Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • February 2019
    M T W T F S S
     123
    45678910
    11121314151617
    18192021222324
    25262728  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

ሳውዲ ሴቶች ወደ አውሮፓ በብዛት በመሰደድ ላይ ሲሆኑ፡ ፳ሺህ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ደግሞ እንደ ከብት ለሳውዲ ሊሸጡ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 18, 2019

ይህ ወገኖቼ ካለፈው ዘመን የከፋ ዘመናዊ ባርነት ነው

የግራኝ አህመድ መንግስት በመጭው መጋቢት ወር ብቻ ሃያ ሺ ኢትዮጵያውያን ሴቶችን ለሳውዲ አረቢያ ለመሸጥ መወሰኑን የሳውዲ ሜዲያዎች ዘግበዋል።

፳፩ ኛው ክፍለ ዘመን ወገኖቻችን ወደ እስላም ሃገራት ለሥራ የሚያደርጉት ጉዞ በ ፲፰ ኛው ክፍለዘመን ጫካ ለመመንጠር በባርነት ተገደው ወደ አሜሪካ ከተወሰዱት አፍሪቃውያን ጋር ተመሳሳይነት አለው፤ በአረብ ሃገራት የሚታየው የሥራ ባሕርይ እንዲያውም ከዚያ በጣም የከፋ ነው። ከሦስት መቶ ዓመታት በፊት እንደ አሁኑ በቂ መረጃ በሌለበት የጨለማው ዘመን የተወሰነ ቁጥር ያላቸው አፍሪቃውያን ተገደው የተወሰዱ ሲሆን፤ አሁን ደግሞ ሁሉ ነገር ግልጥ ብሎ በሚታይበት ዘመን የራሳችን ሰዎችና መንግስታችን የአገሪቷን ዜጎች ለጠላት ይሸጣሉ፤ ለሰላሳ አመታት ያህል ባልተቋረጠ መልክ

ነፃ ሆነው የተፈጠሩት ኢትዮጵያውያን ለዚህ ዓይነቱ ባርነት በ ፳፩ ኛው ክፍለ ዘመን መጋለጣቸው እጅግ በጣም ነው የሚያሳዝነውና የሚረብሸው። በተለይ ለታሪካዊ ጠላቶቻቸውና ለእግዚአብሔር አምላካቸው ጠላቶች መሆኑ በይብለጥ የሚያስቆጣ ነው።

ባለሥልጣናቱ በእህቶቻችን ገንዘብ መሥራቱን ቀጠሉበት ማለት ነው፤ “በቃን!” ለማለት በቂ ጊዜ ነበራቸው። ዛሬ በዚህ ጽንፈኛ ተግባር ላይ የተሠማሩትን ባለሥልጣናት እና ተቋማት እግዚአብሔር የሚገባቸውን ፍርድ ይስጣቸው!!!

____________

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: