Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2019
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

ኃይለኛ አውሎ ንፋስ በ ድሬዳዋ እና “አዳማ” በተባለችው ናዝሬት

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 18, 2019

[ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ ፰]

ነፍስን ዘርተዋል፥ ዐውሎ ነፍስንም ያጭዳሉ፤ አገዳ የለውም፥ ከፍሬውም ዱቄት አይገኝም፤ ቢገኝም እንግዶች ይበሉታል

ከጥቂት ሰዓታት በፊት በአዲስ አበባዋ እግዚአብሔርአብ ቤተክርስቲያን ስለተካሄደው የሰርግ ሥነሥርዓት ቪዲዮ አቅርቤ ነበር። አሁን ድሬዳዋንና በክህደት አዳማ የተባለቸውን ናዝሬትን ኃይለኛ አውሎ ነፋስ እንዳናወጣቸው ዜናው ደረሰኝ። የሚገርም ነው! ንፋስ፣ በተልይ አውሎ ንፋስ ቀላል ነገር አይደለም። እግዚአብሔር አምላክ እያናገረን ነው፣ ምልክቱን እያሳየን ነው፣ ይህ የማስጠንቀቂያ ደወል ነው።

ድሬዳዋ ሰኞ፡ ጥር ፲፫ / ፪ሺ፲፩ ዓ./ እግዚአብሔርአብ

ሰኞ የእግዚአብሔርአብ ታቦት ገብቶ ሲመለስ ፖሊስ መሬት በሚባል አካባቢ በተፈጠረ ግጭት የጀመረው የድሬዳዋ ውጥረት ዛሬም ቀጥሏል።

አርብ ዕለት ከማለዳ ጀምሮ ወጣቶች ሰልፍ ሲያካሄዱ፣ የተቃሞው ድምጾችን ሲያሰሙ፣ አልፎ አልፎም ድንጋይ ሲወራወሩ ነበር።

የወጣቶች ጥያቄ እየሰፋ መጥቶ የሥራ አጥነት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትህና የእኩልነት ጥያቄዎች ጎልተው መውጣት ጀምረዋል። በተለይም የድሬዳዋን ፍቅር አታደፍርሱ፣ በብሔር አትከፋፍሉን፣ «40/40/20» የተሰኘው የአስተዳደር ቀመር ይውደም፣ የሚሉ ተቃውሞዎች ሲሰሙ ነበር።

ረፋድ ላይ ድሬዳዋ ራስ ሼል አካባቢ «ከንቲባው ይውረድ!ድምጻችን ይሰማየሚሉ ድምጾችም ከፍ ብለው ይሰሙ ነበር። በዚያ ያልፉ የነበሩ ሦስት መቶ የሚገመቱ ወጣቶች ባንዲራዎችን ከመያዝ ውጭ ተቃውሟቸውን በሰላማዊ መንገድ ያቀርቡ ነበር።

[የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፩፥፳፭፳፯]

በፀሐይና በጨረቃም በከዋክብትም ምልክት ይሆናል፤ በምድር ላይም አሕዛብ ከባሕሩና ከሞገዱም ድምፅ የተነሣ እያመነቱ ይጨነቃሉሰዎችም ከፍርሃትና በዓለም የሚመጣበትን ከመጠበቅ የተነሣ ይደክማሉ፤ የሰማያት ኃይላት ይናወጣሉና። በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በኃይልና በብዙ ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል።

__________________

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: