ይህ ሚያጠራጥር አይደለም፤ ምስጢሩ የተገለጠለት የዲያብሎስ ሠራዊት በኢትዮጵያ ላይ አተኩሯል፤ እኛን አስተኝቶ እርሱ ወደ ኢትዮጵያ ጠጋ ጠጋ ማለት ከጀመረ ውሎ አድሯል። አሁን በኢትዮጵያውያኑ ከሃዲዎች እርዳታ ሠራዊቱን በግልጽ በማሰባሰብ እናት ኢትዮጵያን ከብቧታል፣ ሠርጎ ገብቷል፣ ዓለማዊውን የመንግስት እና መንግስት ያልሆነ መዋቅር ሁሉ ተቆጣጥሮታል።
“የታሪክ አባት” በመባል የሚታወቀው ዝነኛው የግሪክ ዓለማዊ ፈላስፋ፤ ሄሮዶትስ እንኳን ከሁለት ሺህ ዓመታት በፊት እንዲህ ሲል ተናግሮ ነበር፤
“ረጅም እድሜ የሚያስገኘው የውሃ ምንጭ የሚገኘው በኢትዮጵያ ነው”።
አዎ! ከሌሎች ብዙ ነገሮች ጋር፡ የውሃው ምንጭ የሚገኝባት እና የህይወት ዛፉ የሚበቅልባት ቦታ ያለው በአገራችን ነው።
የሉሲፈራውያኑ ቀጠሮዋቸው አሁን ደርሷል። ለአዲሱ የምድር መንግስት ምስረታ ይህችን የተቀደሰች ቦታ ከኢትዮጵያውያን እጅ ፈልቅቆ መንጠቅ የመጨረሻው ግባቸው ነው። ለዚህ ግባቸውም መሰናክል የሚሆኑትን ጽኑ ተዋሕዶ ኢትዮጵያውያኑን አንድ ባንድ በማፈናቀል፣ በመመረዝ ብሎም በመግደል ኢትዮጵያን “ለማጽዳት” በመታገል ላይ ናቸው።
ደጋግሜ የምናገረው ነው፡ የ ዶ/ር ማዕረግ ያላቸው ኢትዮጵያዊውያን በየመስኩ ብቅ ብቅ እንዲሉ እየተደረገ ነው (የ ዶ/ር ማዕረግ ከ666 ማኽተሞች አንዱ ነው)። ዶ/ር አብይ፣ ዶ/ር ደብረጺዮን፣ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ ዶ/ር አድሃኖም ወዘተ።
ሰሞኑን በተሠራጨው ዜና፤ “አሜሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዘንድ የኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ በብዛት ተስፋፍቷል” ብለው ሲናገሩ ሰምተናል፤ ከዚህ ዜና ጀርባ የተለመደው ተንኮል አለበት። አውሬው በፈጠረው አጋጣሚ ሁላ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያውያንን ማንቋሸሽ ወይም መኮነን አለበትና። በረሃብ፣ በበሽታ፣ በጦርነት ወዘተ።
ከሃጢዓታችን የተነሳ በጣም የረቀቀውን፣ ዘላለማዊን እና የእግዚአብሔርን ሕግ የሚከተለውን ሥርዓት ወደ ጎን በማድረግ ሉሲፈራውያኑ ባጠመዱልን ጊዚያዊ ደካማ ርዕዮተ ዓለማት (ካፒታሊዝም፣ ኮሙኒዝም፣ ፌሚኒዝም፣ እስላም፣ ዲሞክራሲ፣ ሊበራሊዝም ወዘተ)ጊዚያችንና ጉልበታችንን እናባክናለን። በዚህም ለአውሬው ልጓም አመች ሰለምንሆን ልክ ጅራቷን ለመያዝ እንደምትሽከረከር ውሻ ምንም ነገር ሳንይዝ እራሳችንን ደግመን ደጋግመን ለመጉዳት እንበቃለን።
አንድን ሕዝብ አዕምሮውን በማጠብ ለመቆጣጠር ያስችለው ዘንድ አውሬው በኢትዮጵያ ላይ የሚጠቀምበት ስልት፦
- 1ኛ. የሕዝቡን ሞራል ማውደቅ (ዘመነ ኃይለ ሥላሴ፦ ድርቅ፣ ረሃብ የነገሠበት)
- 2ኛ. አገሪቷን መተናኮል/ማናጋት የግጭት፣ ቀውስ መፍጠር፣ የጦርነት እና ዕልቂት ዘመን(ዘመነ ደርግ፦ ጦርነት፣ ግድያ፣ ድርቅ፣ በሽታ፣ ስደት የሰፈኑበት)
- 3ኛ. የመረጋጋት ዘመን (ዘመነ ኢህአዴግ/ ዘመነ ሸኽ አላሙዲን፦ ሰላምና የ ኢኮኖሚያዊ እድገት የታየበት)
እንደገና ተመልሶ፦
1ኛ. እና 2ኛ. የሕዝቡን ሞራል ማውደቅ ብሎም አገሪቷን መተናኮል/ማናጋት የግጭት፣ ቀውስ፣ ጦርነት እና ዕልቂት ዘመን(ዘመነ ግራኝ አህመድ)
በዚህም መሠረት የኢትዮጵያውያኑን ሕዝብ ቁጥር ለመቀነስ ብሎም ሃገራቸውን ለመቆጣጠር ላለፉት ፳፯ ዓመታት በመሠረቷቸውና ባደራጇቸው የፌደራል ክልሎች መካከል ግጭቶች ይካሄዳሉ።
በኢትዮጵያ የስልጣን ለውጥ ከተካሄደ ከአሥር ወራት ገደማ በኋላ በሀገሪቷ የተለያዩ ክልሎች ውስጥ ብዙ ሕይወት የቀጠፉ የኅብረተሰብ ብጥብጦች በመፈጠር ላይ ናቸው። ይህ የተከሰተው ለበርካታ ዓመታት የፖለቲካ መረጋጋት ከሰፈነ በኋላ ነው። ኢትዮጵያ ምናልባት አሁን እስከ መገነጣጠል ድረስ ሊያደርስ የሚችል ጽኑ ብጥብጥ ሊያጋጥማት ይችላል። እነዚህም ግጭቶች ድርቅን፣ ረሃብን፣ በሽታን እና ሞትን ይወልዳሉ። ይህም ሁኔታ ለብዙ ኢትዮጵያውያን ማለቅ፣ መፈናቀል እና መሰደድ ምክኒያት ይሆናል። ይህን የሚታዘበው የዓለም አቀፋዊው ማሕበረሰብም ለ ”እርዳታና” “ሰላም ለመፍጠር” ያዘጋጀውን ሠራዊት በጣልቃ ገብነት ወደ ኢትዮጵያ ይልካል፤ የመረጠውንም ተዋሕዶ ያልሆነ አዲስ ነዋሪ ያሠፍራል፤ በዚህም የህይወት ዛፍ የምትገኝበትን ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ይቆጣጠራል ማለት ነው።
አዎ! እግዚአብሔር ለአባታችን ኖህ የገለጠለትንና የማርያም መቀነት ያረፈባቸውን የኢትዮጵያ ቀለማት ከስነደቅ ዓላማችን ላይ ይሠርዙ ዘንድ የሉሲፈርን ኮከብ እንዲያሳርፉበት እንዳዘዟቸው፤ አሁንም የህይወትን ዛፍ መቀዳጀት አላማቸው እንደሆነ የሚጠቁመንን ሰንደቅ ዓላማቸውን („ኦሮሞ” የሚባሉት የሚይዙትን) በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። ኢትዮጵያውያን የእግዚአብሔር ልጆች ኮከቡ ከባንዲራቸው ላይ እንዲነሳ ሲሹ፥ ሉሲፈራውያኑ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች ደግሞ ባንዲራውን በዋቄዮ አላህ ባለ–ዛፍ ባንዲራ ለመተካት እየታገሉ ነው።
ታሪክ እንደሚያስረዳን፤ አፄ ኃይለ ሥላሴ ከሥልጣን ሊወገዱ ጥቂት ዓመታት ሲቀራቸው፡ ሉሲፈራውያኑ በሰሜን ኢትዮጵያ (የህይወት ዛፍ በሚገኝበት አካባቢ)ሃይለኛ ድርቅ እንዲፈጠር አደረጉ፤ በዚህም በብዙ ሚሊየን የሚቆጠሩ ተዋሕዶ ኢትዮጵያውያን ህይወታቸውን አጡ፤ ኢትዮጵያ ሞራሏ ወደቀ። ኢትዮጵያ የሚለው ስም የረሃብ ተመሳሳይ ቃል መግለጫ ሆነ።
በወቅቱ የነበሩ ብዙ የዓይን ምስክሮች ስለዚህ ጉዳይ እንዳጫወቱኝ፤ ይህ ዜና በእነ ቢቢሲ እና የተባበሩት መንግስታት አማካኝነት በመላው ዓለም እንዲሠራጭ ተደረገ፤ ብዙም ሳይቆይ፤ የአሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ጀርመን እና ፈረንሳይ የናቶ ሠራዊት በትግራይ እና ወሎ እንዲሠፍር ተደረገ። (የናቶ ሠራቲ እዚያ ምን ያደርግ ነበር??? ጸሐፊዎቻችን እና የሜዲያ ሰዎች በዚህ ጉዳይ ላይ ለምን እንዳልተናገሩ/ እንደማይናገሩና እንደማይጽፉ በጣም ነው የሚገርመው።) እንግዲህ አሁን ለሚካሄደው ትግላቸው በወቅቱ መርዛማ ዛፋቸውን መትከላቸው ነበር ማለት ነው። የ፶ ኛው ዓመት ኢዮቤልዩአቸውን እየጠበቁ ነው።
ሆኖም ብዙ ልንጎዳ እንችላለን፤ ነገር ግን ከአለቃቸው ከዲያብሎስ ጋር አንድ በአንድ እየተሠባበሩ የራሳቸውን መውደቂያ ያዘጋጃሉ እንጅ አገራችንን ሙሉ በሙሉ ሊቆጣጠሯት አይቻላቸውም።
ለማንኛውም፤ አባቶቻችንን ፍዬል ጣልያንን ያንበረከኳት በሁዳዴ ጾም ነበርና፥ እኛም በዚህ የአብይ ጾም ወቅት የዲያብሎስን ሽንገላ መቃወም እንዲቻለን፣ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ መልበስ ያስፈልገናል። ወገብን አጥብቆ ለመያዝ ዝናር እጅግ አስፈላጊና በጦርነት ሥፍራ መታጠቅ እንደሚገባ እንዲሁ፣ ለመንፈሳዊ ውጊያ እውነትን እንደዝናር መታጠቅ ይገባናል። በውጊያው ውስጥ ከእውነት በቀር ሌላ ነገር መቀላቀልና መሸቃቀጥ ፈጽሞ አይገባንም። በውጊያው ውስጥ ከጭካኔና ካለመራራት ይልቅ እውነተኛ የሆነውን የክርስቶስን ጠባይ በሕይወታችን ገንዘብ ማድረግ ይገባናል። እውነትን እየሠዉ ውጊያ የለም፣ ከእውነት እየቀነሱ ውጊያ የለም፣ በእውነት ላይ እየጨመሩ በመሸቃቀጥ ውጊያ የለም፤ እውነት እንደዝናር ታጥቆ በመዋጋት ግን እውነተኛ ውጊያና ድል በዚያ አለ።
የተጠራነው፣ “ለእውነት እንጂ በእውነት ላይ ምንም ለማድረግ አይደለም”(፪ቆሮ. ፲፫፥፰)፤ ማናቸውንም ነገሮች መፈጸም ያለብን በእውነት መንገድ ብቻ በመሄድ ነው። ያለእውነት ሰይጣንንም ሆነ አገልጋዮቹን ሐሰተኝነታቸውን በማጋለጥ ድል ልንነሣቸው አንችልም። በማኅበረሰባችን እሳቤ “ዋሽቶ ማስታረቅ” እንደመልካም እሴት ይቆጠራል፤ ነገር ግን ያለእውነት የሚሆነው ማናቸውም ትጥቅ ለዲያብሎስ ፈንታ የመስጠት ያህል ምቹ ነው።