Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 15, 2019
ወቸውጉድ! አንድ ቀን ጀርመን የኛ ናት፤ ልዩ ጥቅም ይገባናል ማለታቸው አይቀርም። “ፅጌረዳውም፣ ቡናውም፣ ቋንቋውም፣ የላቲን ፊደሉም” ኬኛ….
በዘረኝነት ጋኔን የተለከፈው ወንድማችን ያሬድ ዲባባ ይባላል፤ በ አስራ ሁለት ዓመት እድሜው ነው ጀርመን የገባው። በሰሜን ጀርመን (ብሬመን + ሃምቡርግ) ለሚገኝ የቴሌቪዥን እና ራዲዮ ጣቢያዎች በጋዜጠኝነት ዝናን ያተረፈ ነው፤ አብዛኛዎቹ ጀርመኖች የማይናገሩትን የሰሜን ጀርመን ቀበሌኛ/ዲያሌክት (ፕላት ጀርመን፤ ለእንግሊዝኛ እና ሆላንድኛ ይቀርባል) አቀላጥፎ ይናገራል። በቋንቋ ችሎታው አደንቀዋለሁ (እኔ እራሴ በሰባት የተለያዩ ሕዝቦች መካከል የኖርኩና ቋንቋዎቻቸውንም በሚገባ የምናገር “ኩሩ ኢትዮጵያዊ” ነኝ፤ የእርሱን ያህል ግን አልሆንም)፤ ያሬድ እንግሊዝኛውንም ሰምቼዋለሁ ጥርት ያለ እንግሊዝኛ ነው የሚናገረው። ነገር ግን፡ እንዲሁ በቀላሉ የተገኘ ስጦታ አይደለም፤ ብዙ ተከፍሎበታል፤ ነፍስ ተሽጧል፤ ስለዚህ ያሬድ ዲባባ ማንነቱን የሸጠና እናት ኢትዮጵያን የካደ ደካማ ዘረኛ ነው።
[የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ ፰፥፴፮]
“ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?”
ፕሮቴስታንት ጀርመኖች ኢትዮጵያን ለመበታተን ባላቸው የረጅም ጊዜ ህልም እንደ ያሬድ ያሉትን ሞኞች ይጠቀሙባቸዋል። ከአንድ ከስድስት ዓመት በፊት ያሬድ ዲባባና ደነነሽ ዘውዴ (በጀርመን ቴሌቪዥን ድራማዎችን በመሥራት የምትታወቅ ኢትዮጵያዊት ናት) በተመሳሳይ ፕሮግራም ላይ አቅርበዋቸው በጎሳ ሲያባሏቸው ነበር፤ ሆን ብለው ነበር ያን ፕሮግራም ያዘጋጁት።
የመናፍቁ የማርቲን ሉተር ፕሮቴስታንት ጀርመን በአምስት መቶ አመት ውስጥ ክርስትናን አጥፍታ ወደ ጣዖት አምልኮት በመመለስ ላይ ነች። የክርስቶስ ተከታዮች የሆኑት ምናልባት አስር በመቶ አይሆኑም፤ ግን በግዛቷ የቀሩት ጥሩ ሰዎች እነርሱ ብቻ ናቸው፤ ከአገራችን ጋር ግን ግኑኝነት የላቸው፤ ወደ አገራችን የሚገቡት ግን ልክ “ወንጌላዊ” ነኝ በማለት ወደ ኢትዮጵያ ተጉዞ እደየነበረው ጀርመናዊው ዮኻን ክራፕፍ ዓይነት ሰዎች ናቸው። ይህ ሰው ከመቶ አመታት በፊት ኦሮሚያ የተባለውን ግዛት ለመመሥረት የተነሳሳ፣ የኢትዮጵያን ቀጥተኛ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ለመዋጋት የዘመተ እርኩስ የክርስቶስ ተቃዋሚ ሰው ነበር።
“ኦሮሚያ‘ መርዝ ነው!!!
“እውነቱን ትተው ውሸቱን፤ ሰፊውን ጠልተው ጠባቡን፣ የሚያኮራውን ንቀው የሚያቀለውን፣ የሚያስከብረውን አውግዘው የሚያዋርደውን፣ ግዕዝን ትተው ላቲኑን፣ የማርያም መቀነትን ትተው የዘንዶ ቀበቶን፣ ክርስቶስን ትተው ዲያብሎስን፣ እግዚአብሔርን ትተው ዋቄዮን፣ ተዋሕዶን ትተው አምልኮ ጣዖትን፣ ኢትዮጵያን ትተው ኦሮሚያን መርጠዋል። በዚህም በቅርቡ ክፉኛ ይቀጣሉ። መዳን የሚፈልጉ ዋቄዮ አላህን ትተውና ንስሃ ገብተው ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ቶሎ ቢሰለፉ ይሻላቸዋል።
_______:_›_____
Like this:
Like Loading...
Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: ሽቴፋን ሞሊኑ, ኢትዮጵያ, ኦሮሚያ, ኦሮሞ, ወራሪዎች, ዘረኝነት, ያሬድ ዲባባ, ዮኻን ክራፕፍ, ጀርመን, ጀርመን ቴሌቪዥን, ጋላ, ፀረ-ኢትዮጵያ ሤራ, ፀረ-ክርስቶስ, ፕላት ጀርመንኛ ዲያሌክት, ፕሮቴስታንቶች | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 15, 2019
ከ ፲፰ ዓመታት በፊት፡ በኢትዮጵያ አዲስ ዓመት መስከረም ፩ ላይ፡ በአውሮፕላኖች ጥቃት የጀመረው ታሪካዊ የማስጠንቀቂያ ምዕራፍ አሁን በኢትዮጵያ አየር መንገድ መከስከስ ቀጥሏል። አውሮፕላናችን እንዴት፣ ለምን፣ በምን እና በማን እንደተከሰከሰ፡ ታወቀ አልታወቀ፡ ምንም የሚፈጥረው ነገር የለም። እውሩን ዓለማችንን ለመቀስቀስ ይህን መሰሉ “አደጋ” መከሰት አለበት። የዓለምን ትኩረት የሚስብው የአውሮፕላን አደጋ ነው። የአውቶብስ አደጋ ያን ያህል አይሆንም።
ይህ የአውሮፕላን አደጋ በኢትዮጵያ በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ መከሰቱ፣ እንዲሁም አውሮፕላኑ በተለይ ለአፄ ኃይለ ሥላሴ ውድቀት ምክኒያት በሆነውና ጥልቁ የአጋንንት ዋሻ በሚገኝበት “ቢሸፍቱ ሆራ” መከስከሱ፡ ዲያብሎስ መለቀቁን እና የ ጦርነቱም ሂደት ወደ መጨረሻው ምዕራፍ መቃረቡን ነው የሚጠቁመን።
ከክርስቶስ ተቃዋሚዎች አንዱ የሆነው ግብረሰዶማዊው የፈረንሳይ መሪ፤ ማክሮን ልክ አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት ማግስት ሹልክ ብሎ ወደ ላሊበላ መጓዙ (በ አብይ ጾም ከ አብይ አህመድ ጋር) በደንብ የተቀነባበረ ትልቅ ነገር እንዳለ ይጠቁመናል።
የኢትዮጵያ ቴሌኮምን “መውረስ” የምትፈልገዋ ፈረንሳይ ከጀርመን ጋር በማበር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን እና አየር መንገድ ከኢትዮጵያ እጅ መንጠቅ ትሻለች። ለገንዘቡ ብለው ሳይሆን “ኢትዮጵያ” ለሚለው ስም። ልክ “ጤፍ” የሚለውን መጠሪያ ሊነጥቁን እንደሚፈልጉት። ቡናውን “ኮፊ” ወይም “አራቢካ” ቢሉት ምንም አይቀርብንም፤ ይውሰዱት።
የተከሰከሰው አውሮፕላን ጥቁር ሳጥን (ብርቱካናማው ሳጥን፡ ጥቁር ይባላል „Orange is the new Black“) እንደተገኘ በመጀመሪያ ወደ ጀርመን ይላካል ተብሎ ነበር፤ ነገር ግን ጀርመን አይ ይቅርብኝ አለች፤ ባለፈው ወር ላይ የጀርመን ፕሬዚደንት አውሮፕላን በአዲስ አበባ “ተበላሽቶ” አልንቀሳቀስም ማለቱ በጣም አስደንግጧቸዋል፤ ለሁለተኛ ጊዜ ነበርና። ጥቁሩ ሳጥን በመጨረሻ ወደ ፈረንሳይ እንዲላክ ተወሰነ። ደም መጣጩ ፕሬዚደንት ማክሮን በመቶ ሃምሳ ስድስት ሰዎች ደም የተቀባውን ሳጥን ወደ ፈረንሳይ ይዞ ወደ ፈረንሳይ ተመለሰ ማለት ነው።
ስለ ጥቁሩ ሳጥን ምርመራ ውጤት እውነቱን እንደማይናገሩ መጠበቅ ይኖርብናል።
__________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: ላሊበላ, መከስከስ, አውሮፕላን, አደጋ, ክርስትና, የሃይማኖት ጦርነት, የምዕራብ ውድቀት, የብሔር ግጭት, የአሜሪካ ሴራ, የኢትዮጵያ አየር መንገድ, የኦሮሞ እንቅስቃሴ, ጥቁሩ ሳጥን, ፕሬዚደንት ማክሮን, ፕሬዚደንት ትራምፕ, Ethiopian, Ethiopian Airlines, Plane Crash | Leave a Comment »