Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 20, 2019
ጃንዋሪ 21ን በጣም የሚፈልጋት ኃይል ባለፉት ቀናት ብዙ የግድያ መስዋዕቶች እንዲፈጸሙ አድርጓል፦
ኬኒያ፥ ጃንዋሪ 15 /2019
- ሆቴል ውስጥ 21 ሰዎች ተሰው፥ ከመስከረም ፩ ጥቃት የዳነውን አሜሪካዊ ጨምሮ
ኮሎምቢያ፥ ጃንዋሪ 17 / 2019
ሜክሲኮ፥ ጃንዋሪ 18 / 2019
ኃይለኛ የእሳት ቃጠሎ በመቀስቀሱ፤
- መጀመሪያ፦ 66 ሰዎች ሞቱ
- ቀጥሎ፦ 73 ሆኑ፤ 7×3 = 21
- ቀጥሎ፦ 79 ሆኑ፤ 7+9 = 16
- 666
የጨረቃ ግርዶሽ፡ ጃንዋሪ 21/2019
ጨረቃዋ በመሬት እና በፀሐይ መካከል ትሆናለች፦ ቀይ ደም የለበሰችው ጨረቃ በተለይ በአሜሪካ ላይ ስትሽከረከር ትታያለች።
አስገራሚ የሆነውን የእሳት ገጽታ እንመልከት፦
ዔሳውያኑ አሜሪካ እና አውሮፓ ኢትዮጵያን መተናኮል ከጀመሩ ቆይተዋል፤ በየጊዜው ምልክትና ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶዋቸዋል ግን እንደ እስማኤላውያኑ አጋራቾቻቸው በፈረዖናዊ ትዕቢት ስለተወጠሩ እጆቻቸውን ከአገራችን ላይ ማንሳት ተስኗቸዋል።
በዚህ የፈረንጆች ዓመት ሉሲፈራውያኑ በፕሬዚደንት ትራምፕ ላይ ምናልባት አስከፊ ጥቃት ሊፈጽሙ ይሆናል፤ ሥልጣኑን ሙሉ በሙል ለመቆጠጠር። ስለዚህ የአገራችን ጠላቶች ባለፈው ዓመት ልክ በዚህ ጊዜ ሚነሶታ ውስጥ የጠነሱስትን ተንኮል ይገፉበት ይሆናል። በዚህም በአሜሪካ ላይ ከመስከረም ፩ ከበድ ያለ ፍርድ ይመጣል!!!
_________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: 21, መስዋዕት, ሜክሲኮ, ቃጠሎ, ቍጥር ፳፩, አሜሪካ, አውሮፓ, እሳት, ኬኒያ, ኮሎምቢያ, ደም ጨረቃ, ግድያዎች, Blood Moon, Eclipse, Fire, Full Moon, Sacrifice | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 20, 2019
የ60 ዓመቷ እናት “ማሪ ጄን ፒዬር”፡ በፍሎሪዳዋ ማያሚ ሂልተን ሆቴል ቅርንጫፍ እቃ አጣቢ ሆነው ለአሥር ዓመታት ያህል ሠርተዋል። ትውልደ ሃይቲዋ ማሪ ጄን ሰንበት ሰንበት ለመሥራት ፈቃደኛ ያልነበሩ አጥብቂ ክርስቲያን በመሆናቸው፡ ወደ ቤተክርስቲያን መሄድ ይችሉ ዘንድ ለስድስት ሰንበታት ያህል ወደ መሥሪያ ቤት አልሄዱም ስላሉ በሆቴሉ አለቃዋ ከሥራቸው ተሰናበቱ። በዚህም ምክኒያት በቀድሞ አሠሪዋ ላይ ክስ ለመመስረት ተገደዱ።
ጉዳዩም ለፍርድ ቤት በቀረበበት ወቅት እናት ማሪ የሚከተለውን ብለው ነበር፦
“እግዚአብሔርን ስለምወደው ሰንበት ሥራ የለም በእሑድ እግዚአብሔር መከበር አለበትና”
የማሪ ጠበቃም በማከል፦
“ማሪ የክርስቶስ ወታደር ናት፤ በተመሳሳይ መልክ አድልዎ እየደረሰባቸው ላሉት ለሁሉም ሠራተኞች አርአያ ትሆናለች”
ብለዋል።
ባለፈው ሰኞ ዕለት ፍርድ ቤቱ የማሪ ቀድሞ አሠሪ፡ ሂልተን 21 ሚልዮን ዶላር እንዲከፍል እንዲሁም ለቀጣይ ክፍያ 35,000 ዶላር እና ለደረሰባቸው ስሜታዊ እና አእምሯዊ ህመም $ 500,000 ተጨማሪ መክፈል እንዳለበት ወስኗል።
ጠበቃዋም ውሳኔውን አስመልክቶ የሚከተለውን ብሎ ነበር፦
“ይህ ጉዳይ ገንዘብን የሚያመለክት ጉዳይ አልነበረም፣ እንደ ሂልተን ሆቴል ትላልቅ ለሆኑ ድርጅቶች መልእክት ለመላክ እንጂ” “የፈለግከውን ያህል አንጋፋ ብትሆን፣ የሰራተኞቹን ደም እና ላብ መውሰድ ከፈለጉ እነሱን በተሻለ ሁኔታ መንከባከብ ይገባቸዋል ወይም ቢያንስ በእምነታቸው ባይጋፏቸው ጥሩ ነው።”
አርአያችን ሊሆኑ የሚገባቸው ጎበዝ እናት ናቸው! ግሩም የፍርድ ቤት ውሳኔ!
ሁሌ የሚያሳስበኝ በአገራችን፡ ሰንበትን ጨምሮ በበዓላቱ ሁላ ሱቆች፣ ገባያዎችና ዳንኪራ ቤቶች ገንዘብ ሲያሽከረክሩና ሲጯጯሁ መታዘቤ ነው። እመነተ–ቢስ የሆኑት ብዙ የምዕራባውያን አገራት እንኳን ለሰንበትና ለበዓላት ሱቆቻቸውን እንዲዘጉ ያደርጋሉ።
____________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith, Life | Tagged: ሂልተን ሆቴል, ማያሚ, ሠራተኛ, ሥራ, ሰንበት, ቅጣት, አሜሪካ, አሠሪ, እሑድ, ዕረፍት, ፍሎሪዳ, ፍርድ ቤት, Christian, Dishwasher, Hilton Hotel, Marie Jean Pierre, Sunday | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 20, 2019
____________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: Addis Ababa, ቃና ዘገሊላ, አዲስ አበባ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት, የካ ሚካኤል, ዲያብሎስ, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith | Leave a Comment »