Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for April 2nd, 2019

እነዚህ ሁለት “ጎረምሶች” የዓለም መሳለቂያ አደረጉን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 2, 2019

እንሳቅ? እናልቅስ? ወይስ እየሳቅን እናልቅስ?

ዴንማርክ ሰሞኑን ከኢትዮጵያ ጋር ተጣብቃለች። ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ በዴንማርኳ አዓርሁስ በተካሄደው የዓለም ዋንጫ አገር አቋራጭ የሩጫ ውድድር ላይ ከ ሃያ ዓመት በታች እድሜ ያላቸው ሯጮች ብቻ መሳተፍ ነበረባቸው። ነገር ግን በዚህ ውድድር ኢትዮጵያን ወክለው የተሳተፉት፡ ጌትነት የትዋለ እና ድንቅዓለም አየለ፡ እድሜያቸው አሥራ ስምንት ነው ተብለው እንዲሳተፉ ተደርጓል፤ የተመለከተ ሁሉ ግን ሁለቱም አረጋውያን መሆናቸውን በማየቱ አሁን የአውሮፓውያን ማሕበረሰባዊ ሜዲያ መሳለቂያ ሆነዋል። በተለይ የስፔይኑ የስፖርት ጋዜጣ፡ “አስ/ASሰፊ የሆነ ዘገባ በዚህ ጉዳይ ላይ አቅርቧል። ሯጮቹ አሥራ አንደኛ እና ሃያ አንደኛ ወጥተዋል። እውነትም ጌትነት የትዋለ፤ ለመሆኑ ድንቅዓለምስ የትዋለ? የፊልም ባለሙያዎች እስኪ“የትዋለ እና ድንቅዓለም”በማለት ድራማ ስሩላቸው!

ውድድሩን ተከታትለው አንደኛና ሁለተኛ በመውጣት ያሸነፉት ጀግኖቹ ኢትዮጵያውያን ሚልከሳ መንገሻ እና ታደሰ ወርቁ ናቸው።

_____________________

Posted in Curiosity, Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: