Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for April 15th, 2019

እኅተ ማርያም ይህን ባወሳች ማግስት ድንቁ የፈረንሳይ ካቴድራል የእሳት አደጋ ሰለባ ሆነ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 15, 2019

በጣም የምያሳዝን ነገር ነው፤ ይህ ፈረንሳይ ውስጥ በጎብኝዎች ብዛት የመጀመሪያውን ቦታ የያዘ ታሪካዊ ቦታ ነው። በስምንት መቶ ዓመት ታሪኩ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው የእሳት አደጋ ሰለባ ሲሆን፤ እጅግ ያሳዝናል፤ የአንድ ሺህ ዓመት ታሪክ ያለው የፈረንሳውያን ብሔራዊ ማንነትና ኩራት በአንድ ሰዓት ዕልም ብሎ ጠፋ፡ ዋው!

ነገር ግን፤ በአገራችን ተንኮል ሲሠሩ በእነርሱ ላይ የፍርድ እሳት ይዘንብባቸዋል። የሰሜን ተራሮች ቃጠሎ ከሰማይ ይታያል። ባለፈው ወር ላይ ሰዶማዊው የፈረንሳይ ፕሬዚደንት ማክሮን ከ ዶ/ር አህመድ ጋር ሆኖ ላሊበላን አላግባብ ረግጦ ነበር። “ላሊበላን እናድሰው” ብለው ነበር፤ ግን ጉዳዩ ተንኮል እንዳለበት የላሊበላን ድንቅ ዓብያተክርስቲያናት እንዲሠሩ አባቶችን እና መላዕክቱን ያዘዘው ኃያሉ እግዚአብሔር ያውቃል። እስኪ ይታይን፤ ወገኖቼ፤ በጣም ብርቅ የሆነውን እና በጎብኝዎች ዘንድ የመጀመሪያውን ቦታ የያዘውን ላሊበላ ንብረታችንን በእድሳት መልክ ሲተናኮሉ የራሳቸው አንደኛ ቱሪስት ሳቢ ካቴድራል ተቃጠለ። ሆኖም፡ በተለይ በእነርሱ ፋሲካ ቅዱስ ሣምንት ይህ አደጋ መከሰቱ እጅግ በጣም አሳዛኝና አጠራጣሪም ነው። የመሀመድ አርበኞች ይህን ካቴድራል እናፈርሰዋለን በማለት ደጋግመው ይዝቱ ነበር።

ያም ሆነ ይህ፡ በላሊበላ ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን ያላግባብ ካባውን ለብሰው የነበሩት ፕሬዚደንት አማኑኤል ማክሮን እና ዶ/ር አብይ አህመድ ለራሳቸውም ለአገሮቻቸውም መጥፎ ዕድልን ይዘው መጥተዋል።

ማክሮን በላሊበላ ካባ ለብሶ በተመለስ ማግስት ፓሪስ በተቃዋሚዎቹ ጋየች | የድል ሐውልት ላይ አውሬው ታየ”

ሰዶማዊው ማክሮን ላሊበላን አርክሶ ከተመለስ በኋላ ፲፪ የፈረንሳይ ዓብያተክርስቲያናት ላይ ክፉኛ ጥቃት ደርሶባቸዋል

በሚለው ቪዲዮ ላይ ይህን ጽፌን ነበር፦

ፕሬዚደንት ማክሮን ከአጋሩ ጠ/ሚንስትር ግራኝ አህመድ ጋር በመሆን ወደ ላሊበላ ሄደው ቅዱስ ዓብያተክርስቲያናቶቻንን አርክሰዋል። የሚገርመው ደግሞ፤ የራሱን አገር ዓብያተክርስቲያናት በአግባቡ መንከባከብና መጠበቅ ያልቻለው አማኑኤል ማክሮን የላሊበላ ዓብያተክርስቲያናትን “ለማደስ ቃል ገብቷል” መባሉ ነው።

በክርስቶስ ተቃዋሚዎቹ አማኑኤል ማክሮን እና አብይ አህመድ ላይ መዓት በመምጣት ላይ ነው። የለበሱት ካባ መዘዝ? እነዚህን ሁለት የኢትዮጵያ ጠላቶች ካባዎቹ አቦዝነዋቸው (deactivate) ይሆን?“

የሚገርም ነው፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት እዚህ በእድሳት ላይ ከነበረው ካቴድራል ፊት ለፊት ቁጭ ብዬ አጠገቤ የነበርችው ሕፃን አሜሪካዊት እናቷን እንዲህ ብላ ስትጠይቃት መስማቴን አስታውሰዋለሁ፦

ማሚ እነዚያ ሰዎች እዚያ ሕንፃ ላይ ምን እያደረጉ ነው?እናትየዋም፦ “ቀለም እየቀቡት ነው፤ ዛሬ ቀብተው ከጨረሱ በኋላ ነገር ተመልሶ ጥቀርሻ ይሆናል” አለቻት፤ የአየር ብክለቱን ለመጠቆም።

__________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

ሸክ መሀመድ ለአሜሪካ ፕሬዚደንት ሴት ልጅ በቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አቀባበል አደረገ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 15, 2019

ምን? ማን? ለምን? የት? እንዴት?

ኢቫንካ ትራምፕ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አደጋ ህይወታቸውን ላጡት የሀዘን መታሰቢያ ላይ ለመሳተፍ ነበር ወደ ቤተ ክርስቲያን ያመራችው። ይህ አሶሲየትድ ፕሬስ የዜና ወኪል ያቀረበው ቪዲዮ ነው፤ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መሪ ሸክ መሀመድ አሚን እራሱን ሲያስተዋውቃት ይሰማልሙሉውን እስካላየን ድረስ አንፍረድምሆኖም፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ወይ የፈረንጅ ወይ የግራኝ አህመድ ተንኮል ሊኖርበት ይችላል። ቀደም ሲል በእስራኤል ፕሬዚደንት በ ቢንያም ኔተንያሁ ላይ በ ብሔራዊ ሙዚየም የሠሩትን ተንኮል እናስታውሳለን። እስልምና ተቃውሚውን ፕሬዚደንት ትራምፕን ለመተናኮል ይሆን? ምስል ሺህ ቃላት ይናገራል!

በሌላ በኩል፡ የፕሬዚደንት ትራምፕ ልጅ ትህትናዋ ደስ ይላል፤ ሴት ልጅ እንዲህ ነው የሚያምርባት – የካቶሊኩ ካርዲናልም ይታያሉ – ሆኖም ግን፡ የአንድ ዓለም ሃይማኖት የመፍጠሪያ አካሄድ እንዳይሆን መጠንቀቅ ይኖርባታል።

__________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

የኢቫንካ ትራምፕ ጉብኝት የሚያሳየን ባቢሎን አሜሪካ ከዝሙትዋ ቍጣ ወይን ጠጅ/ ቡና የተነሳ ትወድቃለች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 15, 2019

አሜሪካ በሁለቱ “በ” ዎች ሱስ ተጠምዳለች፤ ሰክራለች፦ ቡና እና ቤንዚን/ ነዳጅ ዘይት። የዮሐንስ ራዕይ “ወይን ጠጅ” የሚለን ቤንዚን/ የነዳጅ ዘይትና ቡና መሆናቸው ነው። እንዲያውም ቡና ነው በይበልጥ ደምና መቅኒ ውስጥ የሚገባው ኃይለኛ ዝሙት አስያዥ እና ነፍስ ገዳይ መጠጥ። ቀስ ብሎ የሚገባ

እኔ የፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ደጋፊ ነኝ፤ ቃለ የገባለትን ተግባራዊ ለማድረግ ስለሚፈጨረጨሩ፤ ሞኟ ልጁ ግን በተንኮለኛው ባሏ ግፊት የሉሲፈራውያን አምባሳደር ሆናለች፤ ታሳዝናለች፤ ግን በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ላይ በእነ ጃዋር በኩል እየፈጸሙት ባሉት – በአሜሪካንህንዶች ላይ የተፈጸመው ዓይነት – ጭፍጨፋ ሳቢያ ባቢሎን አሜሪካ ትወድቃለች። አዎ! ባቢሎን አሜሪካ ከዘረኞች፣ ወራሪዎችና ጨፍጫፊዎች ጋር ብቻ ነው በመላው ዓለም ተመሳጥራ እየሠራች ያለችው።

የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፰

ከዚህ በኋላ ታላቅ ስልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች

በብርቱም ድምፅ። ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች፥ የአጋንንትም ማደሪያ ሆነች፥ የርኵሳንም መናፍስት ሁሉ መጠጊያ የርኵሳንና የተጠሉም ወፎች ሁሉ መጠጊያ ሆነች

አሕዛብ ሁሉ ከዝሙትዋ ቍጣ ወይን ጠጅ የተነሳ ወድቀዋልና፥ የምድርም ነገሥታት ከእርስዋ ጋር ሴሰኑ የምድርም ነጋዴዎች ከቅምጥልነትዋ ኃይል የተነሳ ባለ ጠጋዎች ሆኑ ብሎ ጮኸ

_______________

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

እኅተ ማርያም | ዶ/ር አህመድ ቀን ሰው ሌሊት አውሬ ነው፤ መሀንዲስ ስመኘውን አስገድሎታል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 15, 2019

“ደሙ አብይ አህመድን፣ ሰመኦን በረከትን እና አዜብ መስፍንን ይጣራል”

“ልክ እንደ ግራኝ አህመድ ዘመን ተዋሕዶን ለማጥፋት ሩጫ ላይ ናቸው”

ግራኝ አህመድ ሲያደርገውም የነበረው ቤተክርስቲያንን ማቃጠል ነው፤ የዛሬዎቹ የእርሱ ልጆችም፣ በእርሱ እምነት ነን የሚሉትም ዓብያተክርስቲያናትንና ደኖችን በማቃጠል የኢትዮጵያን ታሪክ ሙልጭ አድርገው ለማጥፋት በመታገል ላይ ናቸው። ጠቅላይ ሚንስትሩም ዓላማ ስላለው ምንም ማድረግ አይፈልግም፤ ሰውዬው ቀን ሰው ሌሊት አውሬ ነው፤ ይህን አስመልክቶ ሕዝቡ ዓይኑ ሊገለጥለት አልቻለም፤ እግዚአብሔር ግን መልስ ይሰጣቸዋል።”

ካልደፈረሰ አይጠራም፤ አገራችን መጽዳት አለበት።”

ታዛቢዎች፣ ተንታኞች ወይም የሜዲያ ባለሙያዎች ተብለው ብዙ ተከታዮችን ካተረፉት ሺህ ወንዶች፡ አንዷ እህታችን በጀግነነቷና በግልጽነቷ በሺህ እጥፍ ትበልጣቸዋለች፤ የምትናገረው ሁሉ ትክክል ነው፤ መታወቅም ያለበት ሃቅ ነው፤ የእኛ እውርነትና ድንቁርና ነው እንጅ ይህ የአደባባይ ምስጢር ነው፤ በመሀንዲሱ ወንድማችን እና በሕዳሴው ግድብ ላይ ዶ/ር አህመድ ከግብጽ እና አረቦች ጋር በመመሳጠር የሠራውን በታሪካችን ተወዳዳሪ የማይገኝለትን ደባ በማጋለጥ በፍጥነት ለፍርድ ማቅረብ ነበረብን/ አሁንም ማቅረብ አለብን።

በእኔ በኩልም፡ በተለይ፡ ግራኙ አብይ አህመድ ኢንጂነር ስመኘውን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ብዙ ያልተነገረላቸውን ኢትዮጵያውያንን፤ ክንፈ ገብርኤልን ጨምሮ፤ አስገድሏል፣ በጅጅጋ እና ሰሜን ሸዋ ዓብያተ ክርስቲያናትንና መነኮሳቱን አቃጥሏል፣ እናቶችን ከለገጣፎ አፈናቅሏል፣ በጌዲኦን ሕዝብ ላይ የተካሄደውን “የሱዳን ዳርፉርመሰል” ጭፈጨፋ፣ የባንኮች ዘረፋ ወዘተ። በአጭር ጊዜ ውስጥ ዓይኖቻችን እያዩ የተሠራው ወንጀል ተቆጥሮ አያልቅም።

ሰውዬው ስልጣን እንደያዘ ፈጥኖ “የቀን ጅቦች” ማለት የጀመረው ወይም ሰዶማውያንን የሚመለከትና የኢንሳ ጥናታዊ ፊልሞች እንዲሠሩ ያዘዘው፡ ብሎም የማሕበራዊ ሜዲያዎች ላይ ሳንሱር ለማድረግ የሚንቀሳቀሰው፡ እራሱ የራሱን ማንነት እና የሚያደርጋቸውን ጽንፈኛ ድርጊቶች ለመሸፈን ሲል ነው። ይህ ዓይነት ባሕርይ በብዛት በመሀመዳውያንና ዘረኛ ሰዎች ዘንድ ነው በግልጽ የሚታየው፤ በእንግሊዝኛው Projection„ አንጸባራቂነት / ማሳየት/ ይባላል፤ ማለትም እራሳቸው ቆሻሾች መሆናቸውን ስለሚያውቁ ከመቀደማቸው በፊት እራሳቸውን ንጹህ አድርገው ሌላውን ቆሻሻ ያደርጋሉ። እነርሱ መናፍቅ ሆነው ሌላውን ኩፋር/ መናፍቅ ይላሉ፣ እነርሱ በምንዝርነት፥ በዝሙት፥ በሌብነት፥ በውሸትና በስድብ ዓለማቸው ውስጥ ተዘፍቀው በእነዚህ ሃጢአቶች ሌላውን ቀድመው ይኮንናሉ፣ እነርሱ በዳዮች እና ገዳዮች ሆነው እኛ ተበድለናል እያሉ ሌላውን ይወቅሳሉ። የዋቄዮ አላህም ልጆች የዚህ ዓይነት ባሕርይ ነው ያላቸው።

____________________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: