር ሚሊየን ኢትዮጵያውያን በመስቀል አደባባይ ዙሪያ ድምጻቸውን ማሰማት ይኖርባቸዋል፤ ያኔ ነው ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን በጤናማው ዓለም ዘንድ አክብሮት እና አድናቆትን በይበልጥ ለማትረፍ የሚበቁት። በመላው ዓለም የፀረ–ግብረሰዶማዊነት ዘመቻ ለመምራት የኢትዮጵያ ቤተ–ክርስቲያን ታሪካዊ ዕድል ያላት አሁን ነው።
ኢትዮጵያን አናሰርቃት! የማርያም መቀነታችንን (ሰንደቅ አላማ) እናስመልሳት!
Leave a Reply