በጣም የሚገርምና አሳዛኝ የሆነ ክስተት በፈረንሳይ እየታየ ነው። ለሦስት መቶ ዓመታት ያህል ታይቶ የማይታወቅ አብዮት በፈረንሳይ እንደገና ተቀስቅሷል። በትናንትናው ዕለት የቢጫ ሰደርያ ለባሽ ተቃዋሚዎቹን ለማደን የፈረንሳዩ ፕሬዚደንት ሠራዊቱን ጠርቶ ነበር፤ ማለትም፡ ወታደሮችና ከባድ መሣሪያዎች በፈርንሳይ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በፓሪስ ከተማ መንገዶች ላይ እንዲሠፍሩ ተደርገዋል። የተቃዋሚዎቹ ኃይል ጠንከር ካለም ወታደሮች ጥይት ተኩሰው እንዲገድሉ ማክሮን ፈቃድ ሰጥቶ እንደነበር ተጠቁሟል። ዋው!
በሌላ በኩል፡ አይሁዶች ፈርንሳይን በብዛት በመልቀቅ ወደ እስራኤል ሄደው እየሠፈሩ ሲሆን፤ በክርስቲያኖችና ዓብያተክርስቲያናቶቻቸው ላይ እየተካሄደ ያለው ጥቃትም አሳሳቢ በሆነ መልክ በመጧጧፍ ላይ ነው።
ፕሬዚደንት ማክሮን ከአጋሩ ጠ/ሚንስትር ግራኝ አህመድ ጋር በመሆን ወደ ላሊበላ ሄደው ቅዱስ ዓብያተክርስቲያናቶቻንን አርክሰዋል። የሚገርመው ደግሞ፤ የራሱን አገር ዓብያተክርስቲያናት በአግባቡ መንከባከብና መጠበቅ ያልቻለው አማኑኤል ማክሮን የላሊበላ ዓብያተክርስቲያናትን “ለማደስ ቃል ገብቷል” መባሉ ነው።
በክርስቶስ ተቃዋሚዎቹ አማኑኤል ማክሮን እና አብይ አህመድ ላይ መዓት በመምጣት ላይ ነው። የለበሱት ካባ መዘዝ? እነዚህን ሁለት የኢትዮጵያ ጠላቶች ካባዎቹ አቦዝነዋቸው (deactivate) ይሆን?