Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • March 2019
    M T W T F S S
     123
    45678910
    11121314151617
    18192021222324
    25262728293031
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for March 31st, 2019

ፀረ-ክርስቶሷ ቱርክ ጥንታዊውን የቅድስት ሶፊያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መስጊድ ልታደርገው ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 31, 2019

ሀጊያ ሶፊያወይም ቅድስት ጥበብበሚለው የመድኃኔዓለም ስሙ የተሰየመው ይህ የእግዚአብሔር ወልድ ቤተ ክርስቲያን በቁስጥንጥንያ መንበር ታላቁ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ሲሆን እጅግ አስደናቂ የሕንጻ ጥበብ የታየበትና የብዙ ቅዱሳን አጽም ያረፈት ታላቅ ካቴድራል ነበረ። በኦርቶዶክሳዊያንና በዓለም የክርስትና ታሪክ ውስጥ ታላቅ ሥፍራ ያለውና በዩኔስኮ ከተመዘገቡ የዓለም ቅርሶች አንዱ የሆነው ይህ ቤተ ክርስቲያን በ1453 ዓ ም ቁስጥንጥንያ፡ ያሁና ኢስታምቡል፡ በኦቶማን ቱርክ እጅ ስትወድቅ በሱልጣን መሀመድ ዳግማዊ ትእዛዝ ወደ መስጊድነት ተቀይሯል። ከ1935 ዓ ም እስከ ዛሬም ድረስ ደግሞ ወደ ቤተመዘክርነት ተቀይሮ የቀደመ ታሪኩ ብቻ እየተነገረ ለጎብኚ ክፍት ሆኖ ይገኛል። አሁን እብዱ የቱርክ ፕሬዚደንት ሬሴፕ ጣይብ ኤርዶጋን በሙስሊም ወንድሞቹ ግፊት ይህን ታሪካዊ ቤተክርስቲያን መስጊድ የማድረግ ፍላጎት እንዳለው አውስቷል።

የክርስቲያን ሃገራትን በመውረር እስካሁን ድርስ ይዛ የቆየችው የክርስቶስ ተቃዋሚዋ ቱርክ መጥፊያዋ ተቃርቧል፤ ቁስጥንጥንያንም ለግሪኮችና አርመኖች በቅርቡ ትመልስ ዘንድ ትገደዳልች፤ ስልዚህ በጣም ያቁነጠንጣታል ያለው። እንደ እኛዎቹ ሁሉንም ነገር “ኬኛ” ትላለች። አውሮፓ የእኔ ነው፣ ሰሜን አፍሪቃ የእኔ ነው ትላለች። እንዲያውም “አሜሪካን እኛ ቱርኮች ነን ያገኘነው” በማለት እብዱ ኤርዶጋን በቅርቡ ቀለባብዶ ነበር። “ኬኛ” የመሀመዳውያን መንፍስ እንደሆነ እያየን ነው?

የሀጊያ ሶፊያ ቤተክርስቲያን ወደ ቀደመ ክብሩ መመለስ በዓለም ዙሪያ ለሚገኙ ኦርቶዶክስ ምእመናን ታላቅ ደስታ የሚሆን ነው። በዓለም ዙሪያ ብዙ የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት በሀጊያ ሶፊያ ቤተክርስቲያን ሕንጻ አምሳል መሠራታቸውም ለቤተክርስቲያኑ የሠጡትን ትልቅ ሥፍራ የሚያስረዳ ነው። ሀጊያ ሶፊያን መስለው ከተሠሩ ቤተክርስቲያኖች መካከል በግብጽ ካይሮ የሚገኘው የዘይቱን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንና በኢትዮጵያ የሚገኘው የርእሰ አድባራት አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ይጠቀሳሉ። በቱርክ እና ግብጽ የሚገኙት ሙስሊሞችም አብዛኛዎቹን መስጊዶቻቸውን ከዚህ ድንቅ ቤተክርስቲያን ሕንፃ ኮርጀው ነው የሠሯቸው።

ቀድሞ ቁስጥንጥንያ ዛሬ ደግሞ ኢስትንቡል በመባል የምትታወቀው የግሪኮችና አርመኖች ከተማ ስሟን ያገኘችው „εἰς τὴν πόλιν“ „is tim boli (n)„ ከሚለው የግሪክኛ ቃል ነው። “ከተማው” ወይም “በከተማው” ማለት ነው፤ ለቁስጥንጥንያ። የኦርቶዶክስ ጠላት የሆኑት ቱርኮች ግሪክ ኦርቶዶክሶችን የጎዱ ስለመሰላቸው ነበር ቁስጥንጥንያን ኢስታንቡል ብለው የሰየሙት። ልከ በአገራችንም ከሃዲዎቹ የዋቄዮ አላህ ልጆች ኦርቶድክስ ኢትዮጵያን ያሸነፉ መስሎ ስለታያቸው አዲስ አበባን “ፊንፊኔ” ብለው ለመጥራት ይታገላሉ፤ ግን ፊንፊኔ የአማርኛ ቃል መሆኑን አላወቁም ነበር

_________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , | 1 Comment »

ብፁዕ አቡነ ጎርጎሪዮስ | ”የኢትዮጵያውያን መታወቂያ፤ ሰላምም፣ ፀሎትም፣ መከባበረም፣ እንግዳ መቀበልም ነው”

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 31, 2019

የሰላም፣ የፍቅርና የበረከት በዓል ያድርግልን!

ግን እስኪ አሁንም ደግመን እናስበው፤ ይህን ተወዳዳሪ የሌለውን ፀጋና በረከት ትይዝ ዘንድ “ደብረ ዘይት” ለመባል የበቃቸውን ከተማ “ቢሸፍቱ” ያሉት ምስጋና ቢሶች ምን ያህል ቢያብዱ ነው? ከ ፍየሉ ጋር ተሰልፈዋል፡ እንዲሁም የኢየሱስ ክርስቶስ ጠላት መሆኑን መርጠዋል ማለት ነው። በጣም ይገርማል፤ ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት ይጮሃሉ፣ አሸዋና ሲሚንቶ ተቀላቅሎ ለተሠራው ኮንዶሚኒየም ግን እስከ መጨረሻው እንሞታለን ይላሉ፤ ነፍሳቸውን ሸጠው ዓለምን ለመውረስ በጥላቻ ኃይል ይጓዛሉ። ነፍሳቸውን ለሸጡለት ዲያብሎስ ዛፍ ሊተክሉለት በመሻት ናዝሬትን አዳማ፣ ደብረ ዘይትን “ቢሸፍቱ” ብለው ሰየሟቸው፣ ወርቅን እምቢ ብለው መዳብን መረጡ። አቤት ምስጋና ቢስነት፣ አቤት እብደት! አቤት ቅሌት! አቤት ንቀት! አቤት ትዕቢት፤ አቤት የሚመጣባቸው ፍርድ!

በሌላ በኩል አንድ ሌላ የሚያሳዝነው ነገር፤ ልክ ብፁዕ አቡነ ጎርጎሪዮስ ትምሕርቱን መስጠት ሲጀምሩ ገንዘብ ቆጠራውም አብሮ መጀመሩ ነው፤ ክቡር ታቦቱ ፊት፣ የድምጽ መቅጃው አጠገብ፤ ይህም ከበስተጀርባው በሚረብሽ መልክ ይሰማል። እንደው ምናለ ስነ ሥርዓቱ ሁሉ ተገባድዶ ሁሉም ወደየቢቱ ከተመለሰ በኋላ ለገንዘቡ ጊዜ ቢሰጥ? ምናለ ገንዘብን የተመለከት ነገር ሁሉ እንዲህ በቤተ ክርስቲያን አደባባይ ባይሠራ! ወይስ ተንኮል ነገር አለ? መቼስ ዲያብሎስ ሁሌ ከቤተክርስቲያን አይርቅምና።

_____________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: