Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for April 7th, 2019

የሩሲያ ወታደሮች ወደ ቤተ ክርስቲያን ይሄዳሉ፣ አብራሪዎች አውሮፕላን ውስጥ የቅዱሳት ስዕላትን ይይዛሉ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 7, 2019

ቀዩ የሩሲያ ሠራዊት ወደ ክርስቲያን ሠራዊትነት እየተለወጠ ነው። ሠራዊቱ ቁስጥንጥንያን(ኢስታንቡልን) ከወራሪ ቱርኮች ቁጥጥር ነፃ የሚያወጣበት ቀን ሩቅ አይደለም።

የሚገርም ነው፤ ትናንትና “እግዚአብሔር የለም፤ ሌኒን ነው አምላካችን” ሲሉ የነበሩ ሩሲያውያን ወደ እናት ቤተክርስቲያናቸው በመመለስ ይህን ያህል መሰጠትንና ቍርጠኝነትን አሁን ያሳያሉ። እንዴት ደስ ይላል! እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን!

የኛዎቹስ? መቼ ነው ከኮንዶምኒየም ዘበኝነት ተላቅቀው የቤተክርስቲያናችን ጠባቂ አርበኞች በመሆን አስመራን፣ ጂቡቲን፣ ሞቃዲሾንና ካርቱምን ከመሀመድ ወራሪዎች ነፃ የሚያወጡት? ይህ ጊዜ መምጣቱ አይቀርም። እነዚህ የቀደሞዋ ኢትዮጵያ ግዛቶች ሁሉ አንድ በመሆን ታላቋን ኢትዮጵያ እንደገና እንደሚመሠርቱ አልጠራጠርም! ሌላ የተሻለ አማራጭ የለምና!

_________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የበገና ዜማ በ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ ክርስቲያን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 7, 2019

እንኳን አደረሰን!

የመንበረ ጸባዖት ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን በ፲፰፹፫ / 1883 .ም በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት የተመሠረተ ሲሆን ቤተ ክርስቲያኑ የ፻፳፰/ 128 ዓመት ዕድሜ ባለቤት ነው።

የቅዱስ በዓለወልድ /መካነ ሥላሴ/ ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተው በ፲፰፹፫ / 1883 .ም በዳግማዊ አፄ ምኒልክ አማካይነት ሲሆን ለምሥረታው የተነሳሱበትም ዋናው ምክንያት አንድ ባሕታዊ መነኩሴ ከቤተ መንግሥትዎ በስተቀኝ ባለው ከፍታ ቦታ ላይ ሦስት ነጫጭ ርግቦች መጥተው ሲያርፉ በራዕይ አይቻለሁና (መካነ ሥላሴ) የሚል ጽሕፈት ያለበት ጽላት አስፈልገው በማምጣት እንዲተክሉ እግዚአብሔር አዟልና እንዲተከል ይሁን።ስለተባሉ በዚሁ መነሻነት መካነ ሥላሴ የሚል ጽሕፈት ያለበት ጽላት ሲያስፈልጉ ቆይተው ከአዲስ ዓለም በላይ ፉየታ ከሚባለው ቦታ እንዳለ በጥቆማ ስለደረሱበት ለቦታው ሌላ ጽላት ተፈልጎለት በንጉሡ ትእዛዝ በአለቃ ወልደ ያሬድ ኤላሪዮን አስመጭነት በወቅቱ የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳሳት በነበሩት በግብፃዊው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ማቴዎስ እጅ ከተረከቡ በኋላ ዳግማዊ አፄ ምኒሊክ ንጉሠ ሸዋ በተባሉ በ25ኛው ዓመት የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ሆነው በነገሡ በአንደኛው ዓመት ታህሣሥ ፳፪ / 22 ቀን ፲፰፹፫ / 1883 /ም የአዛዥ ዘአማኑኤል እልፍኝ ተባርኮ በዚሁ ቅዱስ ሥፍራ በመቃኞ /በመቃረቢያ/ ቆይቶ ይህ አሁን ለዕድሳት የበቃው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ለ12 ዓመታት በግንባታ ላይ ከቆየ በኋላ በ ፲፰፺፭ / 1895 /ም በመጠናቀቁ መስከረም ፯ / 7 ቀን ፲፰፺፭ / 1895 /ም ታቦተ ሕጉ ከነበረበት መቃረቢያ ወጥቶ በዓለ ንግሥ ተደርጎለት አዲስ ወደ ታነፀው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ገብቷል

በዚሁ አጋጣሚ ሳይጠቀስ የማይታለፈው ዐቢይ ጉዳይ ደግሞ ቀደም ሲል ጽላቱ ከግራኝ መሐመድ ወረራ በፊት ወረኢሉ ደሴ የነበረ ሲሆን በግራኝ ወረራ ምክንያት ካህናቱ አሽሽተው ወግዳ ወስደው አኑረው ለብዙ ዘመናት ከቆየ በኋላ የራስ ጎበና ባለቤት ወ/ሮ አየለች ከወሎ ወግዳ አስመጥተው አዲስ ዓለም በላይ ፉየታ ከተባለው ቦታ ላይ አስተክለው እንደነበርና ታሪኩ እንደሚያስረዳው በአፄ ምኒልክ ትዕዛዝ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ በዚሁ ቦታ ላይ የተተከለ ሲሆን መካነ ሥላሴ የሚለው የደብሩ ስያሜም የተሰጠው ከጽላቱ ላይ ከተገኘው ጽሕፈት በመነሳት እንደሆነ ከታሪኩ ለመረዳት ተችሏል።

የድንግል እናታችን ልጅ ስሞቹ ፦ ቃል ወልድ አማኑኤል ኢየሱስ ክርስቶስ መድኃኔ አለም ሆኑ ትርጓመያቸውም፦

#ቃል ማለት፦ አንደቤት መናገርያ ማለት ስሆን ከ3ቱ አካላት አንዱ እግዚአብሔር #ወልድ በህልውነት/በመሆን ግብሩ የ #አብ እና የ #መንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ስሆን የእግዚአብሔር ቃል ይባላል። ራእይ 1913 “በደም የታለሰ ልብስም ለብሶአል ስሙንም ቃል እግዚአብሔርአሉት። ቍላስ.116 “በእርሱ ቃልነት እግዚአብሔር ሁሉን ፈጥሮአልና….”

#ወልድ ማለት፦ ከ3ቱ አካላት ፩(1)ዱ ወልድ ስሆን ልጅ ማለት ነው የ #ወልድ አካላዊ ግብሩ መወለድ ማለት ነው የ #አብ የባሕርይ ልጅ ስለሆነ እግዚአብሔር ወልድ ይባላል። ገላ.44,, ዮሐ.516,, ማቴ 317…

#አማኑኤል ማለት፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው። ማቴ 123። ይህን በት.ኢሳ 714 ላይ ስሙን እናገኛለን። ይህ ማለት ከድንግል በተዋህደው ተዋህዶ አምላክ ሰው ሆነ ዮሐ.114 …….. 1ኛ ቆሮ 1521 አዳምን የመጀመርያው ሰው ይላል ክርስቶስን ደግሞ ሁለተኛው ሰው ይለዋል።

#ኢየሱስ ማለት፦ መድሃኒት ማለት ነው ይህን መጽሐፍ ቅዱስም ይናገራል ሉቃስ 211 “እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት ተወልዶላችኃልእንዳለ መልአኩ ለእረኞች….

#ክርስቶስ ማለት፦ ቅቡ /የተቀባማለት ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን እና በመሰሎቿ አብያተ ቤተክርስትያናት የተዋሃደተብሎ ይተረጉማል።

#መድኃኒአለም ማለት፦ የአለም መድኃኑት ማለት ነው። በእርሱ አለም ስለዳነ (በሞቱ አለምን ስላዳነ) መድኃኒአለም የአለም መድሃኒት እንለዋለን። ሉቃስ 211 ላይ እኔሆ ለሕዝብ ሁሉ የምሆን መድኃኒት እንዳላለ ሉቃስ፤ ዮሐ.129 ላይ መጥምቁ ዮሐንስ እነሆ የአለምን ኃጢአት የምያስወግድ የእግዚአብሔር በግእንዳለው እንደገና በሮሜ 512-21 ስናነብ በአንድ ሰው በአዳም ምክንያት ሞት ወደ አለም እንደመጣ ሁሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትም አለም እንደዳነ ይናገራል…………..እኛ ኦርቶዶክሳዊያን በነዚህ ስሞች አምላካችን ጌታችንና መድኃኒታችንን እናከብረዋለን እንጠራዋለን እናመልከዋለን ። ኢየሱስ ብቻ ስሙ ነው ሌሎችን ከየት አመጣችሁ ለምን ባለወልድ አማኑኤል መድሃኒአለም እያላቹ ትጠሩታላችሁ ኢየሱስ ማለት ብቻ እንጅየምሉ ወገኖቻችን አሉና እነዚህን ስሞችን እኛ ኦርቶዶክሶች ፈጥረንለት ሳይሆን መጽሐፍ ቅዱሱ እራሱ እንደምጠራው መገናዘብ ይገባናል።

ለስም አጠራሩ ክብርና ምስጋና ይድረሰው የእኛ ጌታ የድንግል ማርያም ልጅ ጌታችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ። ክብር ለወለደችው ለድንግል!!!

_________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: